Get Mystery Box with random crypto!

Christ Gospel

የቴሌግራም ቻናል አርማ pure_christ_gospel — Christ Gospel C
የቴሌግራም ቻናል አርማ pure_christ_gospel — Christ Gospel
የሰርጥ አድራሻ: @pure_christ_gospel
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.19K
የሰርጥ መግለጫ

ሮሜ 1 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³ ወንጌሉም ስለ ልጁ፣ በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ሆነ፣
⁴ በቅድስና መንፈስ ደግሞ ከሙታን በመነሣቱ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑ በኀይል ስለ ተገለጠው ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-03-17 19:09:04
.....መስቀሉን ታግሶ!

በአውሮፕላን እየበረርን ሳለን የሆነ አስቸካይ ነገር ቢገጥመን "ወራጅ አለ!" አውርደኝ አንልም፤ ነገር ግን ነገሮችን ዋጥ አርገን መዳረሻችን እስክንደርስ ወይም አውሮፕላኑ መሬት ላይ እስኪያርፍ ድረስ እንታገሳለን።

"እነሆ፥ በትዕግሥት የጸኑትን ብፁዓን እንላቸዋለን" ያዕቆብ 5: 13

#ትዕግስት_የጸጋ_ስጦታ_ሳይሆን_የምናልፍባቸው_የሕይወት_ትግል_የጽናት_ውጤት_ነው!!

አንድ ሰው ወደ አቀደው ቦታ ለመድረስ አስቦ መሄድ ሲጀምር የሚገጥሙትን ፈታኝ ነገሮች በትዕግስት ማሳለፍ ካልቻለ ብዙ ነገሮችን ያጣል ።

“አብርሃምም በትዕግሥት ከጠበቀ በኋላ የተሰጠውን ተስፋ አገኘ።”
— ዕብራውያን 6፥15 (አዲሱ መ.ት)

በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ያሉ አባቶች ወደ ፍፃሜያቸው የደረሱት ስለ አመኑ ብቻ ሳይሆን ስለታገሱም ጭምር ነው። ጌታችን ኢየሱስም በፊቱ ያለውን ደስታ በእምነት በመመልከት የመስቀልን መከራ ታግሶ በማለፍ ሄዷል። መስቀልን ከመታገስ ውጭ ምንም ማድረግ አይቻልም።

“የእምነታችን ጀማሪና ፍጹም አድራጊ የሆነውን ኢየሱስን እንመልከት፤ እርሱ በፊቱ ስላለው ደስታ መስቀሉን ታግሦ፣ የመስቀሉንም ውርደት ንቆ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአል።”
— ዕብራውያን 12፥2 (አዲሱ መ.ት)

የትዕግስት ጉዞ ለጊዜው መራራ ቢሆንም ፍሬው ግን እጅግ ጣፋጭ ነውና እንታገስ።

«ምክንያቱም የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንደሚያስገኝ ታውቃላችሁ። ምንም የማይጐድላችሁ ፍጹማንና ምሉኣን እንድትሆኑ ትዕግሥት ሥራውን ይፈጽም።»
ያዕቆብ 1፥3-4

መልካም ቀን
ሬቨረንድ ተዘራ ያሬድ

Join and subscribers
https://t.me/+RadfKjJvYdaWhzed
1.2K viewsEphraim Grace, edited  16:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 16:43:51
"ጸሎትህ የተወሳሰበ እንደሆነ ከተሰማህ ወይም ለመጸለይ አስቸጋሪ እንደሆነ ከተሰማህ ጸሎቶችን ለማቅለል ጊዜው አሁን ነው። መጸለይ መናገር ነው እና በቀላሉ ከእግዚአብሔር ጋር ለመነጋገር ጊዜው አሁን ነው።

" ጆይስ ሜየር"

Join and subscribers
https://t.me/+RadfKjJvYdaWhzed
1.1K viewsEphraim Grace, edited  13:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 06:54:38
Evangelist Dr.billy graham Amazing message.

Join and subscribers
https://t.me/+RadfKjJvYdaWhzed
1.4K viewsRussia, edited  03:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 17:23:27
ክፍል ሁለት

የመጽሐፍ ቅዱስ ትኩረት እና ዋና ማዕከሉ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

“በእነርሱ የዘላለም ሕይወትን የምታገኙ እየመሰላችሁ፣ መጻሕፍትን ትመረምራላችሁ፤ እነዚሁ መጻሕፍት ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው፤”
  — ዮሐንስ 5፥39 (አዲሱ መ.ት)

መጽሐፍ ቅዱስ ዋንኛው ማእከሉ እና ትኩረቱ ኢየሱስ ክርስቶስን የሚገለጥ እና የሚመሰክር ነው።

መጽሐፍ ቅዱስ ከዘፍጥረት አንስቶ እስከ  ዮሐንስ ራዕይ ድረስ የሚመሰክረው በአንድ ወርቃማ ገመድ የተገመደው ስለ ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

ኢየሱስ ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን ዘመን እንደ ተስፋ ቃል ሲነገር የነበረ እርሱ መሲሑ ይመጣል ተብሎ የተነገረለት እና የተመሰከረለት ብቸኛው የእግዚአብሔር ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ በብሉይ ኪዳን ዘመን የተነገረለት ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ በአካል የተገለጠ የእግዚአብሔር ልጅ ነው።

መጽሐፍ ቅዱስ ዋንኛው ትኩረቱ እና መልዕክቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

“እርሱም፣ “ከእናንተ ጋር በነበርሁበት ጊዜ፣ ‘በሙሴ ሕግ፣ በነቢያትና በመዝሙር መጻሕፍት ስለ እኔ የተጻፈው ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ይገባል’ ብዬ የነገርኋችሁ ቃሌ ይህ ነው” አላቸው።”
  — ሉቃስ 24፥44 (አዲሱ መ.ት)

ኢየሱስ ክርስቶስ ከደቀመዛሙርቱ ጋር በነበረ ጊዜ  የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ሁሉ ስለ እርሱ እንደሚናገር ለደቀመዛሙርቱ ተረከላቸው።

የመጽሐፍ ቅዱስ ዋንኛው ትኩረት የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።


ወንድም ኤፍሬም ገ/ኢየሱስ

https://t.me/The_Grace_Gospel_Channel
745 viewsEphraim Grace, 14:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 10:07:31
የደስታ ጥግ እና ሙላት ያለው በእግዚአብሔር መገኘት ውስጥ ነው!!!

ፓስተር ተስፋሁን (ዶ/ር)

Join and subscribers
https://t.me/+RadfKjJvYdaWhzed
772 viewsRuth Dawit, edited  07:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 12:03:33
በእምነት እና በጸጋ ድናችኋል

ኤፌሶን 2 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ በእምነት፣ በጸጋ ድናችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤
⁹ ማንም እንዳይመካ በሥራ አይደለም፤
¹⁰ ምክንያቱም፣ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀልንን መልካም ሥራ እንድንሠራ በክርስቶስ ኢየሱስ የተፈጠርን የእግዚአብሔር እጅ ሥራዎች ነን።

ጸጋ እና እምነት ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠ ስጦታ ነው፤ በሰው ዘንድ ያልተገኘ ሙሉ በሙሉ ከእግዚአብሔር ዘንድ የሆነ።

“በበደላችን ሙታን ሆነን ሳለ፣ በክርስቶስ ሕያዋን አደረገን፤ የዳናችሁት በጸጋ ነው።”
— ኤፌሶን 2፥5 (አዲሱ መ.ት)

በሥራ የተገኘ ነገር ከእግዚአብሔር ዘንድ አይደለም፤ ማንም እንዳይመካ በራሱ ስራ ሳይሆን እግዚአብሔር በልጁ ስራ መመካት ነው።

እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ በተሰራው ስራ እኛ ሁላችንም በጸጋው ድነናል።

በጸጋ የዳነ አማኝ መልካሙን ሥራ እንዲሠራ በክርስቶስ ኢየሱስ እንደተፈጠረ ይናገራል።


ወንድም ኤፍሬም ገብረኢየሱስ

Join and subscribers
https://t.me/+RadfKjJvYdaWhzed
1.0K viewsRussia, 09:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 11:27:33
ሊዲያ ጥፋቷ ምንድነው?

ሊዲያ የምትኖረው ሀላባ ነው። ተማሪ ነች። እንደማንኛውም ተማሪ በትምህርት ቤቷ ተገኘች። እንደ አጋጣሚ ሆኖ አጠገብዋ ቆማ የነበረች አንዲት ሙስሊም ተማሪ መሬት ላይ ወደቀች። ይህች ልጅ በወደቀችበት ሆና "ኢየሱስ ጌታ ነው" አለች። (ልብ በሉ "ኢየሱስ ጌታ ነው!" ያለችው ሊዲያ አይደለችም የወደቀችው ተማሪ ነች) በቃ! የሆነው ይሄ ይኸው ነው።

የሚያስገርመው ግን ይህ ሁኔታ ከተከሰተ በኋላ የወደቀችው ተማሪ ልጅ ቤተሰቦች ባቀረቡት ክስ ሊዲያ በፖሊስ ታሰረች። ቆይ የሊዲያ ጥፋት ምንድነው? ገፍትራ አልጣለቻት፤ በግድ አስፈራርታ "ኢየሱስ ጌታ ነው! በይ!" አላለቻት። ሙስሊሟ ልጅ የወደቀችው ራሷ! "ኢየሱስ ጌታ ነው" ያለችው ራሷ! ታዲያ ለምንድነው ሊዲያ የታሰረችው?

እንደሚሰማው ከሆነ የወደቀችው ተማሪ ቤተሰቦች በሊዲያ ላይ አቀረቡባት የተባለው ክስ "አስደግማባት ኢየሱስ ጌታ ነው እንድትል አደረገቻት" የሚል ነው። አሰቂኝም አሳዛኝም ነው። ይህንን ክስ የሚሰማ ሁሉ የሚያፍር ይመስለኛል።

እስኪ ፍረዱ፤ በትምህርት ገበታዋ ላይ ከመገኘቷ ውጪ የሊዲያ ጥፋቷ ምንድነው?

Tewodros Techan ቴዎድሮስ ተጫን

Join and subscribers
https://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD
1.5K viewsEphraim Grace, edited  08:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 17:00:24 #እዉነተኛ_ታሪክ

በሶሪያ ጦርነት ጊዜ ነዉ፥ በምድረ በዳ የተገኘዉ እዉነተኛ ወዳጅ።

በሃገረ ሶሪያ አንድ ሙስሊም ሴት ከባሏ እና ከ አራት ልጇቿ ጋር የቤታቸዉ በረንዳ ላይ ቁርስ ይበላሉ፤ በድንገትም እየተጫወቱ ምግባቸዉን እየተመገቡ ሳሉ:- ወደ አይር መንገዱ የተወረወረ ሚሳኤል የእነሱ ቤት ላይ ያርፋል ሚሳኤሉም በወደቀ ቅጽበት የዛች ሴት [ስሟን ካልተሳሳትኩ አሊማ] ሁለት ወንድ ልጇቿ እና ባለቤቷ ይሞታሉ፣ አሊማ ላይ ከባድ ጉዳት በእግሯ ላይ ሲደርስ ሁለት ሴቶች ልጆቿ መጠነኛ ጉዳት ያገኛቸዋል።

ለተወሰነ ቀን ሕክምና ካደረገች በሗላ አሊማ ያላትን ንብረት ሁሉ ትሸጥና እጇ ላይ ያለዉን ሁሉ ብር ድንበር ለሚያሻግር ደላላ ሰጥታ ወደ ሌላ ሃገር ከባህር ማዶ ለመሰደድ ትሄዳለች፤ ጉዞዉ ለሊት ስልነበር በጣም የሚያሳዝነዉ አሊማ ከደረሰባት ጉዳት የተነሳ በክራንች ስለምትሄድ ያዉም ሁለት ሕጻናት ሴቶች ልጆች ይዛ እርመጃዉ በጣም የተገታ ነበር። በዚህ ጊዜ ከፊት ከፊት የሚመራቸዉ ደላላ ወደ አሊማ ይመጣና በጣም ተቆጥቶ:- [ስሚ አንቺ ሴትዮ ለሊቱ ከነጋ ሰዎቹ ደርሰዉ ይገድሉናል አንቺ በደንብ አልራመድ ብለሽ እኛን ልታሲዥን ነዉ የራስሽ ጉዳይ] ብሎ ክራንቹን በእግሩ መጥቶ ይጥልባታል አንዴ ብሩን ሰልተቀበለ የአልሚና ጉዳይ ትቶ በሩጫ ያመልጣል። አሊማ ከሁለት ሕጻናት ልጆቿ ጋር በለሊት በጫካ ዉስጥ ወድቃ ታለቅሳለች። እያለቀሰችም እያለ በድንገት ሰዉነቱ የፈረጠመ ረጅም ጎልማሳ ሰዉ ይመጣና:- [አይዞሽ በሶሪየሎ እንባዋን በእጁ ያብሳል፣ በእጁም ደግፎ ያስነሳትና በአንድ እጁ እሷን በሌላኛዉ እጁ ሁለት ሴት ልጆቿን ይዞ በጣም በፍጥነት እየተራመደ ከነበሩበት አገር ያወጣቸዋል]፤ የሚፈለግቡት ሃገር ካደረሳቸዉ በሗላ [ሰለም ሁኑ] ብሎ ሊሄድ ሲል አሊማ [አንተ መልካም ሰዉ አላህ ዉለታህን ይክፈልህ ስምህንና አድራሽን ንገረኝ ደዉዬ ላገኝህ እፈልጋለሁ ትለዋለች]
እሱም:- ስምሽን አዉቀዋለሁ አሊማ ነዉ የሁለት ልጆቿንም ስም ይጠራና አድራሻዬን በቅርቡ ታዉቂዋለሽ ባለሽበት ቦታ እመጠላሁ እስከዛዉ ግን ስሜ አልመሲ ኢሳ ነዉ ብሏት ተሰወረ።

ከቀናት በሗላ አሊማ የሄደችበት ሃገር ያሉ ባልና ሚስት የወንጌል አገልጋዮች ጌታ ስለ አሊማ ይነግራቸዋል፤ ከዛም ሄደዉ ወንጌል እንዲሰብኩላት አዘዛቸዉ። እነሱም ጌታን ታዘዉ ወደ አሊማ ቤት ሄዱ በሯን ሲንኳኩም አሊማም በሯን ከፍታ ተቀበለቻቸዉ፣ መልዕክቱንም ይነግሯት ጀመር:- [99 በጉቹን ትቶ አንዷን የጠፋችዉን በግ ሊፈልግ ስለሄደዉ ሲያገኛትም ተሸክሟት በደስታ ስለተመለሰዉ እረኛ ገና እያወሩላት እያሉ አሊማ በመሃል አቋረገጠቻቸዉ እና ጮህች ይሄ የእኔ ታሪክ ነዉ ከቀናት በፊት ጠፍቼ ወድቄ በሞት አፋፍ ላይ ተሸክሞ አተረፈኝ በፈርጣማ እጆቹ የታደገኝ አልመሲ ኢሳ ነዉ] አለች በጉልበቷ ተንበረከከች፥ አድራሻዉ የጠፋባትን ደጉን እረኛ አልመሲ ኢሳ እዉነተኛዉን አዳኙን በቃሉ በኩል አገኘችዉ!

የኢየሱስ አድራሻዉ ቃሉ ዉስጥ ነዉ፤ አልመሲ ኢሳ ያድናል!

#ምንጭ:- ከአንድ ሚሽነሪ የተገኘ እዉነተኛ ታሪክ

መልካም ቀን፤ ሐምሌ 26/11/2013ዓ.ም። “የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።”
— 2ኛ ቆሮንቶስ 13፥14

የመረጃ ምንጭ የእግዚአብሔር አገልጋይ ማስረሻ በላይ Facebook page የተወሰደ መልዕክት ነው።

https://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD/3296
2.2K viewsEphraim Grace, edited  14:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 16:58:27
እዉነተኛ_ታሪክ

በሶሪያ ጦርነት ጊዜ ነዉ፥ በምድረ በዳ የተገኘዉ እዉነተኛ ወዳጅ።

ሙሉ ታሪኩን ለማንበብ
https://t.me/PRAISE_TO_OUR_GOD/3296
1.1K viewsEphraim Grace, edited  13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ