Get Mystery Box with random crypto!

የድንግል ማርያም ልጆች!♥ጥያቄና መልስ ቻናል!

የቴሌግራም ቻናል አርማ teyakaenamels — የድንግል ማርያም ልጆች!♥ጥያቄና መልስ ቻናል!
የቴሌግራም ቻናል አርማ teyakaenamels — የድንግል ማርያም ልጆች!♥ጥያቄና መልስ ቻናል!
የሰርጥ አድራሻ: @teyakaenamels
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.99K
የሰርጥ መግለጫ

መንፈሳዊ የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልሶች የሚተላፉፈበት!
አስተያየት
@teyakaenamles_bot
https://t.me/joinchat/AAAAAExg87tr37X8VNFEjA
✝ወደ ፌስቡክ ፔጃችን ለመቀላቀል➡https://www.facebook.com/
✝ወደ ይቱብ ቻናል ለመቀላቀል➡https://youtube.com/channel/UCRc7pSmO4wrs-mhAfxwEuOw

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-30 18:55:12 የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ


ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
ዘማሪ አርቲስት ይገረም ደጀኔ
ዘማሪ ገ/ዮሐንስን ገ/ፃዲቅ
ቀሲስ ምንዴዬ ብርሀኑ
ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ
ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ
ዘማሪ ዲ/ን ሮቤል ማቲያስ
ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን
ዘማሪት አቦነሽ አድነው
ዘማሪት ዶ/ር ሔለን ተስፋዬ

እና የሌሎችንም ...........

ዘማሪዎችን መዝሙሮች እና አዳዲስ
መዝሙሮችን ለማግኘት ከስር OPEN
የሚለውን ይጫኑት።

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
█ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █
█ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █
█ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
82 viewsኦርቶዶክስ ፕሮሞሽን ❖ ፬, 15:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 13:28:08

1.1K viewssara mariyam, 10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-14 19:55:19

887 viewsናፍቆት ተስፋ, 16:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-14 14:47:07

761 viewsናፍቆት ተስፋ, 11:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-13 20:44:19

743 viewssara mariyam, 17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-13 10:35:30 ☞ነሐሴ 7 በእመቤታችን ፅንሰት አመታዊ መታሰቢያዋ ቅድስት ድንግል ማርያምን ያስገኘችልን ቅድስት ሀና ማርያምን ከፍ ከፍ እናድርጋት፡፡
☞የድኅነት ብላቴና ብፅዕት ሐና ሆይ ሰላምታ ይገባሻል፡፡
☞የይቅርታ ብላቴና ብላቴና ብፅዕት ሐና ሆይ ሰላምታ ይገባሻል፡፡
☞የልዕልና ብላቴና ብፅዕት ሐና ሆይ ሰላምታ ይገባሻል፡፡
☞የጽድቅ ብላቴና ብፅዕት ሐና ሆይ ሰላምታ ይገባሻል፡
☞የክብር ብላቴና ብፅዕት ሐና ሆይ ሰላምታ ይገባሻል፡፡
☞ሐዳስ ጣዕዋ ለተባለች እመቤታችን እናት የሆንሽ ብፅዕት ሐና ሆይ ሰላምታ
ይገባሻል፡፡
☞ብፅዕት ሐና ሆይ ከባሕር የምታሻግሪ የሕይወት መርከብ አንቺ ነሽ እልሻለሁ፡፡
☞የዓለሙ ሁሉ መድኀኒት የምትሆኝ የማርያም እናት ቅድስት ሐና የሥጋና የደም
ፍጥረታትና የሰማይ መላዕክት ባንቺ ታደሱ፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ ካማረ ከማኅሌት መጠራት ይልቅ ለስም አጠራርሽ ሰላምታ
ይገባሻል፡፡
☞ቅድስ ሐና ለአፍሽና በረዶ ለሚመስሉ ጥርሶችሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ ድንግል ማርያምን ወላዲተ አምላክ ለጠባችው ለጡቶችሽ
ለአንቺ ጉንጭ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ቅድስ ሐና ሆይ ድንግል ማርያም ለተሸከመ ለሆድሽና ንጹሕ ለሆነው ለልብሽ
ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ለሐሳብሽ ምሳሌ የማይገኝለት ቅድስት ሐና ሆይ የምድር ፍጥረታትና የሰማይ
ፍጥረታት ሁሉ ባንቺ ይመካሉ ባንቺ ይደሰታሉ፡፡
☞ቅድስ ሐና ሆይ ለኅንብርትሽና ለተመረቀው ድንግል ማርያምን ለተሸከመው
ማኅፀንሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
☞ቅድስት ሐና ሆይ በማይጠፋ የግምጃ ልብስ ለሥጋሽ መገነዝ ሰላምታ
ይገባል፡፡
☞የማርያም እናት የእየሱስ ክርስቶስ አያት ሐና ሆይ ድንገት እናንጠራ ለንሰሐ
ጥቂት አቆይኝ እንጂ ሞትስ በዓለም አይተወኝም፡፡
☞ድርሳነ ኢያቄብ ወሐና
☞07/2014 ዓ.ም
790 viewsናፍቆት ተስፋ, 07:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 22:01:25 https://yt6.pics.ee/4cdv7y
648 viewsናፍቆት ተስፋ, 19:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-06 10:02:42 ጾመ ፍልሰታ እንኳን አደረሳችሁ / አደረሰን አሜን

ጾመ ፍልሰታ

<ፍልሰታ > የሚለው ቃል የሚገልጸው ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለቆ መሔድን መሰደድን መፍለስን ያመለክታል። ይህም የእመቤታችንን ሥጋ ከጌቴሴማኒ ወደ ገነት መፍለሱን በኋላም በገነት በዕፀ ሕይወት ስር ከነበረበት መነሳቱን ለማመልከት ይነገራል።

ጾመ ፍልሰታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፷፬ ዓመት በዚች ምድር ኖራ እንደ አንድ ልጇ መሞቷን መነሳቷንና ማረጓን ያዩ ዘንድ ሐዋርያት የጾሙት ጾም ነው። ጾሙ ከነሐሴ ፩ ቀን እስከ ነሐሴ ፲፮ ቀን ሲጾም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአዋጅ ከደነገገቻቸው ሰባቱ አጽዋማትም አንዱ ነው።

ኃይማኖታዊ መሠረት

እመቤታችን ከአባቷ ከኢያቄም እና ከናቷ ከሐና ነሐሴ ፯ ቀን ተጸንሳ ግንቦት ፩ ቀን በሊባኖስ ተወልዳለች። <እምሊባኖስ ትወጽዕ መርአት ፦ ከሊባኖስ ሙሽራ ትወጣለች > እንደተባለ ። እምቤታችን በእናት አባቷ ቤት ሦስት ዓመት፤ በቤተ መቅደስ አሥራ ሁለት ዓመት፤ ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ፡ ከዮሐንስ ወልደዘብዴዎስ ዘንድ አሥራ አራት ዓመት ከዘጠኝ ወር ቆይታ በ ፷፬ ዓመት ዕድሜዋ በ፵፱ ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች። የእመቤታችንን ስም የሚገልጹ የውዳሴ ጽሑፎችም በእድሜዋ ልክ ተደርሰዋል። ለምሳሌ የውዳሴ ማርያም ቁጥር ፷፬ ነው፤ የመልክአ ማርያም ቁጥርም ፷፬ ነው።[1]

ባረፈች ጊዜ ቅዱሳን ሐዋርያት ተሰባስበው አስከሬኗን ይዘው ወደ ጌቴሴማኒ መቃብር ለማሳረፍ ሲሄዱ አይሁድ ለተንኮል አያርፉምና ተተናኮሏቸው። ቀድሞ ልጇ ሞቶ ተነሳ፣ አረገ እያሉ ሲያስቸግሩን ይኖራሉ: ደግሞ አሁን እሷም ተነሳች፣ አረገች ሊሉ አይደል በማለት አይሁድ ተሰባስበው አስከሬኗን ለማቃጠል ሲተናኮሉ እግዚአብሔር በተአምር ከነዚያ አይሁዶች አድኗቸዋል ። የእመቤታችንንም አስከሬን ነጥቆ ከሐዋርያው ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር በገነት በዕፀ ህይወት ስር አኑሯቸዋል ። ከዚያ በኋላ ሐዋርያት ሥጋዋን አግኝተው ይቀብሩት ዘንድ በአረፈች በስምንተኛው ወር ከነሐሴ ፩ ጀምሮ እስከ ነሐሴ ፲፬ ቀን ድረስ ሁለት ሱባዔ ይዘው በአሥራ አራተኛው ቀን ሥጋዋን ከጌታ ተቀብለው በጸሎትና በምህላ በፍጹም ደስታ በጌቴሰማኔ አሳረፉት ። በ ሦስተኛውም ቀን ተነስታ ስታርግ ከሰኡቃዊያን ወገን የሆነው ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ አያት። እርሱም በቀብር ስርዓቱ ጊዜም አልነበረም። ሀገረ ስብከቱ ህንድ ስለነበር ሊያስተምር ወደዛው ሂዶ ነበርና። በዚያም ሲያስተምር ሰንብቶ በደመና ተጭኖ ሲመጣ ያገኛታል። ትንሳኤዋን ከርሱ ሰውራ ያደረገች መስሎት አዝኖ «ቀድሞ የልጅሽን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንቺን ትንሳኤ ሳላይ ቀርቼ ነውን ?» ብሎ ቢያዝንባት እመቤታችንም ከርሱ በቀር ማንንም ትንሳኤዋን እንዳላየ ነግራ አጽናናችው። ለሌሎቹ ሐዋርያትም እንዲነግራቸው ለምልክትም /ለምስክርም እንዲሆነው ሰበኗን /መግነዟን ሰጥታው አረገች። ቶማስም ኢየሩሳሌም ደርሶ ሐዋርያትን «የእመቤታችን ነገርስ እንደምን ሆነ?» ሲል ቢጠይቅ «አግኝተን ቀበርናት እኮ» አሉት። እርሱ ምስጢሩን አዉቆ ደብቆ «ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር» እንዴት ይሆናል ? አይደረግም ይላቸዋል። ሊያሳያቸውም መቃብሩ ዘንድ ሂደው ቢከፍቱት አጧት። እርሱም «አታምኑኝም ብዬ እንጂ እርሷስ ተነስታ አርጋልች» በማለት ሁኔታውን ተረከላቸውና ለምስክር ይሁንህ ብላ የሰጠችውን ሰበኗን አሳያቸው። ከዚህ በኋላ ለበረከት ይሆናቸው ዘንድ ሰበኑን ተካፍለው ወደየአህገረ ስብከታቸው ሄዱ። ዛሬ በቅዳሴ ጊዜ ዲያቆኑ በሚይዘው የመጾር መስቀል ላይ በሁለት ቀዳዳዎች አልፎ ተጠምጥሞ የምናየው መቀነት መሰል ጨርቅ የዚያ ሰበን ምሳሌ ነው።

በዓመቱ ሐዋርያት ከያሉበት ተሰባስበው ቶማስ ትንሳኤሽን አይቶ እኛስ እንዴት ይቀርብናል ብለው ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምርው ሱባዔ ቢይዙ ከሁለት ሱባዔ በኋላ እንደገና ትንሳኤዋንና እርገቷን ለማየት በቅተዋል። ሐዋርያዊት የሆነች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናም ምእመኖቿ ከእመቤታችን በረከትን እንዲያገኙ ይጾሙ ዘንድ ይህን ሐዋርያት የጾሙትን ጾም እንዲጾሙ አዉጃለች። ምእመናንም በተለየ መልኩ በጾም በጸሎት በሱባዔ ጽሙድ ሆነው ይህን ወቅት ያሳልፋሉ።

የእመቤታችን ትንሳኤ ድንገት እንደእንግዳ ደራሽ እንደ ዉሀ ፈሳሽ የተደረገ ሳይሆን በቅዱሳት መጻሕፍት በትንቢተ ነቢያት የተገለጸ ነው። ነቢዩ ዳዊት በመዝሙር ፻፴፩ ቁጥር ፲ ላይ «አቤቱ ወደ እረፍትህ ተነስ አንተና የመቅደስህ ታቦትም» ይላል። በዚህም ምዕመናንን ወደ ምታሳርፍበት ወደ መንግሥተ ሰማያት የመቅደስህ ታቦት ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነስ አለ። ታቦት የጽላት ማደርያ እንደሆነ ሁሉ እምቤታችንም ለክርስቶስ ማደርያ በመሆኗ አማናዊት ታቦት ትባላለች።

ንጉስ ሰሎሞንም በመኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ምዕራፍ ፪ ቁጥር ፲ ላይ «ውዴ እንዲህ ብሎ ተናገረኝ፤ ወዳጄ ሆይ ተነሽ፡ ውበቴ ሆይ ነይ» ብሏል። እዚህ ላይ «ወዳጄ …ዉበቴ»“ የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት ። ክቡር ዳዊት መዝሙር ፵፬ ቁጥር ፱ ላይ «በወርቅ ልብስ ተጎናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች» እንደሚል ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛነቱን ከፈጸመ በኋላ ወደ ቀደመ ክብሩ እንዳረገ እመቤታችን ቅድስት ድንገል ማርያምም በቀኙ ትቀመጥ ዘንድ «ተነሽ ነይ» አላት ። እንግዲህ ይህንና የመሰለዉን ሁሉ ይዘን የእናታችንን እረፍቷን ትንሳኤዋን እንዘክራለን እንመሰክራለንም።
1.0K viewsናፍቆት ተስፋ, 07:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-06 10:02:27
741 viewsናፍቆት ተስፋ, 07:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 21:50:16
889 viewssara mariyam, 18:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ