Get Mystery Box with random crypto!

ሰፋኒት ሚዲያ-Sefanit Media

የቴሌግራም ቻናል አርማ sefanit_media — ሰፋኒት ሚዲያ-Sefanit Media
የቴሌግራም ቻናል አርማ sefanit_media — ሰፋኒት ሚዲያ-Sefanit Media
የሰርጥ አድራሻ: @sefanit_media
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 696
የሰርጥ መግለጫ

በሃይማኖታችን ጸንተን በመንፈሳዊ ሕይወታችን እንበርታ!
Let us stand firm in our faith and be strong in our spiritual life.

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-04-24 11:46:31 “ንስሐ ልገባ እችላለሁ ወይም እገባለሁ ብለህ ኃጢአት አትሥራ፤ ይቅር ይለኛል በሚል ድፍረትም በኃጢአት አትውደቅ፤ አስታውስ ሞት አይዘገይሞ፡፡ እግዚአብሔርም አይሾፍበትም፡፡”
(ማር ይስሐቅ)
#ሰፋኒት
44 viewsErmiyas Belay, 08:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 23:47:44 Live stream finished (24 seconds)
20:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 23:47:20 Live stream started
20:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 12:40:44
ለጓደኞቻችሁ ሼር አድርጉላቸው እውነቱን ይወቁት።
Forward/share በማድረግ እውነትን ማወቅ ለሚፈልግ ሁሉ አድርሱ።
#ሰፋኒት
91 viewsErmiyas Belay, edited  09:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 12:22:48 "እንዳይታመሙ ፈርተው ከምግብ የሚከለከሉትን ሰዎች እደነቅባቸዋለሁ። እንዳንታመም ብለው ከምግብ ሲጠበቁና ሲከለከሉ ኵነኔን ፈርተው ወይም እንዳንኮነን ብለው ከኃጢአት አለመጠበቃቸውና አለመከልከላቸው ከቶ ስለምን ይሆን? እያልሁ እደነቃለሁ።"
(አንጋረ ፈላስፋ)

"ትንኝን የምታጠሩ ግመልን ግን የምትውጡ እናንተ ወዮላችሁ።" (ማቴ ፳፫)
#ሰፋኒት
91 viewsErmiyas Belay, 09:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 22:53:06 +  መልአኩ ነው +

       ሰዓቱ ሌሊት ነው ፤ እንደ አጋጣሚ ሆኖ በዚያ ሌሊት መላው የቤተሰባችን አባል አምሽቶ እየተጫወተ ነው፡፡ ከዚህ የቤተሰብ ስብስብ መካከል ሳይገኝ የቀረው አንድ በወኅኒ ቤት የታሰረ ወንድማችን ብቻ ነበር፡፡ ድንገት ግን የጊቢው በር በተደጋጋሚ ተንኳኳና ሁላችንም ጨዋታችንን አቋረጥን፡፡ በሌሊት ደግሞ የሚያንኳኳው ማን ነው ? አልን በልባችን

ሠራተኛችን ሮጣ ሔደች:: ወዲያው ግን በሩን ሳትከፍተው ተመልሳ እየሮጠች መጣች፡፡ በደስታ ሰክራ ‹‹የታሰረው ልጃችን በር ላይ ቆሟል!›› ብላ ተናገረች፡፡ "በድምፁ አወቅኩት!› እያለች ዘለለች፡፡ ከሁኔታዋ የተነሣ ‹አብደሻል እንዴ!?› አላት ቤተሰቡ ሁሉ፡፡

እስዋ ግን በእርግጠኝነት ተናገረች! በቀን የታሰረው ልጅ በሌሊት ተፈቶ መምጣቱ ፈጽሞ ሊታመንን የማይችል ነገር ነው፡፡ ቤተሰቡ ሁሉ የታሰረው ልጅ መጣ ብሎ አላመነም፡፡ ባይሆን የመንግሥት ወታደሮች የቀረነውን ሊወስዱን ይሆን? ማን ሊሆን ይችላል? ብሎ ተብሰለሰለ:: በመጨረሻም የሁሉም ግምት አንድ ነገር ላይ አረፈ:: ሁሉም ሰው በአንድ ድምፅ አንድ ቃል ተናገረ "መልአኩ ነው!"

  መልአኩ የሰው ስም አይደለም:: ቤተሰቡ የተስማማው "ደጅ የቆመው የታሰረው ልጃችን ሳይሆን እሱን ለመጠበቅ ከእግዚአብሔር የተሠጠው ጠባቂ መልአኩ ይሆናል›› ብሎ ነበር፡፡ የበሩ መንኳኳት አሁንም ስላልቆመ ቤተሰቡ ግር ብሎ ወጣና ተቻኩሎ በሩን ከፈተ፡፡ በደጅ የቆመው ግን እንደተባለው የታሰረው ልጅ ራሱ ነበር፡፡ ሁሉም ተደሰተ!!!

      ይህ ገጠመኝ በአሁን ዘመን የተፈጸመ ነው ብዬ ብናገር ማን ያምነኛል? እውነት በሌሊት የቤታችን በር ሲንኳኳ  መልአክ ነው ብለን እንገምታለን? ይህን የገመተው ቤተሰብ ምን ዓይነት ቤተሰብ ነው?

በሌሊት ሲንኳኳ በብዙዎቻችን አእምሮ ውስጥ መጀመሪያ የሚመጣው ጥርጣሬ ‹ሌባ ሊገባ ይሆን?› የሚል ስለሚሆን ዱላ ፍለጋ እናማትራለን፡፡ ወይ ደግሞ ሌሊቱ ወደ መንጋቱ እየተቃረበ ከሆነ ‹‹የምን መርዶ ሊያረዱኝ ይሆን? የቱ ዘመዴ ሞቶ ይሆን?› የሚል ጭንቀት ይፈጠራል፡፡

‹የሚያንኳኳው የእግዚአብሔርመልአክ ይሆናል› ብሎ የሚጠረጥር ሰው ግን በዚህ ዘመን ለማግኘት ያስቸግራል፡፡ እንዲህ ብሎ ግምቱን የሚናገር ሰው ከቤተሰባችንመካከል ቢገኝ እንኳን እንደ ዕብድ ልንቆጥረው እንችላለን፡፡ ታዲያ ይህን ገጠመኝ ከየት አመጣኸው ትሉኝ ከሆነ መልሱ ከመጽሐፍ ቅዱስ የሚል ነው፡፡

      በሐዋርያት ዘመን ሔሮድስ የተባለው ንጉሥ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስን ወኅኒ ቤት ውስጥ ወርውሮት ነበር፡፡ የቀሩት ደቀመዛሙርትና ክርስቲያኖች በዚያ ሰሞን ሲጸልዩ ከርመዋል፡፡ በአንድ ሌሊት በማርቆስ እናት ቤት ውስጥ ተሰብስበው አምሽተው ነበር፡፡ ድንገት የቤቱ በር ሲንኳኳ ሮዴ የምትባል የቤት ሠራተኛ ደጁን ልትከፍት ወጣች፡፡ ማነው ብላ ስትሰማ የቆመው እስረኛው ቅዱስ ጴጥሮስ መሆኑን በድምፁ አወቀች፡፡ ደስታ ግራ ሲያጋባት በሩን መክፈትን ረስታ ወደ ውስጥ ሮጠችና ጴጥሮስ መምጣቱን ተናገረች፡፡ እነርሱ ግን አላመኑአትም፡፡ ጤንነቷን ተጠራጥረው ‹አብደሻል› አሏት፡፡ እርግጠኛ ሆና ተናገረች፡፡ እነርሱ ግን መልሰው ‹‹የቆመው ጴጥሮስ ሳይሆን መልአኩ ነው፡፡›› አሉ፡፡ ይደንቃል የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች እንዲህ በር ሲንኳኳ ‹መልአክ ነው› ብለው የሚገምቱ መንፈሳዊያን ነበሩ፡፡ (ሐዋ. 12፡12-15)

ክርስትናን ከመላእክት ውጪ አይታሰብም:: ከመጽሐፍ ቅዱስም እንደ ትንቢተ ሐጌና መጽሐፈ አስቴር ያሉ ጥቂት መጻሕፍት በቀር ስለ መላእክት የማይናገር መጽሐፍ የለበትም:: ክርስትና የጀመረው በገብርኤል ብሥራት ነው:: ልደቱ በመላእክት የታጀበ ነው:: ስቅለቱ ትንሣኤውም ከመላእክት ጋር ነው:: የጌታ ምጽአቱም በመላእክት የታጀበ ነው::
     

ቅዱሳንመላእክት እኛ የሰው ልጆች ከመፈጠራችን ቀድመው የተፈጠሩ ታላቅ ወንድሞቻችን ናቸው፡፡ እንዲያውም ምድርና የሰው ልጅ ሲፈጠር ደስ እያላቸው ‹‹እልል›› ይሉ ነበር፡፡ (ኢዮ. 38፡6) ቅዱሳን መላእክትን እግዚአብሔር ለእንዳንዳችን ጠባቂዎች አድርጎ ሠጥቶናል፡፡ መላእክት ለሰው ባልተናነሰ ቁጥር ምድር ላይ አሉ:: እነርሱን ለማየት ግን ቅድስና ይጠይቃል::

ከክርስቶስ እግር ሥር ቁጭ ብለው የተማሩት ቅዱሳን ሐዋርያት ስለ መላእክት ጠባቂነት ጋር ይህን ያህል እምነት ከነበራቸው እኛም የመላእክቱን ጠባቂነት ማመን ለዚህ ዘመን ክርስቲያኖችም ምን ያህል ይገባን ይሆን? ቅዱሳን መላእክት በክርስትና ሕይወት ለሚኖርሰው ሁሉ የመላእክት ረዳትነት እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ ለሁሉ ብርታት የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን በሥጋው ወራት በተያዘባት ምሽት ሲጸልይ ‹‹ከሰማይም መጥቶ የሚያበረታው መልአክ ታየው›› ተብሎ ተጽፏል፡፡ (ሉቃ. 22፡43) ይህም ቀርበው አገለገሉት‹ለከ ኃይል› እያሉ አመሰገኑት ማለት ሲሆን ለእኛም የመላእክት ርዳታ አያስፈልገኝም እንዳንል የሚያስተምረን ነው፡፡

ቅዱሳን መላእክት በምድር የሚሆነውን ያውቃሉ:: (2 ሳሙ 14:20) በበደላችን ስንጸጸት "ኃጢአትህ ተሠረየችልህ" ይላሉ (ኢሳ 6:7) በክፋታችን ጸንተን ከቀጠልን ደግሞ "ይቅር አይሉም" (ዘጸ 23:20)
ስለእኛ በእግዚአብሔር ፊት ቆመው "የማትምራቸው እስከ መቼ ነው?" ብለው ያማልዳሉ:: (ዘካ 1:12)

አንዳንድ ሰዎች መላእክትን ለረዳትነት ስንጠራ ሲሰሙ እነርሱ በምን ያውቃሉ በሁሉ ቦታ የሉም እኮ ሊሉን ይሞክራሉ:: ሰይጣን "ፈተነኝ" ስንል ግን "እሱ በሁሉ ቦታ የለም ምን ያውቃል አይሉም:: እኛ ግን መላእክት በሁሉ ባይሞሉም ለትንሽዋ ፕላኔት ምድር ግን እንደማያንሱና አንዱ መልአክ ብቻ ለምድር እንደሚበቃ እናምናለን:: (ራእ 18:1)
ለመላእክት ስንዘምር የሚቃወሙ ሰዎች "ጠላቴ ሆይ" ብለው ስለ ሰይጣን ክፉነት እያነሱ ብዙ መዝሙር ሲዘምሩ ስንሰማ ግራ እንጋባለን::

እኛ ግን በመላእክቱ ረዳትነትና ምልጃ እናምናለን:: ባለንበት ዘመን በየሆስፒታሉ በዓለም ሁሉ በበሽታ የሚሠቃየው ብዙ ነው::  በሕመም ለሚሠቃየው ሁሉ

"መልአክ ቢገኝለት እየራራለት [ለእግዚአብሔር] ፡— ቤዛ አግኝቻለሁና ወደ ጕድጓድ እንዳይወርድ አድነው፡ ቢለው፥ ሥጋው እንደ ሕፃን ሥጋ ይለመልማል፤ ወደ ጕብዝናውም ዘመን ይመለሳል" ኢዮ 33:23-25

(ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ)

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ዘንድ ጸልዩ! ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like እና Share ያድርጉ።
#ሰፋኒት
103 viewsErmiyas Belay, 19:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 21:25:42 ++የቅዱሳን አማላጅነት ++
የቅዱሳን አማላጅነት ለምን አሰፈለገ ?
ቅዱሳን ያማልዳሉ ማለት ሰው ጸሎት ያቆማልማለትነውን ?

በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
90 viewsErmiyas Belay, edited  18:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 08:11:12 «ማዕዶት»

በዕለተ ትንሣኤ ማግስት የሚገኘው ሰኞ፦ «ማዕዶት» ተብሎ ይጠራል። «መሻገሪያ» ማለት ነው። ይኸውም ቤዛችን ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት እንደ አሻገረን ያመላክታል።

#ሰፋኒት #Sefanit
join @ErmiyasBelayEB
151 viewsErmiyas Belay, 05:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 20:46:25 የጾሙና የሕማማቱ ያልነበሩ ሰዎች ትንሣኤው ላይ "አለን አለን" ሲሉ ሳይ...
አይ የሰው ነገር ደስታን ማን ይጠላል ብላችሁ ነው። ክርስትና የተጻፈውን ሁሉ እንጂ መርጦ ማመን አይደለም።

#ሰፋኒት #Sefanit
Join @ErmiyasBelayEB
344 viewsErmiyas Belay, edited  17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 11:59:43 #ትንሣኤ በወልቂጤ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን

እንኳን አደረሳችሁ።
አማን በአማን(፪) ተንሥአ እምነ ሙታን (፪)
ትንሣኤከ ለእለ አመነ
ብርሃነከ ፈኑ ዲቤነ

#ሰፋኒት
#Sefanit



137 viewsErmiyas Belay, 08:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ