Get Mystery Box with random crypto!

Seid Social

የቴሌግራም ቻናል አርማ seidsocial — Seid Social S
የቴሌግራም ቻናል አርማ seidsocial — Seid Social
የሰርጥ አድራሻ: @seidsocial
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.83K
የሰርጥ መግለጫ

አለም አቀፋዊ መረጃዎች ምልከታዎችና ታሪካዊ ክስተቶች ይቀርቡበታል

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-27 15:22:35
የአማራ ክልል መንግስት አሁንም ለሽ ብሎ ተኝቷል ። የክልሉ ህዝብ እንደጠላት ተፈርጆ የተደጋጋሚ ጦርነት ሰለባ ሆኖ ሳለ የክልሉ መንግስት ግን ከሰላሙ እስከ ጦርነቱ ጊዜ ማንቀላፋትን ተያይዞታል ።

ህዝባችንን ካደራጁት እንኳንስ ለህወሀት ለማንም የማይመለስ የማይንበረከክ ህዝብ መሆኑ ከአንድም በተደጋጋሚ ጊዜ አስመስክሯል ። ግን ያልተደራጀ ህዝብ ሁሌም የጥቃት የወረራ ተጋላጭ ነው ።

ስንት ጊዜ ነው ህዝብ ይደራጅ ይደራጅ እየተባለ የሚለፈፈው !?

አሁንም ቢሆን ከረፈደ በሗላ ብዙ መስዋዕትነት ከከፈልን በሗላ እንደገና ከመንደፋደፍ ቀድሞ ይዘጋጅ ። የክልሉ ልዩ ሀይልና ፋኖ እንደ በቀደሙ ይነቃነቅ ። በእኛ ሜዳ ውስጥ ከምንጫዎት በነርሱ ሜዳ እንጫወት ።

የአማራ ክልል መንግስት ሀላፊነቱን ይወጣ ! ህዝቡን ያነቃንቅ !

ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
2.1K views12:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 11:53:13
መንግስት አሁንም ለቆቦ ግንባር ከፍተኛ ትኩረት መስጠት አለበት ።
እርግጥ ነው በዚያ ወደ ቆቦ ለመምጣት የሚታገለው የህወሀት ሀይሌ ከፍተኛ ኪሳራና ሽንፈት ደርሶበታል ። ግና የህወሀት ጦር በአንዴ መሸነፍ እጅ የሚሰጥ ወይንም የሚመለስ አይነት ጦር እንዳልሆነ በተደጋጋሚ አይተናል ። የመጀመሪያው ዙር ሲያልቅበት ሌላ ዙር እየተካ እስከመጨረሻው ዙር የሚጋደል ሀይል ነው ። በመሆኑም የአንድ የሁለት ጊዜ ድሎች ሳያዘናጉን የኛም እስከመጨረሻው የሚመክት አይነት መሆን አለበት ።
ከዚያ በዘለለ ግን መከላከያ ሀይላችን ከመከላከል ውጊያ ቢወጣ ። ህወሀት ለሚከላከል ጦር ሳይሆን ለሚያጠቃ ጦር የበለጠ ተጋላጭ ነው ።

ጦርነቱ ወደ ቆቦ ባይጠጋም ህዝቡ ግን ስጋት ላይ ነው ያለውና መንግስት በወሎ ግንባር አስተማማኝ ስራ መስራት አለበት ።

ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
2.1K views08:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 22:30:32 ዛሬ ሱልጧን አልብ አርስላን ልእለሀያሉን የሮም የባይዛንታይን ኢምፓየርን ያንበረከከባት ቀን ነች !!!
አዎ የማንዚኪርት ( መላዝከርድ ) ጦርነት - የከፈኑ ጦርነት !!

የባይዛንታይኑ ግሪካዊው ንጉስ ሮማኖስ 300,000 ጦሩን አሰልፎ መላው ሙስሊም አለምን ለመቆጣጠር እየገሰገሰ ነው ። ያኔ ገና እስልምናን ከተቀበሉ ብዙም ያልቆዩት ቱርኮች ሙስሊሙን አለም የመጠበቅ ግደታን ተሸክመዋል ። በርግጥ ለጦረኞቹ ቱርኮች ጦርነት ምናቸውም አልነበረም ። " ጦርነት ባህላዊ ጨዋታችን ነው " ሊሉስ የሚገባቸው ቱርኮች ።

ያኔ የምስራቅ ሮም የባይዛንታይን ኢምፓየር በመቶ ሺህ የሚቆጠር ጦሩን ሲያንቀሳቅስ የሰልጁቆቹ ሱልጧን አልብ አርስላን ጦርነቱን ለማስቆም የተቻለውን አደረገ ። ጦርነቱ ገፍቶ ከመጣ በመሳሪያም በሰው ሀይልም አነስተኛ ስለሆኑ የጦር መሳሪያ እርዳታ ኦንኳ ቢያደርጉ ብሎ ለሙስሊሞቹ የአባሲያ ኸሊፋ መልእክት ቢልክም የተሰጠው ምላሽ ግን " ልንሰጥህ የምንችለው ምንም አይነት መሳሪያ የለንም " የሚል የስንፍና መልስ ነበር ።

ስለዚህ ሱልጧን አልብአርሰላን ጦርነቱን እንዲያቆምና እንዲስማማ ለንጉስ ሮማኖስ መልእክት ቢልክም የንጉሱ መልስ ግን " መላው የኢስላሙ አለምን በቁጥጥራችን ስር አድርገን መካና መድናን በእጃችን ካስገባንና እናንተንም ወደመጣችሁበት ካባረርናችሁ በሗላ እንስማማለን " የሚል የምፀት መልስ ላከለት ። መዋጋት ግድ ሆነ !

የሱልጧን አልብ አርስላን ተስፋ አንድ ብቻ ሆነ - አሸናፊው ጌታ አላህ !
እናም ወታደሮቹን ሰበሰበና እንደዚህ አላቸው " ወላሂ ሀገራችን ከገቡ ሴቶቻችንን መጫዎቻ ያደረጓቸዋል ፣ ልጆቻችንን ባርያ ያደርጓቸዋል ፤ መሳጂዶቻችንን የአስካሪ መጠጥ መፈንጪያ ያደርጓቸዋል ከመዋጋት ውጭ አማራጭ የለንም " አላቸው ።
በዚህ ጊዜ ሸይኹ አቡናስር አልሀነፊ ተነሱና " ወላሂ እናን ለአላህ ዲን ነው የምትዋጉት እናንተ የምትጋደሉት አላህ ከዲኖች ሁሉ የበላይ አድርጎ ለላከው የአላህ ድን ነው አልብአርስላን ሆይ አላህ የሙስሊሞችን ድል በአንተ እጅ ሊያደርገው እመኛለሁ " አሉት ።

አልብአርስላን ነጭ ከፈኑን ይዞ ወጣ ለወታደሮቹም " እኔ ዛሬ አዛዣችሁ አይደለሁም መዋጋትና ሸሂድነትን የፈለገ ከኔ ጋር አብሮኝ ይዋጋ መሄድ የፈለገ ይሂድ የሚከለክለው የለም " በማለት ተናገራቸው ። ሁሉም ወታደሮቹ አብረን ሸሂድ እንሆናለን ! በማለት በከፍተኛ ለቅሶና ወኔ ቃላቸውን አስተጋቡ ። ሁሉም ተላቀሱ !! ሁሉን ሸሂድነትን ናፈቁ ። እናም ሁሉም ነጭ ከፈናቸውን ያዚና ወደ ወይ ድል ወይ ሸሂድነትን ናፍቀው ወደ መላዝከርድ ተመሙ ። 300,000 የሮም ወታደሮች በ አስር ሺዎች ከሚቆጠሩ የቱርክ ሙስሊሞ ጦር ጋር ተላተሙ ።

በመጨረሻም ሰልጂቆች አሸነፉ ። አላህም አልብአርስላንን አሸናፊ አደረገና ሙስሊሙን አለም ከውድመት ጠበቀው ። አልብአርስላን የባይዛንታይኑን ንጉስ ማረከው ። ቱርኮችም የአሁኗ ቱርክ ምድር ላይ ሰፈሩ ። ባይዛንታይን ከዚያ በሗላ አላገገመም ።

ያ የአለምን ታሪክ የቀየረው ጦርነት የተካሔደው ልክ በዛሬዋ እለት በ 1071 እ.ኤ.አ ነበር ።

Seid Mohammed Alhabeshiy

ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
2.3K views19:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 14:29:17
የኢትዮጵያ አየር ሀይል ወደ ሙሉ ድብደባ ገብቷል ። ዛሬ መቀለን የጥቃት ኢላማው አድርጎ በአየር ደብዶቧል ።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ዛሬ ባወጣው መግለጫ ህወሀት የተኩስ አቁሙን አፍርሶ ጥቃት እየፈፀመ በመሆኑ ከዚህ በሗላ የሽብር ቡድኑን የሚያዳክሙ እርምጃዎችን አጠናክሮ እንደሚወስድ አሳውቋል ።
በመሆኑም ንፁሀን የትግራይ ነዋሪዎች ከጦር ኢላማዎችና ወታደራዊ ጣቢያዎች እንዲርቁ አሳስቧል ። ይህም መከላከያ ሰራዊቱ የትግራይ ክልል የጦር ኢላማዎችን ለማውደም ሙሉ ዝግጅት ማጠናቀቁን ያሳወቀበት ነው ።

ኢትዮጵያ ታሸንፋለች !!

Seid Mohammed Alhabeshiy

ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
2.3K views11:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 21:57:49
ቱርክ ዛሬም ቃሏን አድሳለች - ከኢትዮጵያ ጎን በፅናት እቆማለሁ ስትል !

የቱርኩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሜቭሉት ካቩስኦግሉ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ቱርክ በየትኛውምና በማንኛውም መልኩ ከኢትዮጵያ ጎን ትቆማለች ለኢትዮጵያም ሁሉንም አይነት ድጋፍ ታደርጋለች በማለት ዳግም የቁርጥ ቀን አጋርነቷን አረጋግጧል ።

ቱርክ ኢትዮጵያ ሰላም የሰፈነባትና የተረጋጋች እንድትሆን ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥልም አረጋግጠዋል ሲል TRT world ዘግቧል ።

ቱርክ በባለፈው ጦርነት እነዚያን ሚዛን ቀያሪ ድሮኖቿን ጨምሮ በርካታ ወታደራዊና ድፕሎማሲያዊ ድጋፎችን ያደረገችልን የቁርጥ ቀን አጋራችን ናት ። ያኔ ምእራባውያን ፊታቸውን ሲያዞሩብን ኤርዶጋን ዶክተር አብይ አህመድን ቱርክ ድረስ በመጥራት አጋርነቱን ያሳየበት መንገድ መቼም የሚረሳ አይደለም ።

ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
2.4K views18:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 20:20:17
የህወሀት ዋነኛ ጥንካሬ የመከላከያ አመራሮችን በማስከዳት መቁረጥና ወታደሩን መበታተን ነው ።

በዚህ ስልት ህወሀት ከ ተንቤን በረሀ ተነስታ እስከ ደብረሲና ለመድረስ ችሏል ። ያም የሆነው የመከላከያ መሪዎችን ማስከዳት በጥቅም ማታለል መቻሉ ነው ። ከ*ሀዲዎቹ የጦር መሪዎችም ከባባድ ጦር መሳሪያዎችን እያስረከቡ ወታደሩን እያስቆረጡ ህወሀት ያሸንፍና ቃል የገባላቸውን ስልጣንና ገንዘብ ያገኙ መስሏቸው እናት ሀገራቸውን ክደዋታል ። ወታደሩን በስነልቦና በመስለብ አንድነቱን በትነው ታሪክ የማይረሳውን ጠበሳ አሳርፈው አልፈዋል ።

የ 11 ኛው ክፍለጦር ከነመሳሪያው ከነ ወታደሮቹ አንድም ሳይወጣ በትግራይ በረሃ የቀረው በክፍለጦሩ መሪ ክህ*ደ*ት ነበር ። የጦር ሀይላችንን እንቅስቃሴ እያንዳንዷን ምስጢር እያሳለፉ በመስጠት ህወሀትን የከባባድ ጦር መሳሪያዎች ባለቤት አድርገውትም ነበር ።

እነዚያ የካዱ የጦር መሪዎች በርግጥ ሁሉም የእጃቸውን አግኝተዋል ። እነርሱን መመንጠር በመቻሉም ህወሀት 500 ሺህ ጦሩን የጥይት ሲሳይ አድርጎ አሳፋሪ ሽንፈትን ተከናንቦ ተመልሷል ። የህወሀት ወዳጆችም 500 ሺህ ወታደሮቻቼውን ተቀላቅለው የው*ሻ ሞትን ሞተዋል ።

አሁን ከዚያ ስህተቱ የተማረ ባንዳዎችን የመነጠረ በፈተና ውስጥ ተፈትኖ ያለፈ በትጥቅም በሞራልም በቁጥርም የደረጀና የገዘፈ ጦር ባለቤት ነን ። ህወሀት ካሸነፈ የሚያሸንፈው በባ*ንዳዎች ክህ*ደት ብቻ ነው የሚሆነው ። ከዚያ ውጭ የትግራይን ህዝብ የትግራይን ወጣት ከማስጨረስ የዘለለ አሁን የሚያሸንፈው ጦር የለንም ።

ህወሀትን እስከመጨረሻው የማስወገጃው ጊዜው አሁን ነው ። ኢትዮጵያ በዚህ የናት ጡት ነካሽ እያለቀሰች የምትኖርበት ጊዜ ማብቃት አለበት !

ኢትዮጵያ ታሸንፋለች !!!

ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
2.3K views17:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 23:32:57
" ቆርጦ የገባው ተቆርጦ ተመቷል ፤ ፊት ለፊት የገባው ደግሞ ተረፍርፏል ። የትግራይ ህዝብ እንዲሞት ፍላጎት አልነበረንም ህወሀት በገፍ አሰልፎ የማገደው ወጣት ተረፍርፏል ። የህወሀት ሰሬዊት አሰጨረሳችሁን እያለ ሲንጫጫ ነበር ከ 11:00 ጀምሮ በቀጠለው ጦርነት ህወሀት ያሳካው አንዲት ነገር እንኳ አልነበረም ። የሰላም አማራጩን ወደ ጎን ካለ ይህንን ቡድን ሳናጠፋ አንመለስም "

ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ለ EMS ከሰጡት መግለጫ የተወሰደ

t.me/Seidsocial
2.4K views20:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 22:22:35
በተለይም የወሎ ህዝብ በከፍተኛ ዝግጁነትና ተጠንቀቅ መቆም አለበት !

እርግጥ ነው የወሎ ህዝብ እንደባለፈው ጦርነት በተበታተነ ሁኔታ አይደለም ያለው ። አሁን የወሎ ፋኖ ከመከላከያ ሰራዊቱና ከአማራ ልዩ ሀይል ጋር በአንድነት ግንባር ላይ ይገኛል ። ዛሬም ህወሀት በሰጠው መግለጫ ጦርነት ከፈቱብኝ ካለው ውስጥ የወሎ ፋኖን በቀዳሚነት አንስቷል ።

ግና መላው የወሎ ህዝብ ከዚህ የበለጠ መንቃት መዘጋጀት አለበት ። ይህ ወራሪ ሀይል ወሎ ሳይደርስ ከተመታ የትም አያመልጥም ። መላው የአማራ ህዝብ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ እንደተለመደው በአንድነት መቆም አለበት ።

ህወሀት ፈረ*ስ ነው ከሗላ የሚጋልቡት አድርግ የሚሉትን ነው የሚያደርገው ። ይህንን ወራሪ ሀይል እስከመጨረሻው ማ*ጥፋት መቻል አለበት ። ሀገራችን ሁሌ እሾህ አጠገብ እንዳለ ቁልቋል ስታለቅስ መኖር የለባትም ። ለዚያ ሲባል እሾሁ መነቀል መወገድ አለበት ።

በተለይ የወሎ ህዝብ ንቃ ! ተደራጅ ! ትጥቅህን አደራጅና የጦር ሀይሉ ደጀንና አለኝታ ሁን !

ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
2.3K views19:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 22:32:30 ፓኪስታን አይደለም ሀያልነት ከልእለሀያላኑ ጎራ ሊያሰልፋት የሚችል አቅም ያላት ሀገር ነበረች ። ከቻይናና ህንድ ቀጥሎ በአለም በሶስተኛነት የሚያስቀምጣት የህዝብ ብዛት ያላትም ሀገር ነበረች ። ግና በሙሰኛ መሪዎቿ አቅሟን የተነጠቀች ሀገር ሆነች ።
ፓኪስታን የሀይማኖት መገፋት የእስልምና መጨቆን የወለዳት ሀገር ነበረች ። እንግሊዝ የህንድ ክፍለ አህጉርን በቅኝ ግዛት ከመቆጣጠሯ በፊት መላው ቀጠና በሙስሊሞች የሚተዳደር ግዛት ነበር ። መቀመጫውን ደልሂ ያደረገው የሙጋል ሱልጧኔት ህንድን ለ 500 አመታት ሰጥ ለጥ አድርጎ መርቷታል ።

እንግሊዝ ህንድን ስትቆጣጠር ከሃንዱዎች ጋር በማበር በሙስሊሞች ላይ ተቆጥሮ የማያልቅ በደልን ፈፅማለች ። በመጨረሻም እንግሊዝ ከህንድ ስትወጣ ሙስሊሞቹ ህንዶች ራሳቸውን ፓኪስታን በማለት ሲገነጥሉ ሂንዲዎቹ ደግሞ ህንድ የምትባል ሀገር መስርተው ተገነጠሉ ። ግና የመገነጣጠል ጦርነቱ ሰቃጣጭነቱን ቃል አይገልፀውም ነበረ ።

የሂንዱ እምነት አራማጆች ሙስሊሞቹን በጅምላ በማጨፈጭፉበት ጊዜ ሙስሊሙን ከሂንዱው የሚለዩበት መንገድ አንዱ ግርዛት ነበረ ። ሙስሊሞች ሲገረዙ ሂንዲዎች ደግሞ አይገረዙም ነበር - ወሸላ ነበሩ ። እናም የተገረዘ ሰው ካዩ ህፃን ቢሆን አዛውንት ሙስሊም ስለሆነ በጅምላ ይገድሉ ነበር ።

ከብዙ መስዋእትነት በሗላ ሙስሊሟ ፓኪስታን በሙስሊሞች ደም ተመሰረተች ። ስፋቷም ከአረቢያ ባህር እስከ ምስራቅ ህንድ ውቅያኖስ የተዘረጋ ነበረ - የዛሬዎቹን ህንድና ፓኪስታንን ያቀፈ ትልቅ ሀገር ። እናም ያኔ ህንድ በፓኪስታን የተከበበች ሀገር ሆነች ። በሙሀመድ አሊ ጂናህ መሪነት ነፃይቱ ፓኪስታን ከአለም ሀያላን አንዷ የሙስሊሞችም ቁንጮ ሀገር ለመሆን ተመሰረች ።

ግና ሀገር አስቀጥሎ ማበልፀግ ሀገር ከመመሰረት የማያንስ ፈተና ያለው ከባድ ሸክም ነበረ ። እንደውም ሀገር ከመቆጣጠር ሀገር መምራት በእጅጉ ይከብዳል ። እናም ፓኪስታኖች ሀገር መመስረት እንጅ ሀገር አስቀጥሎ የማበልፀግን ድል መቀዳጄት ተሳናቸው ። ምክንያት ቢባል የመንግስቶቻቼው የሙስና እና ዘረኝነት ዝቅጠት ። ሀገርን የአንድ ቤተሰብ የማድረግ ንቅዘት ።

እናም ፓኪስታን በተመሰረተች በጥቂት አስርት አመታት ውስጥ ለሁለት ተሰነጠቀች ። ምስራቅ ፓኪስታን ባንግላዴሽ ስትባል ምእራብ ፓኪስታን ደግሞ ያው ፓኪስታን የሚል ስያሜ ይዛ ቀጠለች ።

ፓኪስታን ጠንካራ መንግስታትን አልታደለችም ። በታሪክ አጋጣሚ ብቅ ያሉት እነ ዙልፊቃር አሊ ቡቶ በአጭሩ ተቀጭተዋል ። ሙሰኞቹ የሼሪፍ ቤተሰቦችኛ ወታደሬዊ ዘሪፊ ባለስልጣኖች ዛሬም ድረስ ፓኪስታንን እየጋጡ ካሰበችበት እንዳትደረስ ትብታብ ሆነዋታል ።

ከዘመናት በሗላ ብቅ ያለው ጠንካራው መሪ ኢምራን ኻን ብዙ ቢታገልም በውጭ ሀይሎች ጭምር ተሸርቦበት ከስልጣን ሊወገድ ችሏል ። ግና ኢምራን ኻን እጅ ሳይሰጥ ትግሉን አጧጡፎ ቀጥሏል ። ኢምራን ኻን ከፓኪስታናዊያን ያለው ድጋፍ ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ መሆኑ ብዙ ተስፋ እንዲጣልበት የሚያደርግ ነው ።

ፓኪስታን ቀጣይ ምርጫ ታደርጋለች ። እናም በዚያ ምርጫ ኢምራን ኻን እንደሚያሸንፍ የሚጠራጠር የለም ። ያ ከሆነ ምናልባት ፓኪስታን የተመሰረተችለትን ሆና እናያት ይሆን ??

ሁሉንም ጊዜ ይመልሰዋል !

#Seid_Mohammed_Alhabeshiy

ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
2.4K views19:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 19:37:18
በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ የትግራይ ወገኖቻችን እጣፈንታ ይህን ይመስላል !

አላማ ለሌለው ከንቱ ጦርነት በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ወጣቶች እንደ ቅጠል ረግፈዋል ። መቶ ሺዎች ደግሞ ገና አበባቸውን ሳይጨርሱ ውበታቸው ረግፎ የዘልአለም አካል ጉዳተኛ ሆነው ቀርተዋል ። ይህ ሁሉ ሳይበቃ ዛሬም ሌሎች መቶ ሺዎችን ለመገበር ህወሃት የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ ይገኛል !

ለማን ሲባል ? እኮ ለምን ሲባል ነው ይህ ሁሉ ወገናችን የሚረግፈው የተባለ እንደሆነ ለስልጣን ጥመኞች ሲባል ! ለስግብግብ አረመኔዎች ወንበር ሲባል !

ዛሬ የትግራይ ህዝብ ያለበት ሁኔታ የዛሬ 50 አመት ከነበረበትም የከፋ ነው ። ህፃናቶች ህይወታቸውን ለማቆየት ሲሉ ስጋቸውን ለሴሰኞች እየሸጡ የሚኖሩባት የዋይታ ምድር ናት ትግራይ ። ካለ እርዳታ በህይወት መቆየት የማይቻልባት ምድር ናት ትግራይ ።

ምናለ ህወሃት አንድ ጊዜ እንኳ ተሳስቶ ለትግራይ ህዝብ ቢያዝንለት ? ምናለ ከወንድሞቹ የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ዳግም እንዲጣመር ቢፈቅድለት ?
ዛሬ ለትግራይ ህዝብ ከመሰረታዊ የምግብ ፣ የውሀ ፣ የመብራት ፣ የባንክ ፣ የትራንስፖርት መቋረጥ በላይ የሚያመው የሚሰብረው የሚያሳስበው ነገር የለም ። ሌላው ትርፍ ነው !!

ገና ከጅምሩ ጀምሮ የሽምግልና እና የእርቅ ጥረቶችን ሁሉ ከንቱ ያስቀረው ህወሀትን የትግራይ ህዝብ በቃ ሊለው ይገባል !

#Seid_Mohammed_Alhabeshiy

ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
2.2K views16:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ