2021-02-16 00:40:20
"በ6 ወር 449 ሰዎች በትራፊክ አደጋ ሞተዋል" - የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የመንገድ ትራፊክ ደህንነት መምሪያ
በአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የመንገድ ትራፊክ ደኅንነት መምሪያ የትራፊክና ስታስቲክስ ባለሙያ ም/ኢንስፔክተር ሰጠኝ አለሙ የትራፊክ አደጋ አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱን ገለፁ።
ባለፉት 6 ወራት አንድ ሺህ እንድ መቶ ሃያ አንድ የትራፊክ አደጋ መመዝገቡን አሳውቀዋል፡፡
በዚህም ፦
- 449 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል
- 461 ሰዎች ከባድ የአካል ጉዳት
- 487 ሰዎች ደግሞ ለቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል
- ከ28 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወድሟል፡፡
ለአደጋዎች መከሰትም ከ29 በላይ የትራፊክ አደጋ መንስኤዎች ተለይተዋል፡፡ ይሁን እንጅ በቀዳሚነት ከፍጥነት ወሰን በላይ በማሽከርከር ብቻ 234 አደጋ ደርሷል፡፡
ለእግረኞች ቅድሚያ ባለመስጠትም 206 አደጋዎች ደርሰዋል፡፡
ይህ ደግሞ ከምንም በላይ የአሽከርካሪዎችን የማሽከርከር ብቃት እና ሥነ ባህሪ ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ መሆኑን ምክትል ኢንስፔክተር ሰጠኝ አለሙ ገልፀዋል፡፡
አደጋውን ለመቀነስ ተደጋጋሚ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ ቢከናወንም አጥጋቢ ውጤት አለመገኘቱን ነው ያስረዱት፡፡
አደጋው እየተባባሰ በመምጣቱም የጋራ መፍትሔ እንደሚሻ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፦ አብመድ
7.9K viewsShegye Marie, 21:40