Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxslijoch — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ortodoxslijoch — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች
የሰርጥ አድራሻ: @ortodoxslijoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.17K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ምንማማርበት :መዝሙር: ስብከቶች ይተላለፋል !

መንፈሳዊ ትምህርቶች : መንፈሳዊ ጥያቄዎች : ስብከት : መዝሙር : ይቀርብበታል #ጉዞው ገዳማት #ሰማህታት ታሪክ ይቀርባል!
FacebookGroup : ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ይቀላቀሉ ::

#shear

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 18

2022-11-09 07:26:03 "እንደ ሞተ ሰው ሁን"


❖ ከወንድሞች አንዱ ወደ አባ መቃርዬስ መጥቶ " አባክህ ለህይወቴ የሚሆን መመርያ ስጠኝ" አለው ፡፡ አባ መቃርዬስም ያንን ወንድም ወደ መቃብር ሂድና በሙታን ላይ ክፋ ነገር አድርግባቸው፡፡ ብሎ ላከው ሰውየውም በሙታኑ ላይ ድንጋይ በመወርወርና በመሳደብ የተላከውን ፈፅሞ መጣ ፡፡ " አባ መቃርዮስም ምን አሉህ ? ሲል ጠየቀው " ያም ወንድም "ምንም አላሉኝም " ብሎ መለሰ ፡፡ በነጋታውም ተመልሰህ ናና አመስግናቸው አለው፡፡ በነጋታውም ያ ወንድም ወደ መቃብሩ ስፋራ ተጉዞ ሙታኑን " ሐዋርያ ፣ ቅዱሳን ፣ጻድቃን ፣ እያለ አመሠገናቸውና ተመለሰ ፡፡ መቃርዮስም " ምን መለሱልህ አለው" ምንም አለ ፡፡" መቃርዮስም " ስትሰድባቸው ፣በድንጋይ ስትመታቸው ፣ ስታመሰግናቸውም ፣ ስታወድሳቸው ፣ ምንም አልመለሱልህም ፡፡ አንተም ለነፋስህ ድህነት ከፈለግክ እንደ "ሞተ ሰው ሆነህ ኑር" ፡፡ ሰዎች ክፋ ቢያደርጉብህም ቢያመሰግኑህም ምንም አይሰማህ አለው ፡፡፡

ወዳጄ ሆይ የታላቁን አባት ምክር ልብ አልክን ? የሚሰድብህንና ድንጋይ የሚወረውርብህን እንዴት ማለፋ እንዳለብህ ተማርክ ? የሚያመሰግኑህንና የሚያወድሱህን እንዴት መቀበል እንዳለብህ አስተዋልክ ?

☞ ቀልብህን የሚቀሙህን ብዙ ሰዳቢዎች አሉብህ ፡፡ የሚያስጎነብሱህ ብዙ ድንጋይ ወርዋርዎች አሉብህ ፡፡
☞ አንዱ ድህነትህን እያነሳ ያሸማቅቅሀል ፤ሀብት የሌለህና ገንዘብ መቁጠር ያልቻልከው የማትረባ ስለሆንክ ብቻ እንሆነ በማሰብ ያሳንስሀል
☞ በምግባርህ የሞትህ እንደሆንክ እየጮኸ ይነግርሀል
☞ ሃይማኖትህና ኢትዮጲያዊነትህ ለድህነት አስተዋፅኦ እንዳደረገና ማንነትህ ራሱ የተዋረደ እንደሆነ በመንገር ተፈጥሮህን " ንቀህ "አርቴፋሻል እንድትሆን ኦርጅናልነትህን አርክሰህ ፌክ እንድትሆን ይሰብክሃል፡፡
☞ በዘር ገመድ ተብትበው ከወንድምህ ጋር የሚያናቁሩህ ሃይማኖትህንና ሰብአዊነትህ ሳይቀር በዘረኝነት ሰፌድ የሚያበጥሩ ድንጋይ ወርዋርዎችን እንዴት ይሆን ያለፋካቸው ፡፡
☞ ጾምህን የሚያንቋሽሹ ፣ ሱባኤህን የሚረብሹ ፣ ጸበል መጠጣትህን ፤እምነት መቀባትህን የሚያንሻፋፉ ፤እግዚአብሔር በሞተ ነገር ላይ ታሪክ እንደሚሰራ ስትነግራቸው የሚስቁ ፤ በሰማይ ህይወት አለ ስትላቸው በሙት አምራቸው የሚሳለቁ ፤ይልቅ ዓለምህን ቅጭ ጊዜህን ተጠቀምበት የሚሉ አለማውያንና ማንነትህን ለማርከስ ማንነታቸውን ለማንገስ የሚወረውሩት ጥቁር ድንጋይ አቁስሎህ ይሆን ????

ወዳጄ ሆይ ታላቁ አባት እንዲህ ይልሃል ለስጋውያን ለስሌታውያን እንደ ሞተ ሰው ሁን !!!!
☞ ደግሞስ ገና ልትሰራ የምትችለውን ገና በልዑልነትህ ንጉስ ብለውህ ገና በወጣትነትህ ጻዲቅ አድርገውህ ገና በተማሪነትህ ረብኒ ብለውህ ዳዴህን ሳትጨርስ የአትሌትነት ማዕረግን ሰጥተውህ በዲያብሎስ መዝሙር ከፋ ከፋ በጣሙን ከፋ ከፋ ሗላ ስትወድቅ አጥንትህ እንዳይተርፋ ሰቅለው በአፋጢምህ የሚደፋህን አድር ባዮችና ህሊና ቢሶች እንዴት አልፈሀቸው ይሆን ? ለእነርሱም ወሬ መንኩሰህ እንደ ሞተ ሰው ሆንክን ??

☞☞ እንደ ሞተ ሰው ሆነህ የምታድነው ትዳር አለህ ፡፡
☞☞ እንደ ሞተ ሰው ሆነህ የምታድነው ህይወት አለህ
☞☞ እንደ ሞተ ሰው ሆነህ የምታጠነክረው ወዳጅነት አለህ
☞☞ እንደ ሞተ ሰው ሆነህ የምትሰራው እልፋ ስራ አለህ ፡፡

✞ ደግሜ ደግሜ እልሃለሁ የታላቁን አባት ቃል ተውሼ ለእነዚህ እንደሞተ ሰው ሁን!!!!

እንደ ሞተ ሰው ሁን እንጂ ሙት ሁን አልተባልክም ፤ እንደ ሞተ ሰው ሆነህ በግብርህ ሕያው ሁን እንጂ ሙት አትሁን፡፡

" ሀዋርያው እንዳለው አንተ ለዚህች አለም ሙትባት ይህች አለምም በአንተ ዘንድ የሞተች ትሁን ፡፡፡
"" እንደሞተ ሰው ሁን """
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
Join @ortodoxslijoch
887 views04:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-08 07:21:47 "እግዚአብሔር የሰው ልጅን ያዳነበት መንገድ በዕለተ ዐርብ በመሰቀሉና መከራን በመቀበሉ ብቻ የሚመስለውና ከነገረ መስቀሉ ውጪ ያለው ጉዳይ የሚጠቅም የማይመስለው ሰው ካለ ነገረ ድኅነትን ሙሉ በሙሉ አልተረዳም፡፡ እንደዚያ ቢሆን ኖሮ እግዚአብሔር በድንግል ማርያም ተፀንሶ ተወልዶ ሠላሳ ዓመታትን መቆየት ሳያስፈልገው ልክ የመጀመሪያውን አዳም እንደፈጠረው የሠላሳ ዓመት የሆነ ሥጋንና ነፍስን ለራሱ ፈጥሮ መለኮቱን አዋሕዶ ሰው መሆን ይችል ነበር፡፡ ይህንን ቢያደርግም ሦስት ዓመታት በምድር ላይ አስተምሮ በጊዜው ተሰቅሎ የማዳን ሥራውን መፈጸም ይችል ነበር፡፡

እርሱ ግን ማዳኑን የጀመረው በማሕፀን ከመፀነስ ነበር፡፡
አረጋዊው ስምዖን ‘ዓይኖቼ ማዳንህን አይተዋል’ እንዳለ ማዳኑንም የጀመረው ሕፃን ሆኖ በመታቀፉ ነው፡፡ ሉቃ. ፪፥፴ የጌታ የማዳን ሥራ ወሳኙ ታሪክ ከመስቀሉ ጋር በችንካር የታሰረበት ብቻ ሳይሆን በድንግል ማርያም እቅፍ በፍቅር የታሰረበት ቅፅበትም ነው፡፡ ክርስቶስ ሊያስታውሰው የማይፈልገው የልጅነት ሕይወት ያለው አይደለምና ስለ ክርስቶስ የሚሰብኩም ሁሉ ይህንን ድንቅ የሕፃንነት ጊዜውንና ያደገበትንሁኔታ ቸል ሊሉ አይገባም፡፡

ክርስቶስን ‘በመስቀል ላይ እንደተሰቀለ ሆኖ’ በሰዎች ልቡና እንዲሣል በመጀመሪያ በድንግል ማርያም እቅፍ እንደተወለደ ሆኖ መሣል ይገባዋል፡፡ ልብህ ውስጥ ሳይወለድ የሚሰቀል ክርስቶስ ካለ ለወለደችው እናቱና ለድንቅ ልደቱ ዋጋ ልትሠጥ አትችልም፡፡

መስቀል መሸከሙ ዘልቆ የሚሰማህ በልጅነቱ ያቀፈችውን ድንግል ማየት ስትችል ነው፡፡ ሐሞትና ከርቤ መጠጣቱ የሚያስለቅስህ ድንግልናዊ ወተትን ካጠባችው እናቱ ጋር አብረህ ስትሆን ነው፡፡ አልፋና ኦሜጋ እኔ ነኝ ላለው ክርስቶስ በምድር ላይ በቆየበት መዋዕለ ሥጋዌው አልፋው ድንግል ማርያም ስትሆን ኦሜጋው መስቀል ነበር፡፡ የተሰቀለ ቀን ብቻ አይተህ ልታውቀው አትችልም፡፡ ሁለተኛ አዳምነቱ ዘልቆ የሚሰማህ ወደ ልደቱ ስትመለስ ነው፡፡ የሰው ልጅ ቁስልም የሻረው ጌታ ሊወለድ ካለበት ቅፅበት ጀምሮ ነው፡፡

በገነት ዛፎች መካከል አንድ የረከሰ መልአክ እና አንዲት ሴት ተነጋግረው ተስማምተው ያበላሹትን የሰው ልጅ ታሪክ ድጋሚ ሊጽፈው የፈቀደው እግዚአብሔር በተቀደሰ መልአክና በአንዲት ሴት መካከል ንግግር አስጀመረ፡፡

ሰይጣን በምድር ከሚርመሰመሱ አራዊት መካከል
ተንኮለኛውን እባብን መርጦ ሔዋንን በማሳመን የሰው ልጅ ከገነት አስወጥቶታል፡፡ እግዚአብሔር ደግሞ በሰማያት ከሚያመሰገኑ ብርሃናዊያን መላእክቱ መካከል ከዋነኞቹ አለቆች አንዱን ቅዱስ ገብርኤልን መርጦ ድንግል ማርያምን እንዲያበሥራት ላከ፡፡

ሁለተኛይቱ ሔዋን ድንግል ማርያም ከመጀመሪያይቱ ሔዋን እጅግ በብዙ ነገሮች ትለያለች፡፡ ሔዋን የተቀደሰው ገነት ውስጥ ተፈጥራ ፈጣሪዋን የበደለች ስትሆን ድንግል ማርያም ግን በእርግማን በረከሰው ምድር ላይ ተፈጥራ የተቀደሰች ናት፡፡

የቀደመችው ሔዋን በገነት መካከል ሥራ ፈትታ የምትመላለስና የእባብን ድምፅ ሰምታ አዳምን ለሞት የምትዳርግ ስትሆን አዲሲቱ ሔዋን ግን ራስዋ ምድራዊት ገነት ሆና አዳምን ያስገኘች ናት፡፡ ከዚህች ገነት ተፀንሶ የተወለደው ሁለተኛው አዳም እንደ ቀድሞው አዳም ተባርሮ የወጣ ሳይሆን ‘ሙሽራ ከጫጕላው እልፍኝ እንደሚወጣ’ ከእርስዋ የወጣ ሙሽራ ነው፡፡

ይህችኛይቱ ሔዋን የሰው ልጅ ቃልዋን ቢሰማ ‘የሔዋንን ቃል ሰምተሃልና የተረገምህ ትሆናለህ’ ተብሎ የሚሞትባት ሔዋን አይደለችም፡ ፡ ይህች ድንግል ቃልዋን ብንሰማ የምንባረክባት ከአንደበትዋ የሚወጣው ቃል እንደ ሔዋን ካለመታዘዝ ፍሬ እንድንበላ ሳይሆን ‘የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ’ የሚል የሚያድን ቃል ነው፡፡ ዮሐ. ፪፥፭

ያችኛይቱ ሔዋን ከአዳም ተገኝታ የተሠራችና አዳም ወደ
እርስዋ እያየ ‘ይህች አጥንት ከአጥንቴ ይህች ሥጋ ከሥጋዬ ናት’ የሚላት ናት፡፡ ይህችኛይቱ ሔዋን ድንግል ማርያም ግን ከአዳም የተገኘች ሳትሆን አዳምዋ ክርስቶስ ሥጋው በጅራፍ ግርፋት ሲቆስልና አጥንቶቹ ሲቆጠሩ በጭንቀት እያየች ‘ይህ አጥንት ከአጥንቴ ነው ፤ ይህ ሥጋም ከሥጋዬ ነው’ የምትል ሔዋን ናት፡፡

የቀደመችዋ ሔዋን አዳምዋ በእርስዋ ምክንያት ጠፍቶ ‘አዳም ሆይ ወዴት ነህ?’ ተብሎ ሲፈለግ በዛፎች መካከል ሆኖ ከአባቱ ከእግዚአብሔር ‘ፈርቼ ተሸሸግሁ’ የሚል አዳም ሲሆን ሁለተኛይቱ ሔዋን ግን አዳምዋን ፍለጋ የምትጨነቅና ወዴት ነህ? ስትለው አዳምዋ ‘በአባቴ ቤት እኖር ዘንድ እንዲገባኝ አታውቁምን’ ብሎ የሚመልስላት ከአባቱ እቅፍ ያልተለየ አዳም እናት ናት፡፡

ለድንግል ማርያም ክርስቶስ ከእርስዋ የተገኘ አዳምዋ ብቻ ሳይሆን በቀናተኞቹ ቃየኖች አይሁድ በግፍ የተገደለባት አቤልዋም ጭምር ነው፡፡ ልዩነቱ የአቤል ደም ወንድሙን የሚከስስ ደም ሲሆን የእርስዋ ልጅ የክርስቶስ ደም ግን ‘ከአቤል ደም ይልቅ የሚሻለውን የሚናገር’ ‘ከኃጢአት ሁሉ የሚያነጻ ደም’ ነው"

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥቅምት 27 2015 ዓ.ም.
ከብርሃን እናት መጽሐፍ ገጾች
1.5K views04:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-07 05:31:14 አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው ማለት ነው
ዘወትር እግዚአብሔ ከሁላችን ጋር ይሁን በቸርነቱ ይጠብቀን አሜን

አማኑኤል ማለት አማኑ ኤል፣ የአምላክ ሰላም፣ የእግዚአብሔር እርቅ፣ የጌታ አንድነት ማለት ነው።

« አማነ»እና «ኤል» ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከኛጋ ማለት ነው።

« ድንግል ትፀንስ ወትወልድ ወልደ ወይሰመይ ስሙ አማኑኤል ዘበትርጓሜሁ እግዚአብሔር ምስሌነ»

«ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልጅንም ትወልዳለች ሰሙንም አማኑኤል ትለዋለች ትርጉሙም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው፡፡» ( ኢሳ 7፥14)

ክብር ፣ኃይልና ምስጋና ለአምካችን ለአማኑኤል ይሁን ለዘለዓለሙ አሜን።
ወስብሓት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክብር አሜን
Join @ortodoxslijoch
3.4K views02:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-05 18:54:09 ​​በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን፡፡ ✞✞✞

✞ ጥቅምት ፳፯ (27) ✞

✞✞✞ እንኳን ለፈጣሪያችን "መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ" እና ለቅዱሳኑ "አባ መቃርስ": "አቡነ መብዓ ጽዮን" "ወአባ ጽጌ ድንግል" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ

ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ለእኛ ሲል በፈጸመው የማዳን ሥራ ክፉዎች አይሁድ ከምሽቱ 3:00 ጌቴሴማኒ ውስጥ ያዙት:: ሙሉውን ሌሊት ከቀያፋ ወደ ሐና: ከሐና ወደ ቀያፋ ሲያመላልሱት: አስረው ሲደበድቡት አድረዋል::

ዝም ቢላቸው ዓይኑን ሸፍነው በጥፊ መቱት:: ምራቃቸውን ተፉበት:: ዘበቱበት:: ራሱንም በዘንግ መቱት:: እርሱ ግን ሁሉን ታገሰ:: በጧት ከገዢው ዘንድ ሞት እንዲፈረድበት አቀረቡት::

በሠለስት (3:00 ላይ) አካሉ እስኪያልቅ እየተዘባበቱ 6,666 ገረፉት:: ሊቶስጥሮስ አደባባይ ላይ እርጥብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት:: 6:00 ላይ በረዣዥም ብረቶች 5 ቦታ ላይ ቸንክረው ሰቀሉት::

7 ታላላቅ ተአምራት በምድርና በሰማይ ታዩ:: ዓለም በጨለማ ሳለች ጌታ በመስቀል ላይ 7 ቃላትን ተናገረ:: ከቀኑ 9:00 አካባቢ በባሕርይ ስልጣኑ ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ለየ::

+በዚያች ሰዓትም ወደ ሲዖል ወርዶ የታሠሩትን ሁሉ ፈታ:: 11:00 ላይ ደጋጉ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከታላቅ ክብርና ሐዘን ጋር በአዲስ መቃብር ቀበሩት:: በዚአች ቀን ድንግል ማርያም ልቧ በሐዘን ተቃጠለ:: ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም ፍፁም ለቅሶን አለቀሰ:: ቅዱሳት አንስት በዋይታ ዋሉ::

ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለው መጋቢት 27 ቀን ቢሆንም በዓሉ ወደ ጥቅምት እንዲመጣ ያደረጉት አበው ሊቃውንት ናቸው:: ምክንያቱም ብዙ ጊዜ መጋቢት 27 የሚውለው ዓቢይ ጾም ውስጥ በመሆኑና የንግሥ በዓላት በዓቢይ ጾም ስለማይፈቀዱ ነው::

ምንም እንኩዋ በቅርብ ጊዜ በዓቢይ ጾም የሚያነግሡ አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት ቢኖሩም አባቶቻችን ግን እንዲህ ያለውን ሥርዓት አላቆዩልንም:: ከበሮና የቸብቸቦ ዝማሬም በወቅቱ የተፈቀደ አይደለም::

በዚህም ምክንያት የበዓለ ስቅለት ንግሡ ወደ ጥቅምት 27 ሲመጣ: የመጋቢት 5 ገብረ መንፈስ ቅዱስ ንግሥ ወደ ጥቅምት 5: የመጋቢት 10 መስቀል ወደ መስከረም 17 መጥቶ እንዲከበር ሆኗል::

ዝክረ ቅዱሳን
1.8K views15:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-05 09:43:40 #መድሃኒአለም ማለት የአለም ሁሉ መድሃኒት ማለት ነዉ
ስጋዉን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ ለኛ ሲል ህይወቱን የሰጠ

፨ አሮንና ልጆቹን ....... ለክህነት የመረጠ
፨ ኤልያስን ....... በአዉሎ ነፋስ የነጠቀ
፨ እዮብን ....... በባእድ ሀገር ከፍ ከፍ ያደረገ
፨ ሎጥን ........ ከእሳት ያወጣ
፨ ለሳምሶን ........ ሀይልን የሰጠ
፨ አዛርያን አናንያን ሚሳኤልን ....... ከእሳት የታደገ
፨ ጥበብና ማስተዋልን ....... ለሰለሞን የሰጠ
፨ ያዕቆብን ....... በመንገዱ የጠበቀ እና የባረከ
፨ እስራኤልን ....... ከግብፅ ባርነት ያወጣ
፨ ለሙሴ ....... ጽላት የሰጠ
ለኪሩቤል ላይ የተቀመጠ ክብሩንም የገለጠ ስጦታዉ የማያልቅበት

#ቸሩ_መድሃኒአለም_ይክበር
_ይመስገን_አሜን /፫/
#መድኃኒአለም _የገዢዎች ሁሉ ገዢ
#መድኃኒአለም ____ የነገስታት ሁሉ ንጉስ
#መድኃኒአለም ____ የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ ነዉ
ኃይሌን ጉልበቴን ታድሳለህ
ቀና ቀና እንድል ታደርጋለህ
መድኃኒአለም መድኃኒቴ

መ ____ መሃሪ ይቅር ባይ አምላክ
ድ ____ ድካሜን ተመልከት ስለዉ ተበርክኬ
ኃ ____ ኃያላት የማይችሉህ የኃያላን ኃያል
ነ ____ ነፍሴ ትልኃለች ጌታዬ ይረዳኛል
አ ____ አለምን ለማዳን መስቀል ላይ የዋለ
ለ ____ ለዘላለም ፍቅር ነህ ሁሌ የማትቀየር
ም ____ ምህረትህ የበዛ
#የድንግል_ማርያም_ልጅ_ቸሩ_መድኃኒአለም_አንተ_ነ
ህ_አባቴ !!

ቸሩ መድኃኒአለም በያላቹሁበት ይጠብቃችሁ ወጥቶ ከመቅረት ከድንገተኛ አደጋ ይጠብቃችሁ አሜን/፫/
የሚያኖረን ሰዉ ሳይሆን የአለም መድኃኒት የሆነዉ ለእኛ ሲል የእሾህ አክሊል የደፈዉ ቸሩ መድኃኒአለም ነዉ።
ቸሩ መድኃኒአለም ሃገራችን ይጠብቅልን
የዲያብሌስ ስራ እጅግ ተስፋፍቶብን
የሰዉኛ ዘይቤዉ ከእኛ ዘንድ ጠፍቶብን
ምግባራችን ከፍቶ ትዛዝህን ሽረን
..... በበደል ጨቂተን

ዉስጣችን ሲያነባ ካንተ ተሰዉረን
ለሰዉ ልጅ ነዉና ደምህ የፈሰሰዉ
በምህረት እጆችህ እንባችን አብሰዉ
ምስጋና ይሁን ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ጥንት ለነበረ አሁንም ላለ ኋላም የሚኖር ስሙ የተመሰገን ይሁን አሜን

Join @ortodoxslijoch
1.6K views06:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-04 16:06:58 + አልለምንም እግዚአብሔርንም አልፈታተንም +

‘እነሆ ድንግል ትጸንሳለች’ የሚለው ትንቢት ከመነገሩ አስቀድሞ ምክን ያት የሆነ አንድ ክስተት ይህ ነበር፡፡
የይሁዳ ንጉሥ አካዝ ዙሪያውን በጠላቶች ተከብቦ ነበር፡፡ ሁለት ነገሥታት ሊወጉትና ኢየሩሳሌምን ሊወርሯት አሰፍስፈው እየጠበቁ ነው፡፡ የጦር ምክራቸውም ‘ወደ ይሁዳ እንውጣ እናስጨንቀው እንስበረው በላዩ ላይም ሌላ ንጉሥ እናንግሥበት’ የሚል ነበር፡፡ ይህን ምክራቸውን አስቀድሞ ይነግረው ዘንድ እግዚአብሔር ነቢዩ ኢሳይያስን ወደ ንጉሥ አካዝ ላከው፡፡ ኢሳይያስም የሚመጣበትን የጠላት ከበባና መጻኢ ፈተናውን ነገረው፡፡

እንደመፍትሔም እንዲህ አለው ‘ከጥልቁም ወይም ከከፍታውም ከእግዚአብሔር ምልክትን ለምን’ የሚል ምክር ነበር፡፡ እግዚአብሔር ወይ ከሰማይ ወይ ከምድር አንዳች ተአምር አድርጎ ከዚህ ጭንቅ እንዲያወጣህ ፈጣሪህን ለምን ብሎ የነገረው ከእግዚአብሔር በቀጥታ የተላከው ነቢይ ነበር፡፡ ‘’ለምነኝ አሕዛብን ለርስትህ እሰጥሃለሁ’ እንደማለት ያለ ዕድል ቀርቦለት ነበር፡፡
ንጉሥ አካዝ ግን ግልጽ እና አጭር ምላሽ ሠጠ ፦ አልለምንም ፤ እግዚአብሔርንም አልፈታተንም! /ኢሳ 7፡13/

እርግጥ ነው በኦሪት ጌታ አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ተጽፎአል፡፡ ራሱ እግዚአብሔር ነቢዩን ልኮ ለምነኝ ተአምር ልፈጽምልህ እያለህ ‘አልለምንም እግዚአብሔርን አልፈታተንም’ ማለት ግን በራሱ እግዚአብሔርን መፈታተን ነው፡፡

ንጉሥ አካዝ እንዲህ በጠላት ተከብቦ እያለ ‘ወደ ፈጣሪ ለምን’ ሲባል እምቢ ያለው እርሱ እንዳለው እግዚአብሔርን ላለመፈታተን አልነበረም፡፡ በዚያ ጦርነት እንዲረዳው ወደ አሶር ንጉሥ ቴልጌልቴልፌልሶር መልእክተኛ ልኮበት ስለነበር ነው፡፡ በታላላቅ ተአምራት ሕዝቡን የታደገ እግዚአብሔርን እንዲለምን ጥሪ እየቀረበለት አካዝ ግን ከፈጣሪ ይልቅ በአሶር ንጉሥ እርዳታ ተስፋ አድርጎ ነበር፡፡ ኢሳይያስም ጸልይ ሲለው የልቡን ሃሳብ ደብቆ ፣ ከፈጣሪ ይልቅ በሰው ለመመካቱም መንፈሳዊ ካባን አልብሶ ‘ፈጣሪን አልፈታተንም’ ብሎ ተናገረ፡፡

አካዝ ይረዳኛል ብሎ የተማመነበት በመጽሐፍ ቅዱስ በስሙ ርዝመት ሁለተኛ የሆነው ቴልጌልቴልፌልሶር በጥያቄው መሠረት ወደ ይሁዳ ቢመጣም እንኳን አስጨነቀው እንጂ አልረዳውም፡፡ ይረዳኛል ብሎ ከቤተ መንግሥቱ ፣ ከመኳንንቱ ግማሹን አሳልፎ ለአሶር ንጉሥ እስከመሥጠት ቢደርስም ቴልጌልቴልፌልሶር ግን እንደ ስሙ የተንዛዛ ቆይታ ቆይቶ በዘበዘው፡፡ ችግር በመፍታት ፈንታ ችግር ሆነበት ፤ አካዝም በዚህ ተበሳጭቶ ‘ለምነኝ‘ ብሎ ሲጠይቀው አልፈልግም ያለውን እግዚአብሔርን መንቀፍ ጀመረ፡፡ ጭራሽ ጠላቶቼ እኔን ድል ያደረጉት አማልክቶቻቸው ከእኔ አምላክ ቢበልጡ ነው ብሎ ለጠላቶቹ አማልክት መሥዋዕት አቀረበ፡፡ መጨረሻውም እጅግ የከፋ ሆነ፡፡ /2ዜና 28፡20/

‘’አልለምንም እግዚአብሔርን አልፈታተንም’’ ብዙ ጊዜ የእምነታችንን ማነስ የምንደብቅባት ሽፋን ናት፡፡ ሀገር ሲታመስ ፣ መከራ ሲጸና ፣ ነገሮች ድብልቅልቅ ሲሉ ፣ ጠላት ከግራና ቀኝ ሲበዛ ምንድን ነው መፍትሔው? አካዝን ለምነኝ ያለ አምላክ ለእኛም ‘‘በመከራህ ቀን ጥራኝ እኔም አድንሃለሁ አንተም ታከብረኛለህ’’ ብሏል፡፡ /መዝ 49፡15/ በደስታችን ቀን ትዝ ብሎን የማያውቀው ፈጣሪያችን ግድ የለም በመከራህ ቀን ጥራኝ ብሎ ለሁላችን ጥሪ አቅርቧል፡፡ ምንም ዓይነት ፈተና በግላችን ፣ በሀገራችንና በቤተ ክርስቲያናችን ላይ ሲመጣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መፍትሔዋ ከጥልቁ ወይም ከከፍታው ምልክትን ከእግዚአብሔር መለመን ነው፡፡ በጎንደርና አክሱም በመላው ዓለም ባሉ አድባራትና ገዳማትዋ ስታደርግ እንደነበረው ዓይነት ምሕላና ጸሎት ታውጃለች፡፡ ዕንባዋን ትረጫለች ፤ የኃያላን ኃያል ፣ ብርቱዎችን ከዙፋናቸው የሚያዋርድ ፣ ትዕቢተኞችን የሚሰብር አምላክ እንዲደርስላት እንደ ኢሳይያስ የፈጣሪ አንደበት የሆነች ቤተ ክርስቲያን ጸልዩ ትላለች፡፡

ይህን ጊዜ አካዞች እንበሳጫለን ‘አልለምንም ፣ እግዚአብሔርንም አልፈታተንም’ እንላለን ቤተክርስቲያንን የላካት ኢሳይያስን የላከው አምላክ መሆኑን አናስተውልም፡፡ የጾም ፣ ጸሎት ፣ ስግደት ፣ ምሕላ ጥቅም አይታየንም፡፡ ሌላ መፍትሔ መፈለግ ነው እንጂ ዝም ብሎ ወደ ሰማይ በማንጋጠጥ ጊዜ ማጥፋት የለብንም እንላለን በሆዳችን፡፡ አፋችን ግን ለታዛቢ ይጠነቀቃል ስለዚህ ‘ዝም ብሎ መጸለይማ እግዚአብሔርን መፈታተን ነው’ እንላለን፡፡ እነ እገሌ ቢረዱን ብለን የምናስባቸው ቴልጌልቴልፌልሶሮች ብዙ ናቸው፡፡ ማናቸውም ግን መጥተው ያስጨንቁናል እንጂ አይረዱንም፡፡ ሰውን ተስፋ ከማድረግ ከጥልቁ ወይም ከከፍታው ምልክትን ብንለምን ጥሩ ነው፡፡

እኛ ባንለምንም ግን እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንደሚሆን እንዲህ ብሎ ተጽፎአል፦

ጌታ ራሱ ምልክትን ይሠጣችኋል ፤ እነሆ ድንግል ትጸንሳለች ወንድ ልጅንም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ይሉታል /ኢሳ 7፡14/

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ታኅሣሥ 24 2012 ዓ ም
ሐዋሳ ፤ ኢትዮጵያ
1.6K views13:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-27 06:46:27 ⨳የቅዱስ እስጢፋኖስ ታሪክ ባጭሩ
እስጢፋኖስ የግሪክ ቋንቋ ሲሆን

ትርጓሜውም «አክሊል» ማለት ነው።
ቅዱስ እስጢፋኖስ በግሪክ ሀገር እንደተወለደ የሚነገርለትና ከክርስቶስ እርገት በኋላም አስራ ሁለቱም ሐዋርያት በጋራ ተሰብስበውና ለአገለግሎት ከመረጡዋቸው ሰባት ዲያቆናት አንዱና ዋነኛው ነበር። ሕዝቡን በማዕድ ያገለግሉ ዘንድ ሰባት ዲያቆናት ተመርጠዋል።

ከእነዚህ መካከል ቅዱስ እስጢፋኖስ አንዱ ሲሆን ለስድስቱ ዲያቆናት ደግሞ አለቃ ሊቀ ዲያቆን ሆኖ ተሹሟል። ቅዱስ እስጢፋኖስ በማዕድ አገልግሎት ሕዝቡን ከማገልገሉ በተጨማሪ ወንጌልን ይሰብክ ነበር ። ተዐምራትን የማድረግ ጸጋም ተሰጥቶት ነበር በዚህም አገልግሎቱ ብዙዎችን ወደ ክርስትና መልሷል።
በዚህም አይሁድ በቅናት ተነሳስተው በሐሰት ከሰሱት ከከተማውም ወደ ውጭ አውጥተው ቄዳር በተባለ ቦታ በድንጋይ ወገሩት በሚወግሩትም ጊዜ ሰማያት ተከፍተው ምሥጢረ ሥላሴን እግዚአብሔርን በሦስትነቱ ተመለከተ።
ኢየሱስ ክርስቶስንም በአብ ቀኝ ተቀምጦ አየ ። ለሚወግሩትም ሰዎች ከአምላኩ እንዲህ በማለት ምሕረትን ለመነ «ጌታ ሆይ ይህንን ኃጢአት አትቁጠርባቸው» በመጨረሻም «ጌታ ኢየሱስ ሆይ ነፍሴን ተቀበል»ብሎ ነፍሱን ሰጠ።
ከከተማም ወደ ውጭ አውጥተው ወገሩት። ምስክሮችም ልብሳቸውን ሳውል በሚሉት በአንድ ጎበዝ እግር አጠገብ አኖሩ። እስጢፋኖስም። ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ነፍሴን ተቀበል ብሎ ሲጠራ ይወግሩት ነበር። ተንበርክኮም። ጌታ ሆይ፥ ይህን ኃጢአት

አትቍጠርባቸው ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህንም ብሎ አንቀላፋ። ሳውልም በእርሱ መገደል ተስማምቶ ነበር። 《የሐ ሥራ 7፥58—60》

⨳ የቅዱስ እስጢፋኖስ ረድኤት በረከትና ምልጃው አይለየን ለዘለዓለሙ አሜን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክብር አሜን
Join @ortodoxslijoch
4.5K views03:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-26 07:24:21 ኪዳነ ምህረት

ኪዳነምህረት ስንል የምህረት ቃልኪዳን ማለት ነው፡፡በዚህ ውስጥም ምህረት አድራጊው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ምህረት ተቀባይም መላው የአዳም ዘር ነው፡፡


እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በምድራዊ ቆይታዋ ዘውትር ወደ ክርስቶስ መካነ መቃብር ጎለጎታ እየወረደች ትፀልይ ነበር፡፡ ልጇ እና ወዳጇ ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገችው ልመናና ፀሎት ተመልክቶና ሰምቶ የምህረት ቃል ኪዳን ገባለት ፡፡


እንኳን የእናቱን ፀሎት እና ልመና ቀርቶ ዘውትር በሀጥያት የምንዘፈቀውን እኛን ክፉዎቹን የሚሰማ አምላክ ስለ አንቺ ፣ ስለ እናቴ ክብርና ፀጋ ስል ይኸው ቃሌ ብሎ ቃልኪዳን አደረገ፡፡
« ከመረጥሁት ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ። … » መዝ, 89 : 3 እንዲል መፅሐፉ፡፡

ስሟን ለሚጠሩ፣ በእርሷ አማላጅነት ለሚታመኑ በምድር በረከትን በሰማይ የዘለዓለም መንግስትን እንደሚወርሱ የምህረት እና የቸርነት ቃልኪዳን ሰጥቷታል ፡፡

ታላቁ መፅሐፍ እንዲህ ይላል፦
". . . ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች፤ በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ ሁሉ መካከል ያለውን የዘላለም ቃል ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ። " ኦሪት ዘፍ. 9 : 16

በዚህም መሠረት ቃልኪዳኗን ምክንያት በማድረግ ኪዳነ-ምህረት እያልን እንጠራታለ

እንኳን ለ«ኪዳነምህረት» አደረሳችሁ። የእመቤታችን ምህረት እና ረድዔት፤በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን!!!
@ortodoxslijoch
@ortodoxslijoch
6.1K views04:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-24 15:27:27 + ሽማግሌው አባታችሁ ደህና ነው? +

ዮሴፍ በግፍ የሸጡት ወንድሞቹን ለሁለተኛ ጊዜ ሲያገኛቸው እንዲህ ሲል ጠየቃቸው ‘የነገራችሁኝ ሽማግሌው አባታችሁ ደህና ነው? ገና በሕይወት አለን?’ እነርሱ መለሱ ፦ አባታችን ደህና ነው ገና በሕይወት አለ አሉት፡፡ (ዘፍ 43:27)

ዮሴፍ የጠየቀው የአረጋዊውን አባቱን የያዕቆብን ደህንነት ነበር፡፡ እርሱ ወንድማቸው መሆኑን ገና ስላላወቁ ‘አባቴ ደህና ነው?’ በማለት ፈንታ ‘ሽማግሌው አባታችሁ’ አለው፡፡ እርግጥም ያዕቆብ መቶ ሠላሳ ዓመቱ ነበር፡፡ ዮሴፍ እንደፈራው አልሞተም፡፡ ገና በሕይወት ነበረ፡፡

ይህንን ዮሴፍ ለወንድሞቹ የጠየቀውን ጥያቄ ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ጻድቁን አቡነ አረጋዊን ለመጠየቅ በሔደ ጊዜ ዳግም ተናግሮታል፡፡ ቅዱስ ያሬድ ወደ ደብረ ሃሌሉያ ዳሞ ተራራ በደረሰ ጊዜ ከተራራው ግርጌ ዮሴፍና ማትያስ የተባሉ ሁለት የአቡነ አረጋዊ ደቀ መዛሙርትን አገኘ፡፡

‘ዳኅንኑ ዝስኩ አረጋዊ አቡክሙ’ [ሽማግሌው አባታችሁ ደህና ነውን] ብሎም ጠየቃቸው፡፡ ይህ ንግግሩ መልስ አግኝቶ ሳያበቃ ምስጋና ሆኖ በአቡነ አረጋዊ ማሕሌት ይዜማል፡፡ ሽማግሌው አባታችሁ [አረጋዊ አቡክሙ] የተባለለት ጻድቁ አቡነ ዘሚካኤል አረጋዊ ተብሎ ለመጠራት እንደ ያዕቆብ 130 ዓመታት መቆየት አላስፈለገውም፡፡ ገና በዐሥራ አራት ዓመቱ መንኖ ለብዙዎች መመነን ምክንያት የሆነ በዕድሜው ሳይሆን በቅድስናው አረጋዊ ለመባል የደረሰ ጻድቅ ነበር፡፡

ዛሬም ላይ ሆነን የዮሴፍንና የቅዱስ ያሬድን ጥያቄ ደግመን እንመልስ፡፡ ‘’ሽማግሌው አባታችሁ ደህና ነው? ገና በሕይወት አለን?’’ ለሚለን ሁሉ መልሳችን ‘አረጋዊው አባታችን [አቡነ አረጋዊ] ደህና ነው፡፡ አሁንም ድረስ በሕይወት አለ ፤ እግዚአብሔር ሰወረው እንጂ አልሞተም፡፡ የሚል ነው፡፡

ጻድቁ አባታችን አረጋዊ ሆይ ዮሴፍ ስለ አባቱ ደህንነት እንደጠየቀ እኛ ስለ አንተ ደህንነት አንጠይቅም፡፡ እግዚአብሔር ያከበረህ ሆይ ባይሆን እኛ ልጆችህ ግን ደህና አይደለንም፡፡ ነፍሳችን ዛሬ በፊትህ የከበረች ትሁንና ልጆችህን በምልጃህ አስበን፡፡ ዮሴፍ ሽማግሌ አባቱን በፈርኦን ፊት እንዳቀረበ እኛም አረጋዊ አባታችንን በእግዚአብሔር ፊት ትማለድልን ዘንድ በጸሎታችን እናቀርብሃለን፡፡

ከዳሞ ተራራ ላይ ሆነህ ከችግር መውጫ ቸግሮአት ሰማይ ሰማዩን ለምታይ ሀገራችን የምልጃህን ገመድ ወርውርላት፡፡ ሊተናኮሏት የተጠመጠሙባትን ዘንዶዎችም ወደ መልካም ዘመን መወጣጫ መሰላሎችዋ አድርግላት፡፡ ካለችበት ውድቀት ወደ ከፍታ መወጣጫ ወደ መልካም መሸጋገሪያ ገመድ ትፈልጋለችና የጸሎት ገመድህን ላክላት::

ያን ጊዜ እንዲህ ትላለች ፦
ገመድ ባማረ ስፍራ ወደቀችልኝ ርስቴም ተዋበችልኝ’ መዝ 16፡6

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥቅምት 14 2013 ዓ.ም.

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ዘንድ ጸልዩ! ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like እና Share ያድርጉ
FB: https://www.facebook.com/officialHenokhaile/
Telegram: https://t.me/deaconhenokhaile
Instagram: https://www.instagram.com/p/CBnMF0nnhcQ/?igshid=549jvl607bv4
Youtube: https://www.youtube.com/channel/UCOaVsWC05aUjeqIEW3fWj7g
4.4K views12:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-23 21:07:12 አቡነ #አረጋዊ_ዘደብረዳሞ_እንኳን_አደረሰን
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
አረጋዊ ማለት ሽማግለ ወይም የልጅ አዋቂ ማለት ሲሆን አባታቸው ይስሃቅ እናታቸው እድና ይባላሉ::በቈስጥንጥንያ ወይም በሮም በታህሳስ ፲፬ ፫፻፸፭ ዓ.ም ተወለዱ::

በመቶ ፲፬ ኣመታቸው ወደ ገዳም ገቡ:: ከአባ ጳኩሚስ እጅ ምንኩስናን ተቀበሉ::ከ፰ ቅዱሳን ጓደኞቻቸው ጋር በ፬፻፷፮ ዓ.ም ወደ ታላቂቷ ሀገር ኢትዮጵያ መጡ::ደብረ ዳሞ የቀድሞ ስሙ ሃሌ ሉያ ይባል ነበር:: ከዚያ ተራራ ስር ማን ያውጣኝ እያሉ ሲፀልዩ መልዓኩ ቅዱስ ሚካኤል ዘንዶ ላከለት ዘንዶም ቁመቱ 60 ክንድ ነበር። 30 ክንድ ወደፊት 15 ክንድ ወደ ኋላ ከመሀል ያለው 15 ክንድ ወገባቸው ላይ ተጠምጥሞ ጥቅምት ፲፪ ቀን መልዓኩ ዘንዶውን እያዘዘው ተራራውን ላይ ወጡት::ቅዱስ አባታችን አቡነ አረጋዊ በተወለዱበት በ150 ዓመታቸው ወደ ደብረ ዳሞ ገዳም ከወጡ በኋላ በሞት ፋንታ በጥቅምት፲፬ ቀን ፭፻፳፭ ዓ.ም #ተሰውረዋል::

የእግዚአብሔር መንግስት በኃይል ስትመጣ እስከያዩ ድረስ ሞትን የማይቀምሱ አንዳንዶች አሉ አላቸው ማር ፡ 9፡-1-2 ስለዝህ ቅዱስ አባታችን አቡነ አረጋዊ አልሞቱም ተሰውረዋል:: “ የፃድቅ ፀሎት በስራዋ እጅግ ሃይል ታደርጋለች” ያዕ፡ 5-16፣ ማቴ፡ 10-40፣ መዝ፡ 88-3 መዝ፡67-35
<<ዝክረ ፃድቅ ለኣለም ይሄሉ>>" መዝ.፻፲፩.፮

ለዝህም ነው በየዓመቱ ከተሰወሩበት ጀምሮ ጥቅምት 14 የቅዱስ አባታችን አቡነ አረጋዊ ዝክረ በዓል ሆኖ እስከ አሁን እንደሚታዩት በደብረ ዳሞ ገዳም ይከበራል እስከ ዳግም ዕለተ ምፅኣት #ይከበራል።

የአቡነ አረጋዊ በረከት ረድኤት አይለያቹህ አይለየን፣ ለእግዚኣብሔር ክብር ምስጋና ይግባው፣ ዘለአለማዊ ስቡሕ አምላክ ከኛ ጋር ይሁን።ወለተ ተክለሃይማኖት
ወስበሐት ለእግዚአብሔር ይቆየን

join @ortodoxslijoch
5.2K views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ