Get Mystery Box with random crypto!

ማቲ ሸገር - Mati Sheger®

የቴሌግራም ቻናል አርማ matiosbirhanu — ማቲ ሸገር - Mati Sheger®
የቴሌግራም ቻናል አርማ matiosbirhanu — ማቲ ሸገር - Mati Sheger®
የሰርጥ አድራሻ: @matiosbirhanu
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.81K
የሰርጥ መግለጫ

ስለ ፍትህ ስለ እኩልነት እና ስለ ዲሞክራሲ

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-02 07:35:53
በደባርቅ ከተማ 16 ሰርጎ ገቦች ተያዙ።

የደባርቅ ከተማ አሥተዳደር በምሽት የኬላ ጥበቃ 16 የአሸባሪውና ተስፋፊው ትህነግ ወራሪ ቡድን አባላት የኾኑ ሰርጎ ገቦችን በቁጥጥር ስር አውሏል።

የአሸባሪውና ተስፋፊው ትህነግ ወራሪ ቡድንን እኩይ ዓላማ ለማስፈፀም በተለያየ ምክንያት ወደ ከተማዋ ገብተው እየተንቀሳቀሱ የመረጃ ማቀበል ሥራ የሚሠሩ 16 ተጠርጣሪ ሰርጎ ገቦች እና ሶስት ህገ-ወጥ መሳሪያ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የደባርቅ ከተማ ከንቲባ ብርሃን ፀጋየ ገልፀዋል።

የአሸባሪውና ተስፋፊው ትህነግ ወራሪ ቡድንን ዳግም ወረራ ለመከላከል በሚደረግ ዘመቻ የመጀመሪያው ተግባር የከተማችን ከሰርጎ_ገብ መጠበቅ እና የደጀንነት ሚና መወጣት ዋነኛና ቁልፍ ተግባር መሆኑ ታውቆ በአደረጃጀት ስምሪት ተሰጥቶ ወደ እየተሠራ መኾኑን ከንቲባው ተናግረዋል።

ደባርቅ ከተማ ውስጥ በጠንካራ የመረጃ መዋቅር፣ የኬላ ጥበቃ እና በሌሎች ስምሪቶች የአሸባሪውና ተስፋፊው ትህነግ ወራሪ ቡድን ተላላኪ ሰርጎ ገብ ዓላማውን እንዳያሳካ የሚያስችል እንቅስቃሴ እየተደረገ እንደሚገኝ የከተማው ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

የደባርቅ ከተማ ባለገጀራ ወጣቶች ፣ የሰሜን ጎንደር ጥቁር አንበሳ የቀድሞ ሰራዊት የበጎ አድራጎትና ልማት ማህበር አባላት ፣ አጠቃላይ የፀጥታ መዋቅሩ ፣ ወጣቶችና ማኅበረሰቡ የአካባቢውን ሰላም እያስጠበቀና የደጀንነት ተግባር እየፈፀመ ይገኛል።
 
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/matiosbirhanu
272 viewsMati Sheger, 04:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 07:02:49
የሸዋሮቢት ከተማ ከንቲባ ባልታወቁ ታጣቂዎች መገደላቸው ተሰማ!

የሸዋሮቢት ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ውብሸት አያሌው ከምሽቱ 3:00 ሰዓት አካባቢ ማንነታቸው ባልታወቀ የታጠቁ ሀይሎች ጥቃት ተፈፅሞበት ህይወቱ እንዳለፈ ከስፍራው ተሰምቷል።ተጨማሪ መረጃ ከመንግስትም ሆነ ከሌላ አካል የምናገኝ ከሆነ የምናቀርብ ይሆናል።
 
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/matiosbirhanu
287 viewsMati Sheger, 04:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 07:01:16
284 viewsMati Sheger, 04:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 07:01:15
የአበርገሌ ምሽጎች በትግራይ ለግላጋ ወጣቶች አስኬሬን ተሞልቷል።
አሁን ይሄ ሁሉ ወጣት አልቆ ምንድን ነው ትርፉ? በሎም የምትሉ የትግራይ ዲያስፖራዎች ምን ልትጠቀሙ ነው? እስቲ ወደ ቀልባችሁ ተመለሱ እና ለእነዚህ ልጆች እናት አባት አስቡ።
275 viewsMati Sheger, 04:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 08:07:29 ድራማ የማይሰለቸው ትህነግ ኬሚካል የጦር መሳርያ ተጠቅመው አጠቁኝ የሚል ድራማ እየሰራ እንደሆነ ታውቋል። በጦርነት ያስፈጃቸውን ወጣቶች አስከሬን ወስዶ ሊለበልብ ይሆናል። አሊያም ሌላ አማራጭ ይጠቀማል።

መሬት ላይ ያለውም የዲፕሎማሲውም ሲከብደው ድራማውንም የጦርነቱ አካል ማድረጉ የተለመደ ነው።

ለዚህ ጦርነት ከአደንዛዥ እፅ ጀምሮ ያልተጠቀመው ነገር የለም። ወጣቶቹ እንዲደፍሩለት አንገታቸው ላይም ከሱዳን የመጣ መተት ነው ብሎ ያስርላቸው ነበር። አሁን ደግሞ ሌላ ስልት ቀየሰ ማለት ነው።

ሲጨንቀው ገና በመብረቅ አስመቱኝ ይላል።

የቴሌግራም ቻናል:- T.me/matiosbirhanu
219 viewsMati Sheger, edited  05:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 19:22:05
የወልቃይት ሚስቶች እህቶችና እናቶች ባሎቻቸውንና ልጆቻቸውን ወደጦር ግንባር ሲልኩ።

የተገፋው ጀግናው ወገኔ ሰርጉ ነው ፍትሃዊ ጦር-ነት። ወደግንባር ለመሄድ እሽቅድድሙ እንደቀጠለ ነው።

እናት ኢትዮጵያ ዛሬም ልክእንደትናንቱ በጀግኖች ልጆቿ መስዋዕትነት ሉዓላዊነቷንና ነፃነቷን ጠብቃ ታፍራና ተከብራ ለዘለዓለም ትኖራለች

ድል ለእናት ኢትዮጵያ!!!

የቴሌግራም ቻናል:- T.me/matiosbirhanu
527 viewsMati Sheger, edited  16:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 19:16:35 ሰበር ዜና

ለወራት በሕወሓት ቁጥጥር ስር የነበረችው አበርገሌ በኢትዮጵያ ኃይሎች እጅ ገባች

የቴሌግራም ቻናል:- T.me/matiosbirhanu
520 viewsMati Sheger, 16:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 18:40:05
የሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ ህዝብ ለወገን ጦር የስንቅ ድጋፍ እያደረገ ነው፡፡

አማራን ለማጥፋትና ሀገር ለማፍረስ ጦርነት የጀመረውን አሸባሪና ወራሪ የትግራይ ቡድን በጦር ግንባር እያርበደበደ ላለው የወገን ጥምር ጦር ህዝቡ አስተመማኝ ደጀንነቱን በተግባር እሳዬ ይገኛል፡፡

ሀገር ተወረረ ድንበር ተደፈረ ሲባል ቀፎው እንደተነካ ንብ የሚተመው የአማራ ህዝብ ከየአቅጣጫው ለወገን ጦር ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እያደረገ ነው፡፡

ድጋፉ ተጠናክሮ መቀጠል የሚገባው ሲሆን አሸባሪው ቡድን የሁሉም ጠላትና ሀገር አፍራሽ በመሆኑ ሌሎች ክልሎችም ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንዲያደርጉ ማሳሰብ ያስፈልጋል። በዚህ ረገድ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ መስራት አለበት።

የቴሌግራም ቻናል:- T.me/matiosbirhanu
521 viewsMati Sheger, 15:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 18:39:50

473 viewsMati Sheger, 15:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 18:29:29 ወልዲያ፣ ሌላኛዋ ማርሽ ቀያሪ!

ትህነግ ባለፈው አመት የተለያዩ ቦታዎች ተመትቶ ተዳክሞ ነበር። በአፋር ተመትቷል። ደባርቅ ላይ ተመትቷል። ጋይንት ላይ ተመትቷል። ደብረሲና ላይ ተመትቷል። ጋሸና ላይ ተመትቷል። ወልዲያ ሌላኛዋ ማርሽ ቀያሪ ነች።

ትህነግ በመቶ ሺህ የሚቆጠር ሕዝብ አግተልትሎ እንደመጣ ነው መጀመርያ ቆቦ፣ ከዛም እስከ ወልዲያ ባለው መስመር በርካታ ኃይሉን ያጣው። ህወሃት ወልዲያን እይዛለሁ እንዳለበት ሁሉ ደብረታቦርና ደባርቅን ለማያዝ ጥሯል። ካራ ምሽግን ከዛም ደብረብርሃንን ለመያዝ ጥሯል። በእነዚህ ሁኔታዎች ያላደረገው ሙከራ አልነበረም። በአንዱ ሲመታ በሌላው ይሸሻል። በአንደኛው ተመለሰ ሲባል በሌላው ይመጣል። የሰሞኑ ወልዲያን ለመያዝ ያደረገው ትንቅንቅ ደብረታቦርን፣ ደባርቅንና ደብረብርሃንን ለመያዝ መጥቶ ተቀጥቅጦ ከተመለሰበት ጋር ተመሳሳይ ነው።


እንዲያውም የወልዲያው ረዥም ጊዜ አግኝቶ የሰለጠነ ነው። በጥምር ኃይሉና በደጀኑ ሕዝባችን መስዋዕትነት አላማው ተጨናግፏል። ይህ ግን በቂ አይደለም። በተደራጀ መልኩ ከተመታ ወደ ራያና ወልዲያ መስመር የመጣው ኀይል መመታቱ አሸባሪውን ቅስሙን ይሰብረዋል። ወልዲያን አላስነካም ያሉ ጀግኖቻችንን አግዘን ይህን አሸባሪ በሚገባ መቅጣት ከቻልን ኩራታችን ወልዲያ ሌላኛዋ የትግሉ ማርሽ ቀያሪ ትሆናለች። ሸዋ፣ ጋይንት፣ ጋሸና እና ወቅን ላይ የተመታው ትህነግ መግቢያ እንዳጣው ሁሉ አሁን ተረባርበን ወደ ወልዲያ አሰፍስፎ መጥቶ የነበረውን ማስቀረት ከቻልን የትህነግ ወሽመጥ ይቆረጣል።

መልካም አጋጣሚው ደግሞ የዋግሹም ልጆች ትህነግ የከፈተብንን ወረራ በሚገባ እየመከቱ፣ መልሶ ማጥቃት እያደረጉ በመሆኑ ወደ ራያና ወልዲያ የሄደው ኃይል ትንፋሽ እንዲያጥረው ይሆናል።

የቴሌግራም ቻናል:- T.me/matiosbirhanu
503 viewsMati Sheger, edited  15:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ