Get Mystery Box with random crypto!

Christ Gospel

የቴሌግራም ቻናል አርማ pure_christ_gospel — Christ Gospel C
የቴሌግራም ቻናል አርማ pure_christ_gospel — Christ Gospel
የሰርጥ አድራሻ: @pure_christ_gospel
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.19K
የሰርጥ መግለጫ

ሮሜ 1 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³ ወንጌሉም ስለ ልጁ፣ በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ሆነ፣
⁴ በቅድስና መንፈስ ደግሞ ከሙታን በመነሣቱ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑ በኀይል ስለ ተገለጠው ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-04-17 05:53:56 ይሄን ቪዲዮ በእንባ ሆኜ ካየው በኋላ ክርስቶስን ይበልጥ ወደድኩት
"ዘ ፓሺን ኦፍ ዘ ክራይስት"
የተሰኘው ክርስቶስ ለእኛ የከፈለውን ዋጋ የሚያሳይ ፊልም

አውርዳችሁ ተመልከቱ
453 viewsEphraim Grace, 02:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 05:52:02
#ሰባት_የኢየሱስ_እኔ_ነኝ'ዎች #በዮሐንስ_ወንጌል
1. የህይወት እንጀራ እኔ_ነኝ (ዮሐ 6፡35)
2. እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ (ዮሐ. 8፡12)
3. የበጎች በር እኔ ነኝ (ዮሐ 10፡7)
4. መልካም እረኛ እኔ ነኝ (ዮሐ 10፡11)
5. ትንሳኤ እና ሕይወት እኔ ነኝ (ዮሐ 11፡25)
6. እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ (ዮሐ 14፡6)
7. እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ (ዮሐ 15፡1)

ሰው ሆነ  "እኔ ነኝ" ማለት አይቻልም። ምክንያቱም ሰው ራሱን ሆኖ መቆየት አይችልም። እግዚአብሔር ስለራሱ ለሙሴ ሲናገር እንዲህ አለ:- ያለና የሚኖር ወደ እናንተ ላከኝ ትላለህ አለው (ዘጸ 3:14)። በራሱ ተማምኖ "እኔ ነኝ" ማለት የሚችል እግዚአብሔር ብቻ ነው።

ሁሉን ቻይ አምላክ እኔ ነኝ (ዘፍ 35:11)
ከጥንት ጀምሮ እኔ ነኝ ከእጄም የሚያመልጥ የለም፤ እሠራለሁ፥ የሚከለክልስ ማን ነው? (ኢሳ. 43:13)
በጽድቅ የምናገር ለማዳንም የምበረታ እኔ ነኝ። (ኢሳ 63:1)

Join and subscribers
https://t.me/Pure_Christ_Gospel
980 viewsEphraim Grace, 02:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 13:03:40 …..ኢየሱስ ተነስቷል!!!
የኢየሱስ ትንሣኤ ማለት ከተሰቀለ ከሞተ በኋላ ከሙታን ተነስቷል ማለት ነው።  ይህ ክስተት የክርስትና እምነት የማዕዘን ድንጋይ ሲሆን ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ እና ሞትን ድል ለማድረግ የሚያስችል ኃይል እንዳለው ያመለክታል።  በዓለም ዙሪያ ባሉ ክርስቲያኖች የተስፋ እና የአዲስ ሕይወት ምልክት ሆኖ ይከበራል።  ትንሣኤ ደግሞ በብሉይ ኪዳን የተነገሩትን ትንቢቶች ፍጻሜያቸውን አግኝተው ኢየሱስ እኔ ነኝ ያለው መሆኑን አረጋግጧል።  በአጠቃላይ፣ የኢየሱስ ትንሣኤ በዛሬው ጊዜ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት የሚነካ የታሪክ ወሳኝ ወቅት ነው።
መልካም በአል ይሁንላችሁ!!!

ሬቨረንድ ተዘራ ያሬድ እና ቤተሰቡ

Join and subscribers
https://t.me/+RadfKjJvYdaWhzed
742 viewsEphraim Grace, 10:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 13:24:58 Looking at the thief at Jesus right hand on the cross would debunk many people theologies. No confession of Sin, No water baptism, no restitution and yet Jesus promised him Paradise.

Salvation is only by faith in Jesus!

-Apostle Beng Grace


በመስቀል ላይ በኢየሱስ ቀኝ እጅ ያለውን ሌባ መመልከቱ የብዙ ሰዎችን ሥነ-መለኮት ያጠፋል። የኃጢአት መናዘዝ የለም፣ የውሃ ጥምቀት የለም፣ ምንም ዓይነት ማካካሻ የለም፣ ሆኖም ኢየሱስ ገነትን ተስፋ ሰጠው።

መዳን በኢየሱስ በማመን ብቻ ነው!

የመረጃ ምንጭ Mike Grace Facebook page የተወሰደ መልዕክት ነው።


Join and subscribers
https://t.me/+t5ztTrZ_iU9kNTVk
1.0K viewsEphraim Grace, edited  10:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 06:32:15
“ተግሣጽን የሚወድድ እውቀትን ይወድዳል፤ ምክርን የሚጠላ ግን ደንቆሮ ነው።”
— ምሳሌ 12፥1
የሰው አኗኗሩም ይሁን አገልግሎቱ የአስተሳሰቡ ውጤት ነው።አስተሳሰብ ደግሞ በሰው ዕውቀት ልክ ይወሰናል፤ስለሆነም አንድ ዳግም የተወለደ ሰው እንደ እግዚአብሔር ቃል ለመኖርም ሆነ ለማገልገል በእግዚአብሔር ቃል ዕውቀት ዐዕምሮውን ማደስ ይጠበቅበታል።
አብሮ የሚኖር የአማኝ ጠላት አለማወቅ(ignorance) እንጂ ሴይጣን አይደለም።
የእግዚአብሔር ቃል ራሱ ለህዝብ መጥፋት(መረን መለቀቅ)ምክንያት አድርጎ ያስቀመጠው አለማወቅን እንጂ ሴይጣንን አይደለም።
“ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል።”
— ሆሴዕ 4፥6
የዚህ መልዕክት የጸሐፊ Milka Yonatan

Join and subscribers
https://t.me/+RadfKjJvYdaWhzed
1.6K viewsEphraim Grace, 03:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 05:41:31
"ሁሉም ሰው በህይወት ውስጥ በአስቸጋሪ ጊዜያት ውስጥ ያልፋል፣ ነገር ግን እግዚአብሔር ከታመንን ከምንም ነገር መልካም ያደርጋል።"

ጆይስ ሜየር


http://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD
1.3K viewsEphraim Grace, edited  02:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 18:38:20
የልብሱ ትርጉም

ኤፌሶን 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ ስለዚህ በክፉው ቀን ለመቃወም፥ ሁሉንም ፈጽማችሁ ለመቆም እንድትችሉ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ አንሡ።
¹⁴-¹⁵ እንግዲህ ወገባችሁን በእውነት ታጥቃችሁ፥ የጽድቅንም ጥሩር ለብሳችሁ፥ በሰላም ወንጌልም በመዘጋጀት እግሮቻችሁ ተጫምተው ቁሙ፤
¹⁶ በሁሉም ላይ ጨምራችሁ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ አንሡ፤
¹⁷ የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው።

http://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD
1.5K viewsEphraim Grace, edited  15:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 11:57:16
እግዚአብሔር የፍርሀት መድኃኒት ሰጥቶናል እናም እምነት ነው።

ጆይስ ሜየር

God has given us an antidote to fear and that is faith.

Joyce Meyer


http://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD
985 viewsEphraim Grace, edited  08:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-21 04:01:55
በሀላባ ምድር የምትገኙ ሙስሊም ወንድሞቼ እና እህቶቼ በሙሉ የምስራች ወንጌል አለኝ።

ሮሜ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ ነገር ግን ምን ይላል? በአፍህ በልብህም ሆኖ ቃሉ ቀርቦልሃል፤ ይህም የምንሰብከው የእምነት ቃል ነው።
⁹ ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤
¹⁰ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።
¹¹ መጽሐፍ፦ በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላልና።
¹² በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤
¹³ የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።

የወንጌል አማኞች በሙሉ ይህ መልዕክት ለብዙዎች Share አድርጎ።


http://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD
1.7K viewsEphraim Grace, edited  01:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 07:00:23
#የፀጋ_ቃል "ወደ ጽዮን ተራራና ወደ ሕያው እግዚአብሔር ከተማ ደርሳችኋል፥ ወደ ሰማያዊቱም ኢየሩሳሌም፥ በደስታም ወደ ተሰበሰቡት ወደ አእላፋት መላእክት፥ በሰማያትም ወደ ተጻፉ ወደ በኵራት ማኅበር፥ የሁሉም ዳኛ ወደሚሆን ወደ እግዚአብሔር፥ ፍጹማንም ወደ ሆኑት #ወደ_ጻድቃን_መንፈሶች፥ የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥ ከአቤልም ደም ይልቅ የሚሻለውን ወደሚናገር ወደ መርጨት ደም ደርሳችኋል።" ዕብራውያን. 12፥22


http://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD
772 viewsEphraim Grace, 04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ