2021-02-13 11:50:13
የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሪፖርቶች ፦
- ባለፉት 24 ሰዓት በመላው ዓለም 12,356 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መሞታቸው ሲረጋገጥ 423,186 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ታውቋል።
- በአሜሪካ ወረርሽኙ ሲጀምር 1 ብሎ የጀመረው የሟቾች ቁጥር ዛሬ ላይ 492,521 ደርሷል። በየዕለቱ በሺዎች የሚቆጠሩ አሜሪካውያን እንደቅጠል እየረገፉ ነው። ባለፉት 24 ሰዓት 2,908 የUS ዜጎች በበሽታው ሞተዋል።
- በሜክሲኮ በኮቪድ-19 በሽታ የሞቱ አጠቃላይ ሰዎች 171,234 ደርሷል። ከነዚህ መካከል የ1,474 ሰዎች ሞት የተመዘገበው ትላንት ነው።
- ብራዚል ውስጥ ባለፉት 24 ሰዓት 1,204 ሰዎች በበሽታው ሞተዋል፤ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 237,601 ደርሷል።
- በተጨማሪ ሩስያ 507 ፣ UK 758 ፣ ስፔን 530 ፣ ፈረንሳይ 429 ፣ ጀርመን 523 ፣ ጣልያን 316 ዜጎቻቸውን በ24 ሰዓት አጥተዋል።
- በአህጉረ አፍሪካ አጠቃላይ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 3,753,441 የደረሱ ሲሆን ከነዚህ መካከል 97,950 ህይወቱ ኣልፏል።
- በዓለም አቀፍ ደረጃ በኮቪድ-19 በሽታ የተያዙ ሰዎች 108,730,653 ደርሰዋል ከነዚህ መካከል 2,394,127 ሰዎች ሲሞቱ 80,753,857 ሰዎች አገግመዋል።
ክትባትን የተመለከቱ ጉዳዮች ፦
- በአሜሪካ ዋሽንግቶን ግዛት እስከዛሬ አጠቃላይ የተሰጠው የኮቪድ-19 ክትባት 1 ሚሊዮን ደርሷል። የጤና ጉደዮች ባለስልጣናት ትላንት አርብ 1 ሚሊዮን ክትባት መሰጠቱትን ይፋ አድርገዋል።
- ጎረቤት ኬንያ ይህ ወር ሳይጠናቀቀ የአስትራዜንካ ክትባትን እንደምትቀበል እና ለዜጎቿ እንደምትሰጥ ተሰምቷል። ኬንያ የክትባቱ ውጤታማነት ላይ የሚነሱትን ሀሳቦች ችላ በማለት ነው ክትባቱን የምታስገባው።
@tikvahethiopia
5.6K viewsShegye Marie, 08:50