2022-03-27 09:12:26
አልኖረችም...!
"ኧረ ይቅርብኝ" እያለችኝ ነበር ያስጀመርኳት። በኔ መንገድ ያመጣት ምናልባት ብቸኝነቴን ተመልክቶ ይሆናል የሚል እሳቤ ነበረኝ። ደስ የምትል ልጅ ናት።
"ሮዚ ነይ እዚ ምሳ በልተን እንሄዳለን" ፊት ለፊታችን ካለው ትንሽዬ፣ ነገር ግን የሰፈሩ ስፔሻል ምግብ ቤት ዘው ብዬ ገባሁ። ውስጥ ያሉትን ሰላም ብዬ ላስተዋውቃት ስዞር በር ላይ እንደተገተረች ነው። በመቆጣት 'ምን ሆንሽ' አይነት አስተያየት አየኋት።
"ለመግባት ፈራሁ፤ እነሱ ሲወጡ እንብላ እ አይሻልም?" በልምምጥ እያየች ጠየቀችኝ። መልስ አልመለስኩላትም ጎትቼ አስገባኋት።
፧
"ኧረ አልችልም ደሞ አልጫወትም እንዴ ሰው እያየን?" የዋህነቷ ገረመኝ። "የገጠር ልጅ ስለሆንሽ ነው እዚ እኮ ሁሏም ሴት ፑል ትጫወታለች" የፑሉን እንጨት አስጨበጥኳት...
፡
ከመንገድ ድንጋይ ፈላጭ(ፓስቲ) ገዝቼ አንድ ለኔ አንድ ለሷ ሰጠኋት። ተቀብላኝ በእጇ ስትይዘው ብዪ አይነት ምልክት እየበላሁ አሳየኋት
"እህ መንገድ ላይ ሰው እያየን?"
"ሮዚ የሚያይሽ የለም ምን ሁኚ ምን አድርጊ ማንም ቼክ የሚያደርግሽ የለም ፤ ደሞ ቢያይሽስ ምን ጨነቀሽ?" ከራሷ የምትደበቅ ያህል እየተርበተበተች ገመጠችው።
'ኧረ ይቅርብኝ' ያለችው ነገር ብዛቱ ዘርዝሬ አልጨርሰውም.... ለብዙ ነገር ድንግል ነበረች።
"ኧረ ይሄ ነገር ይቅርብኝ ሞክሬውም አላውቅምኮ" ራሷን እየተጠራጠረች ነበር። ላስረዳት ብሞክር እንቢ እንደምትል ስለገባኝ በድፍረት ሲጋራውን ከከንፈሯ አያይዤ እንድትስበው አደረኳት። ከሁለት ስበት ቡኋላ በጭስ ውስጥ ፈገግ አለችልኝ። (እንዲህ ቆንጆ ናት እንዴ!?)
፡
"ርብቃ አቦ በናትሽ ነይ እንውጣ" ንዴቷ ድምጿ ውስጥ ያስታውቃል። ለመጀመሪያ ጊዜ ትንሽዬዋ ልጅ አዛኝ እሺ ብዬ ተከተልኳት። ሸገርን ከገጠር እየተመላለሰች እንዳየቻት እንጂ አንደኛዋን ለመኖር ስትመጣ የመጀመሪያዋ እንደሆነ ነግራኛለች። ከአክስቷ ቤት ከኔጋ ስራ ትሰሪያለሽ ብዬ ሳስወጣት ፍርሃት እንጂ ንዴት አልነበራትም። ወንዶች በተሰበሰቡበት ቦታ ይዣት ስሄድ ልምምጥ እንጂ ቆራጥነትን ከፊቷ አላነበብኩም። ሲጋራ እንድታጨስ ስገፋፋት 'አይ' አይነት ልምምጥ እንጂ 'አይሆንም' አይነት ቆራጥነት አላሳየችኝም (ምናልባት ሴት ስለሆንኩ አምናኝ ይሆን!?)
"ምን ሆነሽ ነው" ንዴቷን እያየሁ ጠየኳት
"ከዚ ቡኋላ እዚ መምጣት አልፈልግም" አለች። ግራ ገብቶኝ አየኋት። ለደቂቃዎች ያለማቋረጥ ሳያት
"ይቅርታ ከማንም ጋር መተኛት አልፈልግም" ይሄኛው ድምጿ ግን ትንሽዬ ተስፋ ነበረው። ዛሬ ከማንም ሸሽታ ነገ ማንን እንደምትሆን ሳስበው በጣም ኢምንት ተስፋ በሷ ላይ ሽው አለብኝ። ከዚህ በላይ እኔን እንድትመስል ማድረግ የነበረብኝ ሀጥያት በእጥፉ ደጋግሞ ማባዛት መሰለኝ።
ይቀጥላል
ፊያሜታ
@YETBEB_BET
871 viewsፊያሚ , 06:12