2022-07-05 22:34:54
ሰሜን አፍሪካዊቷ ታላቅ ሀገር አልጄሪያ ነፃነቷን ከፈረንሳይ ለመቀዳጄት 1.5 ሚሊዮን ሰማእቶችን ገብራለች ! ለዚያም አልጀራ የ 1.5 ሚሊዮን ሰማእታት ሀገር ትባላለች !
አፍሪካዊቷ ታላቅ ሀገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ ፈፅሞ ነፃነቷን ላለማስነካት ሚሊዮን ውድ ልጆቿን ገብራለች ! በደምና በአጥንት ተቦክታ የተማገረቺው ሀገራችን የአለም የነፃነት ቀንድል ትባላለች !
ይህንን ታሪካችንን ሊያወይቡ ፤ እልፍ አእላፍ ጀግኖች ተሰውተው እዚህ ያደረሷትን ሀገር ሊያፈርሱ የሚደክሙ ሁሉ እነርሱ ይፈ*ርሳሉ እንጅ ኢትዮጵያ እንደሆነ አትፈርስም ! ለዚህ ታሪክ ምስክር ነው ። በትውልድ መካከል የበቀሉ አረ*ሞች ይነቀላሉ እንጅ ለአረሞቹ ሲባል አዝመራው አይነቀልም !
የአልጀሪያን ታሪክ ዝም ብየ አላነሳሁትም ። በነፃነት ታሪክ ተጋድሎዋ ከእኛ ጋር የሚያመሳስላት ነገርም ስላላት እንጅ ። አልጀሪያዊያን ደማቸውን አፍስሰው አጥንታቸውን ከስክሰው ነፃነቷን ያጎናፀፏት ሀገር ብትሆንም ቅሉ ልክ እንደኛ ሀገር ሁሉ የጠላቷ ተልእኮ አስፈፃሚ ባንዳ*ዎች የሞላባት ሀገርም ነበረች ።
በርካታ ሚሊዮኖች ለነፃነታቸው ተፋልመው ሚሊዮኖች ሸሂድ ( ሰማእታት ) ሲሆኑ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ባን*ዳዎች ደግሞ ከቅኝ ገዥዋ ፈረንሳይ ጎን ተሰልፈው ሀገራቸውንና ህዝባቸውን ይወጉ ነበረ ። ባን*ዳ እንደዚህ ነው ! ለፍፁም አራ*ዊትነቱና ጥቅመኝነቱ ውድ ሀገሩን ውድ ህዝቡን ውድ እምነቱን ይሸጣል ። የሀገራችን ባን*ዳዎችም ልክ እንደዚያው ናቸው ።
ኢትዮጵያ ታላቅ የጀግና መስዋእቶች ሀገር ብትሆንም በዚያው ልክ በርካታ ባን*ዳዎች የሚርመሰመሱባት ሀገርም ናት ። ከሻእቢያ እስከ ህወሀት ከዚያም እስከ ኦነግ የሀገራችን የአንድነት እንቅፋቶች የሉአላዊነት ፀሮች ሆነው ኖረዋል እየኖሩም ነው ።
እነዚያ የአልጀሪያ ባን*ዳዎች ፈረንሳይ ከሀገሪቱ ተሸንፋ ተንበርክካ ስትወጣ ፀሀያቸው ጨለመባቸው ። አብዛኞቹ በአልጀሪያ ጀግኖች እስከወዲያኛው ሲሰናበቱ የተቀሩት ደግሞ ከወራሪው ሀይል ጋር በመፈርጠጥ ወደ ፈረንሳይ ተሰደዱ ። እዚያ ግን ፈረንሳይ ባለውለታየ ናችሁ አላለቻቼውም ። እንደውም ተዋርደው ተንቀው ፈረንሳዮች ተፀይፈዋቸው መኖር እጣፈንታቸው ሆነ ። ባን*ዳነት ትርፉ ይህ ነው ። ውርደትና ርክሰት !!
የሀገራችን ባን*ዳዎችም ተጠራርገው ይወ*ገ*ዳሉ !! የንፁሀን የግፍ እንባ የትም አያደርሳቸውም !
ኢትዮጵያ ግን ታሸንፋለች !!!!!
#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
2.3K views19:34