Get Mystery Box with random crypto!

Medical Information- ጤና መረጃ®️🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ tenamereja — Medical Information- ጤና መረጃ®️🇪🇹 M
የቴሌግራም ቻናል አርማ tenamereja — Medical Information- ጤና መረጃ®️🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @tenamereja
ምድቦች: ጤና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 41.15K
የሰርጥ መግለጫ

ሕክምና፣ መረጃ፣ ሥራ ቅጥር፣ የትም/ት ዕድል መረጃዎች ላይ የሚያተኩር ቻነል ነው።
መፍትሔው አለን!
Contact፡ @tenaye24
📱 0974512131
Facebook: facebook.com/tenamereja
🌿 ለማስታወቂያ- Advert your services
0974512131
@tenaye24

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 459

2021-02-14 08:25:23 Apply Here!
859 viewsShegye Marie, 05:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-14 00:20:41
4.7K viewsአብርኆት 2021, 21:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-14 00:14:38
ዓለም አቀፍ የጋይናኮሎጂ ካንሰር ማኅበር ( International Gynecologic Cancer Society) በዓለም አቀፍ ፕሮግራሙ በዚህ ሳምንት በዓለም ዙሪያ ካስመረቃቸው አምስት ሰብስፔሻሊስት ሐኪሞች ውስጥ ሁለቱ ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ትናንት በድረገጹ ላይ ባስነበበው "የእንኳን ደስ ያላችሁ" መልእክቱ አስታውቋል።
ሁለቱ ኢትዮጵያውያን ሐኪሞች
1. ረዳት ፕሮፌሰር ዶ/ር ቤቴል ደረጀ( የቅዱስ ጳውሎስ ሜሊነየም ሕክምና ኮሌጅ ባልደረባ ) እና
2. ረዳት ፕሮፌሰር ዶ/ር ዳዊት ወርቁ( የጥቁር አንበሳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ባልደረባ) ናቸው።
Dr Gebeyaw Addis
4.7K viewsአብርኆት 2021, 21:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 20:48:42 Apply Here!
1.4K viewsአብርኆት 2021, 17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 20:40:48
132 MB, For WiFi Users Only!
5.0K viewsአብርኆት 2021, edited  17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 20:34:57
የዜጎችንን የጤና ፍላጎት መሠረት ያደረገና ከማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ጋር በሚጣጣም መልኩ ተሻሽሎ የተዘጋጀው ብሔራዊ የጤና ፖሊሲ ውይይት ተካሒዶበታል።
------------
በዚህ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ በሚገኘው ብሔራዊ የጤና ፖሊሲ ውይይት ላይ ዶ/ር ሊያ ታደሠ በ1986 ዓ.ም ተቀርጸው ላለፉት ዓመታት በአገራችን ሲተገበር የቆየው የጤና ፖሊሲ በሽታ መከላከል ላይ ያተኮረ መሠረታዊ የጤና አገልግሎትን በስፋት ተደራሽ በማድረግ፣ ተላላፊ በሽታዎችን በመካላከልና መቆጣጠር ረገድ የህብረተሰቡን አጠቃላይና በተለይም የእናቶችና ህፃናት ጤናን በማሻሻል በኩል ከፍተኛ አስተዋጽዖ እንደነበረው ገልጸዋል፡፡
ይሁን እንጂ አሁን ላይ አገር አቀፍና አለም አቀፍ ሁኔታዎችን፣ የህብረተሰቡን እድገትና የጤና ፍላጎት ግምት ውስጥ ያስገባ፣ የተገኘውን የጤና ውጤት ይበልጥ ለማጠናከር ወቅታዊ አገራዊና አለምአቀፋዊ ጤናና ጤና ነክ ሁኔታዎች ይበልጥ ምላሽ ለመስጠት እንዲሁም ከአገራችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ጋር በተጣጣመ መልኩ የጤና ፖሊሲውን ማሻሻል አስፈላጊነት አብራርተዋል፡፡
ረቂቅ ብሔራዊ የጤና ፖሊሲው በውይይት የተገኙ ግብዓቶችን በማካተት በቀጣይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በሚደረገው ውይይት ከዳበረ በኋላ ለሚመለከተው አካል ቀርቦ የሚጸድቅ ይሆናል፡፡
@tenamereja
4.8K viewsአብርኆት 2021, edited  17:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 20:34:13
ቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በመቀበል የመማር ማስተማሩን ሥራ መጀመሩን አስታወቀ።
የዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር ዶ/ር ከሰተ ለገሰ፣ የመማር ማስተማሩን ሥራ የጀመሩት ከሚጠበቁት 13ሺህ ተማሪዎች ውስጥ አብዛኛዎቹን በመቀበል ላይ መሆኑንና የቀሩትንም እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል።
ተማሪዎቹ በመቐለ ማኅበረሰብ እና ተማሪዎች ኅብረት አቀባበል እየተደረገላቸው ከየካቲት 1 ቀን 2013 ዓ.ም አንሥቶ ትምህርታቸውን መከታተል መጀመራቸውን አስታውቀዋል።
የተማሪዎች መማሪያ ክፍሎች፣ መኝታ ቤቶች፣ ምግብ ማብሰያ እና መመገቢያ አዳራሾችን የኮሮና ወረረሽኝን ለመከላከል ታሳቢ ባደረገ መልኩ ቀድመው መሰናዳታቸውን ዶ/ር ከሰተ አስረድተዋል።
ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ዓመት ድረስ የሚማሩት እነዚህ ተማሪዎቹ የተቋሙን ሕግ እና ሥርዓት አክብረው ትምህርታቸውን መከታታል እንደሚጠበቅባቸውም ገልጸዋል።
ትምህርታቸው መከታተል ከጀመሩት መካከል ከደቡብ ክልል የመጣው የአዲሀቂ ካምፓሰ የሶሾሎጂ ሁለተኛ ዓመት ተማሪ ቸርነት ሺፈራው ትምህርት በመጀመሩ መደሰቱን ገልጾ፣ በንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት በኩል ግን እጥረት ስላለ እንዲስተካከል አስተያየቱን ሰጥቷል።
የእኛ ተማሪዎች ሕልም በሰላም እና ፍቅር ትምህርታችንን መከታተል እና ተመርቀን ራሳችንና ሀገራችን መጥቀም ነው ያለው ደግሞ የሁለተኛ ዓመት ሶሾሎጂ ተማሪ እንድሪስ አብዱ ነው።
ከኦሮሚያ ክልል የመጣው ተማሪ ጫላ ሳፋይ በበኩሉ ዩኒቨርሲቲው ለመማር ማስተማር የሚያስችል የግቢው መሠረተ ልማት ማሟላቱን ገልጿል።
በምግብ ሰዓት ግን በወረፋ ብዛት ምክንያት ለብዙ ሰዓታት እየጠበቅን መሆኑ ታውቆ መፍትሔ ሊበጅለት ይገባል ማለቱን ኢዜአ ዘግቧል።
@tenamereja
4.3K viewsአብርኆት 2021, 17:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 20:33:16
3.9K viewsአብርኆት 2021, 17:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 20:33:12 ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ቀብሪ ደሀር ፣ ወለጋ ፣ አርሲ እና የኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች አስመርቀዋል፡፡
ጅማ ዩኒቨርስቲ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰመስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ በተገኙበት በሁለተኛ ዙር በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ያሠለጠናቸውን 4ሺህ 311 ተማሪዎችን ዛሬ አስመርቋል፡፡
ጅማ ዩኒቨርስቲ ባለፈው ጥቅምት ወር 1ሺህ 409 ተማሪዎችን ማስመረቁ ይታወሳል፡፡
ቀብሪ ደሀር ዩኒቨርሲቲም የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ እና ሌሎች የክልልል እና የፌዴራል የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 612 ተማሪዎቹን አስመርቋል፡፡
ወለጋ ዩኒቨርሲቲም 3ሺህ 398 ተማሪዎችን በወለጋ ስታዲየም አስመርቋል፡፡
አርሲ ዩኒቨርሲቲ በበኩሉ በህክምና ስፔሻሊቲ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ 23 ሰልጣኞቹን በመጀመሪያ ዙር አስመርቋል፡፡
የኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ 2ሺህ 39 ተማሪዎቹን በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በተገኙበት አስመርቋል፡፡
በተያያዘም የአዲግራት ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መርሃ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 576 ተማሪዎች ሲያስመርቅ፥ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶክተር ሳሙኤል ሁርካቶ፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
የአማራ አመራር አካዳሚ ለመጀመሪያ ጊዜ 37 ተማሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን፥ በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር አካዳሚው ለዚህ የበቃው በሠራተኞች ድካም በርካታ ፈተናዎችን አልፎ ነው ብለዋል፡፡
ወቅቱ በአንድ በኩል ትልልቅ እና አስደሳች ውጤቶች የተመዘገቡበት፤ በሌላ በኩል ደግሞ ፈተናዎች የበዙበት ሀገራዊና ክልላዊ ነባራዊ ሁኔታ ውስጥ ነው ያለ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ሀገሪቱ በቀጣይ የምትፈልገውን ከችግር መውጫ መንገድ መቀየስ ወሳኝ መሆኑንም ነዚህ ወቅት ገልጸዋል፡፡
አያይዘውም ኢትዮጵያዊነት የማይደበዝዝ ይልቁንም በይበልጥ የሚደምቅና የሚፈካ የጋራ ማንነታችን ሊሆን ይገባልም ነው ያሉት፡፡
FBC
4.0K viewsአብርኆት 2021, 17:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 20:32:37
የጋምቤላ መምህራን ትምህርና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሠለጠናቸውን ሁለት ሺህ 496 ተማሪዎችን ዛሬ አስመረቀ።
Via EBC
@tenamereja
3.9K viewsአብርኆት 2021, 17:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ