2022-07-12 20:13:01
ከ 27 አመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን ነበር በቦስኒያ ሙስሊሞች ላይ እጅግ አስከፊው የዘር ማጥፋት በሰርቢያ ጦር የተፈፀመው ።
ሙስሊሞችን ጨፍልቆ ኦርቶዶክሳዊት ታላቋን ሰርቢያን ለመመስረት ታግሎ ያታገለው ስሎቦዳን ሚሎሶቪች በቦስኒያዎች ጂሃድና በነ ኢራን እና ቱርክ አይተኬ እገዛ ሲከሽፍበት የበቀል እርምጃውን በስሬብሬኒካ ከተማ ላይ ደገሰ ። ለዚህ አላማውም ፅንፈኛውን የሰርቢ ጦር መሪ ራትኮ ሚላዲችን አስታጥቆ ወደ ከተማዋ ላከ ።
ስሬብሬኒካ ያኔ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰላም አስከባሪ እጅ የነበረች ቢሆን ጨፍጫፊውን የሰርቢያ ጦር ግን ማስቆም አልተቻለም ወይንም የማስቆም ፍላጎቱ አልነበረም ። እናም በራትኮ ሚላዲች የሚመራው ጦር የሙስሊሞች ከተማ ወደሆነቺው የስሬብሬኒካ ከተማ ገባ ።
ከዚያ በሗላ የቦስኒያ ሙስሊሞችን ወንዶችና ወንድ ህፃናትን ለብቻ ሴቶችና ሴት ህፃናትን ለብቻ ለያየና ወደ አዘጋጀላቸው ቦታ ወሰዳቸው ። ለብቻ የተወሰዱት ወንዶችና ወንድ ህፃናት በሙሉ እንዲገደሉ ተደረጉ ። በጥይት ጨፍጭፈው የተረፋቸውን በሰይፍ ከዚያም በሰይፍ አልበቃቸው ሲል በቡልዶዘር ከነህይወታቸው ጨፈለቋቸው ። እንደዚያ እየገደሉ ቀድሞ ያዘጋጁት የጅምላ መቃብር ውስጥ በአንድ ላይ ይወረውሯቸው ጀመር ። እነዚህ ፅንፈኛ የሰርቢያ ብሔርተኞች ከቡልዶዘርና ከጥይት የተረፏቸውን ሙስሊሞች ከነህይወታቸው በዶዘር በቆፈሩት መቃብር ውስጥ እየከተቱ አፈር ያለብሱባቸው ነበር ።
የስሬብሬናካ ዘር ማጥፋት ( Genocide ) ግፍ በዚህ አያበቃም ። ከወንዶቹ ነጥለው የወሰዷቸውን ሙስሊም ሴቶች ሁሉም ወታደሮች ህፃናትን ሳይቀር መድፈር ያዙ ።
አንድ የአይን እማኝ ሄግ ለሚገኘው የአለም አቀፉ ፍርድ ቤት ያየውን ጭካኔ ሲናገር እንደዚህ ይላል
" አንድት የወራት እድሜ ያለው ህፃን ያላት ሙስሊም ሴት ቀረበች ከዚያም ደፈሯት በዚህ ጊዜ ህፃኑ ማልበስ ያዘ የሰርቢያ ወታደሮች ይህች የተደፈረች እናት ልጇን ከማልቀስ አስቁሚ አሏት ግና ህፃኑ ማልቀሱን ቀጠለ ። በዚህ ጊዜ አንዱ ወታደር ተቀብሎ አንገቱን ቀን*ጥሶ ጣለው ።
ከዚህ የከፋም አይቻለሁ አንዲቱ ሙስሊም ህፃን ዘጠኝ አመቷ ነው ከዚህች ህፃን ጋር ወንድሟ አብሮ ነበረ ። ወታደሮቹ ያ ወንድሟ እህቱን እንዲደፍር አስገደዱት እርሱ ግን እንቢ አለ እርሱም ህፃን ስለነበር አልደፈራትም ። በዚህ ጊዜ ወታደሮቹ ያንን ልጅ አንገቱን ቆር*ጠው ጣሉት እርሷንም ደፈሯት ። "
ሌላኛው የአይን እማኝ ደግሞ
" የዘጠኝ አመት ልጇ ልትደፈርባት ያለች እናት " እባካችሁ እርሷ ገና 9 አመቷ ነው እርሷን እንኳ ተውልኝ " እያለች ትማፀናቸው ነበር ግና እነርሱ ሊሰሟት አልፈቀዱም ህፃኗን ልጅ ደፈሯት ደሟ በህፃን እግሮቿ ላይ እየፈሰሰ ከመሬት ተዘርራ አየሗት " በማለት ያን ሰቅጣጭ የሙስሊሞች ጭፍጨፋ ተናግሯል ።
የሰርቢያ ብሔርተኞች ያን ሁሉ ሰቅጣጭ የዘር ማጥፋት በመሀል አውሮፓ በቦስኒያ ሙስሊሞች ላይ ሲፈፅሙ በቦታው ያለውና በኔዘርላንድ የሚመራው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰላም አስከባሪ ቅንጣት ታክል እንኳ ሊከላከልላቸው አልቻለም ነበር ። ከዚያም አልፎ የሰላም አስከባሪው ጦር መሪ ያንን ሰቅጣጭ ትእይንት በቀጥታ ይመለከቱ ነበር ።
በዚያች ቅፅበት የሰርቢያ ኦርቶዶክሳዊ ብሔርተኞች ከ 8,000 በላይ ቦስኒያውያንን በጅምላ ሲጨፈጭፉ ከ 25,000 በላይ ሴቶችና ህፃናትን በሰቅጣጭ ሁኔታ ደፈሩ ። ይህ ከሆሎከስት ማለትም ናዚ አይሁዳዊያንን ከጨፈጨፈበት ክስተት በሗላ በአውሮፓ የተከሰተ ትልቁ የዘር ማጥፋት ሆኖ ተመዝግቧል ።
ሗላ ላይ ጭፍጨፋው ካበቃ በሗላ አለምአቀፉ ፍርድቤት በሰርቢያው ጦር መሪ ራትኮ ሚላዲች ላይ የ 700 አመት ( ሰባት መቶ አመት ) እስራት ሲበይን በሌሎችም ላይ ከመቶ አመታት እስከ 50 አመት ድረስ ከፍተኛ እስርን ፈርዶባቸዋል ።
እነ ራትኮ ሚላዲችና ስሎቦዳን ሚሎሶቪች የቦስኒያ ሙስሊሞችን ከምድረገፅ ለማጥፋት የቻሉትን ሁሉ ቢያደርጉም ቦስኒያ ሔርዝጎቬኒያ ግን ዛሬም የሙስሊሞች ሀገር ሆና ቀጥላለች ።
#Seid_Mohammed_Alhabeshiy
ቴሌግራም
t.me/Seidsocial
1.6K views17:13