2022-08-02 18:12:06
በተቀደደ ባሊ ውሀ መቅዳት......!!
...ግሎባሊስቶቹ በካንሰር አሳበው የደፉት አሮን ሱሩሶ የመስከረም 11 የኒዎርክ መንትያ ህንፃዎች ጥቃት የሽብርተኞች ሳይሆን የነሮክፌለር ወጥመድ እንደሆነ ተናግሮ ሽብርተኝነትና ስጋትን የፈጠሩት ሆን ብለው እንደሆነ ተናግሯል።እንዳው "..unending war against terrorism..." በሽብርተኝነት ላይ እማያልቅ ጦርነት....ነበር ያለው።
...ነገሩ ወዲህ ነው....ዲሞክራቱ ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን የቢላድንን ምክትል ደፋውት ብለው አይመን አልዛዋሂሪ በድሮን መገደሉን ነገሩን።የድሮው ዲሞክራት ባራክ ኦባማ በበኩሉ ደግሞ የቢላድንን መገደል በ2011 አበሰረን።ሁለቱም ዲሞክራት ናቸው....የነ ቢልጌት ሎሌዎች መሆናቸው ነው።በነጩ ቤተመንግስት ዲሞክራትና ሪፐብሊክ ግብዳ የፖለቲካ ልዩነት ያላቸው ናቸው።በጣም ይራራቃሉ።
...እንዲህ አይነት ተፈላጊ ሽብርተኛ ገደልኩ ስትል የፖለቲካ ትርፉ ነፍ ነው።የኛ መንግስት እንኳን በቅርቡ የአልሸባቡን አሜሪካ እምትፈልገውን ገደልን ብሎ ሲሰክስ አልነበር.....praise ግድ ነው።
...ሀሳቤ ግን እንዲህ ነው....አስባችሁታል ግን....ሽብርተኝነትን እየፈጠርክ ሽብርተኝነትን ስትፋለም(አሮን ሱሩሶ እንዳለው...)...የሆነ በተቀቀደ ባሊ ውሀ እንደመቅዳት ማለት ነው።...ለምን መሠለህ?!....አሁን ይሄ ተገደለ የተባለው ምክትል አልቃይዳ(የአሁኑ ዋነኛ) ግብፃዊ ነበር።በወቅቱም የታወቀ ሰርጀሪ ባለሙያ ነበር።ትምሮን የጠጣ ዶክተር ነው።ይሄ ሰው ገንዘብ አላጣም በሰላም ቤተሰቦቹን ማስተዳደር መስራት ማደግ መጦር ይችል ነበር....ታዲያ ከአሜሪካ መንጋጋ ጋር ምን ያላትመዋል......?
...በሽብርተኝነት የተቀመጡትን ድርጅቶች ISIS አልቃይዳ አልሸባብ ወዘተ.....እነዚህ ድርጅቶች ውስጥ ያሉትን የአባላቱን ታሪክ ብታጤኑት አብዛኞቹ ቤተሰቦቻቸውን በአሜሪካ ድሮን ያጡ ናቸው።ከልጅ ከሚስት ከናት ከአባቶቻቸው ጋር በሰላም በሚኖሩበት መኖሪያ ቤት ሌላ የሽብር ታርጌት ለመምታት በሚል ሁሉ ነገራቸውን አጥተው ወይ አካላቸው ጎሎ ወይ በፈጣሪ ታዕምር የተረፉ ናቸው።
...አልዛዋሀሪም የዚህ ጦስ ውጤት ነው።ከታዋቂ ሰርጀሪስት ወደ አልቃይዳ መሪነት ወዴት ወዴት??!....ጆ ባይደን እንዳለው...የድሮን ጥቃቱ አፍጋኒስታን ካቡል ውስጥ እንደነበርና ምንም አይነት ተጓዳኝ ጉዳት አለመድረሱን ነው።የታወቀ ነው....የሞተ ሌላ ንፁህ ዜጋ ይኖራል የሱ ቤተሰብ አባል የሆነ የነገው አልዛዋሀሪ ነው....ሙተህም ተተኪህን ማፍራት ማለት እንዲህ ነው።በናንተ ልብ ውስጥ ህያው ነኝ..the people who remain interested in my work are simply carrying the torque!.በተቀደቀለ ኦሾ!...አሁን የሱን ቅሽምና እሚያስፋፉ የሱ ተማሪዎች የነበሩት ናቸው....!!!
ወደ ጉዳዬ ስገባ...
...ሽብርተኝነት ላይ እማያልቅ ጦርነት......አንዱን ገለህ ወንድሙን ሽብርተኛ ማድረግ ማለት ነው።የአሜሪካ ወታደሮች ከአፍጋኒስታን ሲወጡ በአጥፍቶ ጠፊ 6 ወታደሮች ሲገደሉ...የአፀፋ ምላሹ የድሮን ጥቃት ነበር.....10 የአፍጋን ህፃናት ተገለው ነበር።የነዚህ ህፀናት ቤተሰቦች የነገው አልቃይዳ ክንፍ ናቸው።
...ትልቁ ጥያቄ ግሎባሊስቶች ይሄን ሁሉ ትርምስ ለምን ፈለጉት እሚለው ነው.....የመስከረም 11 ጥቃትን አቀነባበሩት(ችግር ፈጠሩ)....የአሜሪካ ህዝብ የሽብር ስጋት እንዳለበት በተግባር አስረዱት....አፍጋኒስታንና ኢራቅን ወረሩ....የአሜሪካን ህዝብና የመካከለኛው ምስራቅን እያፋጁ እነሱ የማዕድን ዘረፋ ትልማቸውን አሳኩ።የአሜሪካ ወታደር 20 አመት አፍጋኒስታን ተቀምጦ ሀገር ከማተራመስ ሽብርተኛ ከማብዛት ውጭ...ታጣቂውን አክራሪ ፅንፍ ታሊባንን ወደ ስልጣን ከማውጠት ውጭ ያደረገው ነገር አልነበረም......
...ግን በወረራ የተገኘ እድል ነበር።እሱም ግሎባሊስቶች አሻንጉሊት የመንግስት ባለስልጣናትን ተጠቅመው የዘረፉት የገነቡት የኢንደስትሪና የዘረፋ ኢምፓየር ነው።ገንዘብ አልጠግብ ብለህ እማያልቅ ጦርነት አቀጣጥለህ ትውልድ ስታፋጅ! አስበው አስኪ ከነሱ ሰይጣን አይሻልም?!
...ቢላድን ሲሞት አልዛዋሀሪ ተተካ ....አሁን አልዛዋሀሪ ሞቷል ሌላ ይተካል....አልቃይዳ ግን እንደሀገር ፀንቶ ይኖራል።በእውነቱ አንድን የሽብር ድርጅት ማክሰም ለአሜሪካው CIA ከባድ አደለም...ሌላ ፍላጎት ሌላ ትርምስ ሌላ አላማ ስላለው ነው።እንዲጠፉ አይፈለግም.....በጣም እንዲጠናከሩም አይፈልጉም...አቅማቸው ተመጣጣኝ እንዲሆን ይተዋሉ እንጂ እነሱን ለማጥፋት ሰርተው አያውቁም።እንዴት 20 አመት ሙሉ ወታደር አዝምተህ ኢንተለጀንስ አሰማርተህ ገንዘብና ቴክኖሎጂ አፍሰህ አልቃይዳን መበተን አቃታቸው???....ኣኣ ማዕዱኑን ማን ይዝረፈው!!።አከተመ!!
http://t.me/Markabyssinia
@እይታዬ
Mark Abyssinia
ሀምሌ 26/2014 ዓ/ም
866 viewsdowen, 15:12