Get Mystery Box with random crypto!

ነገረ ወንጌላውያን

የቴሌግራም ቻናል አርማ negere_evangelical — ነገረ ወንጌላውያን
የቴሌግራም ቻናል አርማ negere_evangelical — ነገረ ወንጌላውያን
የሰርጥ አድራሻ: @negere_evangelical
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.86K
የሰርጥ መግለጫ

በወንጌላውያን አማኞች ዘንድ የሚፃፉ ፅሁፎች፣ ዘገባዎችና ዜናዎች ይቀርባሉ! ትምህርቶች፣ መረጃዎችና ምካቴ እምነቶች በዚህ ቻናል ይስተናገዳሉ! በተለያዮ ሶሻል ሚዲያዎች የሚገኙ ፀሐፊያን የሚፅፉቸው ፅሁፎችን እናጋራለን።

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-07 13:30:11 #ሰባቱ_ዓለማት_ግን... ባለሙያዎቹ ቢረግጧቸው አይሻልምን? [ርዕስ መሆኑ ነው]

ሃይማኖት፣ ቤተሠብ፣ ትምህርት፣ መንግሥት፣ ቢዝነስ፣ ሚዲያ፣ አርት እና የመዝናኛ ኢንዱሰትሪ - ዶሚኒየሞች ለመጨበጥና ዓለም ላይ ተጽዕኖ ለመፍጠር የሚመኟቸው ተራራዎች ወይም ደግሞ ዓለሞች ናቸው።

መንግሥትንም ይህን 'ጥበባቸውን' ይግቱታል። እንዲህ ዓይነቱ ጉዳይ የጨለማ ክፍለዘመን የሚባለውን የመካከለኛው ክፍለ ዘመንን [500 - 1500 A.D. አካባቢ] ቤተክርስቲያንን ያስታውሰኛል። ፍርድም እውቀትም፣ ፍትህም ጥፋትም፣ ፈውስም በረከትም ከቤተክርስቲያን በመንግሥት በኩል ለሕዝቡ ይፈስ ነበር።

መካከለኛ ዘመን የሚለው ስያሜ ራሱ ጥበብና ፍልስፍና ከገነነበት ዓለም አንስቶ ሰብዓዊነት [humanism] ብቅ እስካለበት 15ኛው ክፍለዘመን ድረስ የነበረውን ዘመን ነበር። በመሃል ያለው ቤተክርስቲያን ጥበብን ፍልስፍናን ሳይንስን ጠቅልዬ እኔ ካልባረኩት መላም የለው ያለችበት ዘመን ነው። ስለዚህም ጥበብን ወዳጆች መካከለኛው ዘመን ይሉታል እንጂ ምንም የማድረግ ነጻነት ስለሌለ ከቁምነገር አይከቱትም። የሆነ ጥሩ ዘመንና የሆነ 'ብርሃን' ዘመን ያለ መካከለኛ። የተሃድሶ ዘመን ራሱ ለምን እንደደመቀ ፍንጭ ይሰጣል።

እናሳ:-

ዶሚኒየም መጣልሃ! 7 spheres ምናምን እያለልህ። አማኞችን 'ብሪሊየት ስግብግብ' ለማድረግ የሚያነቃቃ ነው። እንደ መካከለኛው ክፍለዘመን ሳይንሱም፣ ፖሊሲውም፤ አርቱም፣ ፖለቲክሱም፤ ፈረንካውም መዝናኛውንም... አንተ ካልቀረጽከው ይህቺ ዓለም መጥፋቷ ነው እያለ ያወራጭሃል።

ወገኔ: - የቄሳርን ለቄሳር መርህን ብትከተል ትህትና ነው። ሃይማኖት ላይ የዶሚኒየኒዝም ጨረር ከምትረጭ ተማር። ሃይማኖት የሰው ልጆችን እኩልነት እንደሚያከብር፣ ጥሎ መነሳትን እንደሚነውር፤... ተማር። ሃይማኖትህን ሌላው ላይ እየሠለጠንክ ሳይሆን ለሌላው እየኖርክ ጠብቅ። የምን ጨረር መልቀቅ ነው።

ማሕበረሰብን ለማቅናት በዓለም ላይ ተፈትነው ለዛሬ ዘመን የበቁ ማሕበራዊ ሳይንሶችን ዩኒቨርስቲ ገብተህ ተማር። ወይም አንብብ። በአዳራሾቻችን የለመድነውን ሁከትና ሠለም የለሽ ምልልስ ይዘህ ማሕበረሰብ ላይ ዶሚኒየም ምናምን ስትል እፈር። ፖለቲኪኛው ፖለቲካ ይማር። የአርቱም ሰው የሙያውን እውቀት ያዳብር። ፈረንካውንም ለኢኮኖሚስቶቹ ተው! ምንድነው ወጧ እንዳማረላት ሴት እየጠቀስኩ ሁሉንም ካላማሰልኩ ማለት?

ታዲያ ቤተክርስቲያን ምን ቀራት? እጃችንን አጣጥፈን እንቀመጥን? ትለኝ ይሆናል። በጉዳዩ ላይ ሙያዊ ስልጠና ከሌለህ እጅን ማጠፍ ብቻ ሳይሆን 'መቁረጥም' ጥሩ ነው [ከሚፈትንህ]። ቤተክርስቲያንማ ከላይ ያሉት ሁሉ ለሰው ልጆችም ጥቅም በባለሙያዎች ሲሠሩ ፍቅርን፥ አንዱ ለአንዱ አስፈላጊ መሆኑን፣ መታዘዝን፣ ጽድቅን፥ የሰው ልጆች እኩልነትን በመኖርም በመለፈፍም መርህ እንዲሆናቸው ታስተምራለች።

የመድረክ ተረኞች አይነግሩህም ብዬ ነው። እህእ! ዶሚኒየን ስነመለኮት የቤተክርስቲያንን ማንነትና ተልዕኮ ጭቃ ቀቢ ነው። ባ'ላት ሁለት እግር ሰባት የተራራ አናት ካ'ልረገጥሽ እያለ የሚያንጠራውዝ ነው።

አዝናለሁ፦ በምንም ርዕስ ይናገር እዚህ የቅዠት ማዕቀፍ ውስጥ ወንድሜን ሳየው። ለነገሩ መንገድ ጠራጊዎቹ ብዙ ናቸው። አንድ የተጠና ጥናት ነበር - እርሱን ከሼልፍ ማውጣት ሳያስፈልግ አይቀርም።

ተገኝ ሙሉጌታ
609 views10:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-07 11:17:43 “የዳንኤል ጸሎቶች”

ዳንኤል በባቢሎን ሠራዊት በተማረከበት ወቅት አፍላ ታዳጊ ነበር። በግዞት ከተወሰደ በኋላ እጅግ ጨካኝና ክፉ ለሆነ ንጉሥ ባሪያ ሆኖ እንዲያገለግል ተገደደ። በአጋንንታዊ ሃይማኖቶች፣ በጣዖት አምልኮ፣ በቤተ-መንግሥት ባለሟሎች ተንኮል ተከብቦ የነበረ ቢሆንም በአምላኩ ላይ ከፍተኛ እምነት ስለነበረው ስለ ሕዝቡ ውርደት አጥብቆ ይጸልይ ነበር። ስለዚህም ከፍተኛ ተጽዕኖ ፈጣሪና የመሪዎች አማካሪ ሆኗል!

ከትንቢተ ዳንኤል መጽሐፍ ተግባራዊ ፋይዳዎች አንዱ፥ እንዴት የአገር ዕጣ ፈንታ በተራው ሕዝብ ቊርጠኛ ጸሎት ሊቀየር እንደሚችል ማሳየቱ ነው። በግዞት አገር የሚኖር አንድ ተራ ባሪያ አጥብቆ ሲጸልይና፤ እግዚአብሔርም ለሕዝቡ ሲፈርድ ፣ የራሱን መልካም ዕቅድ ሊያስፈጽም ገዢዎችንና መንግሥታትን ሲሾምና ሲሽር እንመለከታለንና።

በመጽሐፉ ውስጥ የሚገኙት ሁለቱ የዳንኤል ጸሎቶች በችግር ጊዜ ለአገር እንዴት መጸለይ እንዳለብን ጠቃሚ ምክሮችን ያዘሉ ናቸው። ምዕራፍ 2፣20-23 እና ምዕራፍ 9፣ 3-19።

ዳንኤል በአምላኩ ፊት ቀርቦ የሕዝቡን ኅጢአት ሲናዘዝ ሁሌም ራሱን ያካትታል። “ኅጢአት ሠርተናል” ይላል። ከችግሩ መንስዔነት ራሱን ነጻ አድርጎ ወደ ሌላው ጣት አይቀስርም። በበደላቸውም ምክንያት የእግዚአብሔር ፍርድ እንደሚገባቸውም (deserve እንደሚያደርጉ) ያምናል። ለሕዝቡ ያለው ብቸኛ ተስፋ እግዚአብሔር መሆኑን በማወጅ ምሕረትና ይቅርታን ይለምናል!

ጸሎቱ በእግዚአብሔር ክብር መመለስ ላይ ያጠነጥናል እንጂ ራስ ተኮር (self-centered) ዓላማ የለውም! “ልመናችንን የምናቀርበው ስለ ጽድቃችን ሳይሆን፣ ስለ ታላቅ ምሕረትህ ነው” (9፥18) ብሎ በትህትና ልብ ይቀርባል። የእርሱን መልካምነት፣ ታላቅነት እና ነገር ሁሉ በቊጥጥሩ ሥር እንደሆነ እውቅና ይሰጣል። በኅጢአት ወይም በክፉ ሰዎች ሤራ ወይም በጨካኝ ገዥዎች ድንፋታ ላይ ከማተኮር ይልቅ በአምላኩ ታላቅነትና በጎነት መደገፍን ይመርጣል!

“ጥበብና ኀይል የእርሱ ነውና፣ የእግዚአብሔር ስም ከዘላለም እስከ ዘላለም ይባረክ። ጊዜንና ወቅትን ይለውጣል፤ነገሥታትን በዙፋን ያስቀምጣል፣ ደግሞም ያወርዳቸዋል፤ ጥበብን ለጠቢባን፣ ዕውቀትንም ለሚያስተውሉ ይሰጣል።” (2፥ 20-21)

አገር በችግር አዘቅት ውስጥ ስትገባ ቅዱሳን ብዙ ዓይነት ምላሽ ሊሰጡ ይችላሉ። አንድም [እንደ ዳንኤል] እግዚአብሔር የሚያየውን ዐይተው ልባቸውን እና ሀሳባቸውን ከእርሱ ጋር ያስተካክላሉ፤ ወይም በሁኔታዎች ትርምስምስ ውስጥ ተውጠው ጥርጣሬ ልባቸውን እንዲቈጣጠር ይፈቅዳሉ። አንዳንድ ምስኪኖች ደግሞ ችግሩን እንደሌለ አድርገው በመቊጠር በክህደት (denial) ቅዠት ውስጥ ይዳክራሉ። (መቼስ ይኼኛው አያድርስ ነው!)

ባጠቃላይ ከዳንኤል ሕይወትና ጸሎት የምንማረው፥ እግዚአብሔር በአገራትና በመንግሥታት ጉዳይ ላይ የበላይ ንጉሥ እንደሆነ፣ ገዥዎችን ለፈለገው ዓላማ እንደሚጠቀምና፣ እርሱ ሁልጊዜ በሥራ ላይ ስለሆነ ቅዱሳን ሳይደናገጡ በጸሎት መትጋት እንዳለባቸው ነው!

ስለዚህ፥ በዚህ ወቅት ስለ አገራችን የተወሳሰበ ፈተናና ስለ ሕዝቦቿ አሳዛኝ ጒስቊልና በየጓዳው የምትጸልዩ ቅዱሳን፥ በሚታየው ነገር ፈጽሞ ተስፋ አትቊረጡ!! እግዚአብሔር ከተሰበረ ልብ የሚፈልቅ እውነተኛ ጸሎትን የሚሰማ ፥ እንዲሁም “ከሚወዱትና ትእዛዙን ከሚፈጽሙ ሁሉ ጋር የፍቅር ቃል ኪዳኑን የሚጠብቅ” የዳንኤል አምላክ ነው!

ፍጹማን ግርማ
582 views08:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 11:44:15
መሥዋዕትን ብትወድ ኖሮ ባቀረብሁልህ ነበር፤ የሚቃጠል መሥዋዕትም ደስ አያሰኝህም። እግዚአብሔር የሚቀበለው መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ የተሰበረውንና የተዋረደውን ልብ አትንቅም።
መዝሙር 51:16-17
647 views08:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 14:13:02
የፆምና የምልጃ ጸሎት!

" ...አንተ ፊቴን እሹት ባልህ ጊዜ፡— አቤቱ፥ ፊትህን እሻለሁ ልቤ አንተን አለ።" መዝ 27:8

ሐምሌ 30፣ 2014 ዓ/ም -- የፊታችን ቅዳሜ

ከጠዋቱ 3:00 እስከ 11:00 ድረስ

ካዛንቺስ ኡራኤል መካነ ኢየሱስ (ልቤ ፋና ትምህርት ቤት ጀርባ ወይም የህይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን ዋና ጽህፈት ቤት አጠገብ)
962 viewsedited  11:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 10:01:55

163 views07:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 18:12:35
አቤቱ ሁሉን ቻይ የሆንህ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ፤ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች፣ በተለይም በቄለም ወለጋ፣ በምዕራብ እና ምሥራቅ ወለጋ እጅግ ዘግናኝ በሆነ መንገድ በተደጋጋሚ በኦነግ ሸኔ ሠይጣናዊ ጭከና በግፍ በተገደሉት፣ የአካል ጉዳትና ዘረፋ በደረሰባቸውና በተሰደዱት ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ሰቆቃ ምክንያት ልባችን በሐዘን እጅግ ተሰብሯል። በትግራይ፣ በአማራ፣ በአፋር፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ እንዲሁም በተለያዩ ክልሎች ባለው የሕዝባችን መከራና ሰቆቃ ልባችን ባለማቋረጥ ይደማል። አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ፤ ካልንበት ጨለማ ልታወጣን የምትችለው አንተ ብቻ ነህ፤ ምሕረትህ አያልቅምና ስማን፤ እንደ ርኅራኄም ብዛት መከራችንን አብቃ።

ልባቸው ለተሰበረ ቅርብ የሆነኸው የመጽናናት አምላክ ሆይ፤ ሐዘን የጐዳችውን ሁሉ አጽናና፤ ለተፈናቀሉትን እረኛ ሁን። ምድራችን በጽኑ ታማለች፣ አቤቱ ፈውስህ ፍጥኖ ያግኛት። በጦርነት ሐዘን የደረሰባቸውን፤ ንብረታቸው የወደመባቸውን፤ በአሰቃቂ መንገድ በመደፈራቸው የአካልና የሥነ ልቡና ስብራት የገጠማቸውን፣ በማያልቀው ቸርነትህ አስብ። በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ራብ ሳቢያ በሞት ጥላ ውስጥ ያሉትን ንጹሐንን በተለይም አረጋውያንን፣ ሕሙማን፣ ሕጻናትንና እናቶቻችንን አስብ። አቤቱ ለዑል ሆይ፤ በየትኛውም ጐራ ካሉ በተለይም በመንግሥት ጥላ ሥር ከተሰወሩ ክፉዎች ታደገን። ግፍ ሲበዛ፣ ፍትሕ ሲጣስና ዐመፅ በጹሐን ላይ ካራውን ሲያሳርፍ እያዩ ዝምታን ከመረጡ የሃይማኖትና የሕዝብ መሪዎች እጅም አስጥለን። ልዑል ሆይ፤ ጦርነትን ሻር፣ መውጫውም ከጠፋብን የዐመፅ ዑደት አውጣን። ስለ ጽድቃችን ሳይሆን፣ ስለብዙ ምሕረትህ ስትል የሰላምን ዝናብም ላክልን።

አሜን!

ግርማ በቀለ (ዶ/ር)
283 views15:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 06:36:48 “እንግዲህ የሰማዩ አባታችሁ ፍጹም እንደ ሆነ እናንተም ፍጹማን ሁኑ።” (ማ​ቴ​ዎስ 5:48 )

ስለ ተራራው ስብከት በአንድ ቤተ ክርስቲያን በማስተማር ላይ እገኛለሁ። በመጀመሪያ፣ ሁልጊዜም እንደማደርገው፣ ስብከቱን እንዴት ልንቀርበውና ልናነበው እንደሚገባ ሥነ-አፈታታዊ አያያዙንና ለስብከቱም ተግባራዊነት ያለውን ፋይዳ በማስገንዘብ ጀምሬያለሁ። ካነሳኋቸው ነጥቦች አንዱ፣ ‹የተራራው ስብከት ከሰባኪው ማንነት› እንደማይለይ ነው። ስብከቱ የሰባኪውን መለኮታዊ ሥልጣን ያጎላልና። ሕዝቡ በትምህርቱ ተደነቁ፥ ምክንያቱም «እንደ ባለ ሥልጣን ያስተምራቸው ነበርና» ነው (7:28-8:1)።

በዚህ ነጥብ ሥር የማነሳው ኢየሱስ የስብከቱ «እውነተኛ ሞዴል» እንደሆነ ነው። በተራራው ስብከት ላይ የተካተቱት መመሪያዎችንና ተምኔታዊ እሴቶችን ኢየሱስ ተላብሶት (ማቴዎስ በወንጌሉ በሌላ ሥፍራ ላይ) ያሳየናል። በ5:5 ላይ "የዋሆች ብፁዓን ናቸው" የሚለው ሰባኪ በማቴ. 11፡29 ላይ "እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝ" እያለ «ወደ እኔ ኑ» ብሎ ሲጣራ ይደመጣል። ይኽም፣ የየዋኅነት ሞዴል ኢየሱስ መሆኑ ነው። ስትጸልዩ «እንዲህ ብላችሁ ጸልዩ» ብሎ ያስተማረው እርሱ በጸሎት የሚተጋውን (ማቴ 14፡23)፣ በጌቴሴማኒም የሚቃትተውን ሰው እያሳየን ነው (26፡36-46)። ሰባኪው ስብከቱን ተላብሶታል።

የልጠፋዬ ዓላማ ግን ከላይ ያሰፈርኩት አይደለም። ንጽጽሩን ይዤ በ6፡19-34 ላይ ስመጣ ግን፣ «ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ» (6፡25-34)፣ ብሎ የሚናገረው ሰባኪ፣ "የእኔ" የሚለው ቤት እንኳ የሌለው ተንከራታች ሰባኪ ነበር "ለቀበሮዎች ጉድጓድ ለሰማይም ወፎች መሳፈሪያ አላቸው፥ ለሰው ልጅ ግን ራሱን የሚያስጠጋበት የለውም" (8፡20)። ይኽ ንጽጽር ልቤን እጅጉን ነካው። ገሰጸኝ። ሰባኪው ስብከቱን የኖረ ሰባኪ ነበር። ከእኛ እጅግ በባሰ አውድ ሥር እያለ ነበር የአባቱን ፍጹም ፈቃድ የፈጸመው።

ብዙዎቻችን የምንበላው ሳይጎድለንን የምንኖርበት መጠለያ ሳናጣ፣ የነገ ኑሮ ጭንቀት ኢየሱስን ከመከተል ሲያጎድለን እንመለከታለን። ሰባኪው "ልብህ ባለበት መዝገብህ በዚያ ይሆናል" ሲለን እኮ (6፡19) አፍቅሮተ ንዋይ ልባችንን ሊቆጣጠር (6፡20-21)፣ አይናችንን ሊያሳውር (6፡23) እና ጉልበታችንን ባሪያ አድርጎ ሊያስገዛው (6:24) እንደሚችል ስላወቀ ነው። ስለዚህ በሁሉም ረገድ፣ የተራራው ስብከት ሰባኪ የስብከቱም ሞዴል ነው።

ኢየሱስን የመምሰል ጥሪ (Imitatio-Christi) ምን እንደሚመስል ማወቅ ከፈለግን (5:48) ጠጋ ብለን የተራራውን ስብከት እናጥና። ግን ደግሞ በማቴዎስ ወንጌል ውስጥ፣ ይህ ስብከት ከአምስቱ ስብከቶች መካክል አንዱ እንደመሆኑ ሌልቹንም እንዲሁ ልንመለከት ይገባል።

በዚህ ምሳሌ ልደምድም። አግናጥዮስ የተሰኘ የቤተ ክርስቲያን መሪ፣ ሞት ወደ ሚጠብቀው ወደ ሮም ከተማ በመንገድ ላይ ሳለ ለፊላደልፊያ ሰዎች እንዲህ እያለ ይጽፋለቸዋል፦

«እርሱ አባቱን እንደመሰለ፥ እናንተም ኢየሱስ ክርስቶስን የምትመስሉ ሁኑ»
(የአንጾኪያው አግናጥዮስ መልእክት ወደ ፊላደልፊያ ሰዎች 7.2)

"የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።" (ዕብ 12:2)

ሳምሶን ጥላሁን
616 views03:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 21:04:19 ለሐረር እና ድሬዳዋ አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት መሪዎች

የጌታ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ!

በጌታ የተወደዳችሁ ሆይ በብዙ ትጋት እና መሰጠት ለእግዚአብሔር መንግሥት እየደከማችሁ ስላላችሁ ስለ እናንተ አምላኬን እግዚአብሔርን እባርካለሁ፡፡ የምስራቁ የአገራችን ክፍል ለወንጌል አገልግሎት እጅግ ከባድ እንደሆነ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ቢሆንም የእግዚአብሔር መንግሥት እንዲሰፋ እያደረጋችሁ ያላችሁት ተጋድሎ በእውነቱ ድንቅ ነው፡፡ በእናንተም እየደከመ ሰላለው የጌታ ጸጋ ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን!

ይህን መልእክት እንድጽፍላችሁ ያነሳሳኝ ዐቢይ ምክንያት፣ እንደምታውቁት ከጊዜ ወደ ጊዜ በቤተክርስቲያን ሾልከው የሚገቡ የስሕተት ትምህርቶች ቤተክርስቲያንን እያናወጧት ይገኛሉ፡፡ በየጊዜው የሚገለጡ የስሕተት ትምህርቶች ያሉ እና የሚኖሩ በመሆናቸው፣ እንደ ብርቅ ነገር አንቆጥራቸውም፡፡

ይልቁንም ከጊዜ ወደ ጊዜ እንዲህ ያሉትን ጉዳዮች ቸል የሚሉ መሪዎች የመብዛታቸው ጉዳይ የበለጠው አሳሳቢ ነገር ነው፡፡ መሪዎች መሪ የሆኑበት ዋና ነገር መንጋቸውን ከተኩላ ለመጠበቅም እንደሆነ ቃለ እግዚአብሔር በስፋት ይናገራል፡፡ ይህንን ጉዳይ ቸል እንዳይሉ በማሰብም ሐዋርያው ጳውሎስ የኤፌሶንን መሪዎች በእንባ አሳስቧል፡፡

ዛሬ ላይ ማንም የነሸጠው ተነስቶ ቤተክርስቲያን ሊያቋቁም የመቻሉ ሐቅ ከእናንተ የተሰወረ አይደለም፡፡ እንዲህ ያሉ ባለ ቤተክስቲያናት ደግሞ ለእውነተኛው አስተምህሮ እና ክርስትና ግድ የሚላቸው አይደሉም፡፡ ትርፍ የሚያገኙ እስከመሰላቸው ድረስ ማንንም በመድረካቸው ሊያቆሙና ወደ ከተሞቻችሁ ሊያሾልኩ ይችላሉ፡፡ እንዲህ ያለውን መርዘኛ አካሄድ ቸል ብሎ መመለከት ለእውነተኞቹ መሪዎች ልከኛ አካሄድ ሊሆን አይችልም፡፡

በመሆኑም ሕዝባችሁ በእውነተኛ ትምህርት እንዲቆምና የሚተባበረውን እና የማይተባበረውን ማኅበር አጥብቆ ማስገንዘብ ይገባችኋል፡፡ በተጠራበት ሁሉ የሚገኝ ምእመን ሊኖረን ጨርሶውኑ አይገባም፡፡ እንደ ወንጌል እውነት የሆነውን ኅብረት እንደምንደግፍ ሁሉ ከወንጌል እውነት ያፈነገጠውን ሐሳዊ ኅብረት ደግሞ አጥብቀን እንቃወማለን፡፡
ከዚህ በፊት የሆሳዕና አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት በአንዱ ሐሳዊ ነባይ ላይ የወሰዱት ቅዱስ አቋም በየትም ቦታ ሊተገበር የሚገባው በጎ ተመክሮ ነው፡፡

ከወንጌላውያን አስተምህሮ ጋር ስምምነት የሌለለው ነባይ ወደ ከተማችሁ ሊመጣ እንደሆነ መለከት እየተነፋ ነው፡፡ የጠሩት ሰዎች መጥራት፣ ተጠሪውም መምጣት መብታቸው ሊሆን ይችላል፡፡ እናንተ ደግሞ እግዚአብሔር የሰጣችሁን መንጋ መጠበቅ ግዴታችሁ ነው፡፡ ስለዚህም ለምታገለግሉት ማኅበረ ምእመን አቋማችሁ በይፋ ታሳውቁ ዘንድ ልመናዬን አቀርባለሁ፡፡

“በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።” ሥራ 20፡28

መጋቢ ስንታየሁ በቀለ
453 views18:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 06:14:36 ቅዱስ ቃሉ በዘመናት መካከል በሁለት መልኩ ተመስክሮለታል። (1) ራሱን ያስመሰክራል (self-authenticating)፣ (2) ስለ ራሱ ይመሰክራል (self-attestation)። ይህ መጽሐፍ “የእግዚአብሔር ቃል” ስለመሆኑ የትኛውም ኮሚቴ ይሁን የአበው ጉባኤ አላጸደቀም። ሰዎች ለእነዚህ ሰነዶች ሥልጣን እውቅናን ሰጡ እንጂ እጃቸውን በመጫን “አልቀቧቸውም”። እነዚህ ሰነዶች በዘመናት መካከል ራሳቸውን በአድማጮቻቸው ህይወት አስመስክረዋል። በተጨማሪም፣ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ራሱ ምንነት፣ ባህርይና ዐላማ እንዲሁ ምስክርነት ይሰጠናል። በዚህ ሁሉ፣ የእኛ እድል ፈንታና ሚና በመጀመሪያ አድማጪነት ነው። አነባበባችን ይሁን ግንዛቤያችን መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ራሱ በሚመሰክረው ባህርይ ላይ የተመሰረት ሊሆን ይገባል። አሁንም በራስ ዓይን ጠቢብ የመሆን መብታችን እንድተጠበቀ ሆኖ።
ስለዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ባህርይ ምን ይመስላል? መምህሬ የነበረው ስቲቭ ዌለም በጥሩ መልኩ እንዲህ ብሎ ገልጾታል።

መጽሐፍ ቅዱስ፣ በቅዱሳት ሰዎች አማካኝነትና በመንፈስ ቅዱስ ምሪት የተሰጠ አስተርእዮተ-እግዚአብሔር (ግላጤ-መለኮት) ሲሆን፣ ይኽም፦ አንድ ወጥ የሆነ፣ በክርስቶስ ላይ ያተኮረና በድነት-ታሪክ ውስጥ ተዘርግቶ ደረጃ በደረጃ እያደገ የመጣ ጽሑፋዊ መገለጥ ወይም የእግዚአብሔር ቃል ነው። [Scripture is the word-act revelation of the triune God through human authors, centered in Christ, which comes to us progressively in redemptive-history” (Stephen J. Wellum)

ይቀጥላል...

ሳምሶን ጥላሁን
445 views03:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 06:14:36 በተደጋጋሚ ሲሰበክ የማደምጠው “ይሁዳ ይቅደም!” የሚል ርእስ ያለውና በመሳፍንት 20:18 ላይ የተመሠረተ አንድ ስብከት ነበር። ይህ ለናሙና ያኽል እንጂ ይህን መሰል ስብከቶችን ማራባት በቀላሉ ይቻላል። የስብከቱ ድምዳሜ፣ “ይሁዳ ይቅደም ማለት ምስጋና ይቅደም ማለት ነው” የሚል ነው። ምክንያቱም የይሁዳ ስም ትርጉም “ምስጋና” ስለሆነ። ስለዚህ በችግሮቻችን ሁሉ መቅደም ያለበት “ምስጋና ነው” እያለ፣ ሰባኪው ጉባኤውን እያስጮኸ ይሰብካል። ግን የመሳፍንቱ ንባብ «ይሁዳ ይቅደም» ያለበትን ዐውደ ምንባባዊ ምክንያት ግምት ውስጥ አላስገባም። መሳፍንት 20፣ ከምስጋና ጋር አንዳች ግንኙነት የለውም። የሰባኪው ተቀዳሚ ትኩረት፣ የቃሉን ድምጽ መስማት ላይ ሳይሆን፣ “መታዘዝ” ላይ ነው። ወይም ለሰባኪው ዋናው ነገር ስብከቱን መስበኩ ላይና ሰዎችን መጥቀሙ ነው። « የትም ፍጭው ዱቄቱን አምጭው» ነው ጥበቡ። ይኽም፣ ስብከቱ የቅዱስ ቃሉን ዘመን መጠቅ መልእክት ፈልቅቆና አውጥቶ የህያው እግዚአብሔርን ድምጽ ለእግዚአብሔር ሕዝብ ማሰማት ሳይሆን፣ ስብከቱ ጀምሮ የሚያበቃው ስብከቱ ላይ ነው። ምን ልስበክ ብሎ ስብከት አቀናብሮ፣ ስብከቱን ሰብኮ፣ ሰብከቱን ጨረሰ። ሰዎችን እስከጠቀመ፣ “እሰየኹ” ባይ ነው። ስለዚህ፣ ጀምሮ እስኪያልቅ “ስብከቱ” የሰባኪው ምርት ውጤት ነው። ሰባኪው ለመናገር እንጂ ለማዳመጥ ጊዜ የለውም። የስብከቱ ይዘትና ስብከቱ የተመሠረተበት የምንባቡ ትርታ አይገናኙም። ትህትና ግን ጥበብ ናት። አስቀድማ፣ ለመስማት የቸኮለች፣ ቃሉን ለማዳመጥም የምትንቀጠቀጥ ናት (ኢሳ 66:1-2)። በራስ የበቃች፣ «እኔ ሁሉን አውቃለሁ፣ ማንንም አላዳምጥ» አትልም።

በዚህ ሁሉ፣ ጥበብ ያሏቸው የሚመስሉ ንግግሮችና ልምምዶች አሉን። ይህ ዓይነቱ ጥበብ ግን «በራስ-ዓይን ጠቢብ» ከመሆን ያላለፈ ጥበብ ነው። ከእነዚህ መካከል አንዱ “ዋናው መጽሐፍ ቅዱስን መታዘዝ ነው” የሚል አነጋገር ነው። ምርጫ እንደተሰጠን ነገር። ሲጀመር፣ ማናችንም ብንሆን በንግግር ይሁን በድርጊት መጽሐፍ ቅዱስን ከመታዘዝ ዳተኛ እንድንሆን የሚያደርግ ጥበብ ሁሉ ውግዝ “አናቴማ” ነው። ይህን ዓይነቱን ሰው ኢየሱስ በመንግሥተ ሰማያት “ታናሽ” እንደሚባል ነግሮናል (ማቴ 5:17-20)። ይህ ትልቅ ኹነኔ መሆኑን አንዘንጋ። ስለዚህ ጉዳዩ፣ «መታዘዝ ወይስ አለመታዘዝ» እንደሆነ አድርጎ ማቅረብ አሁንም በራሳችን ዓይን ጠቢብ መሆን ነው። ምናልባት፣ “የመታዘዝ ጉዳይ” በተግባር ሊካዳ ይችል ይሆናል እንጂ በአማራጭ የለሽነቱስ እንስማማለን። ስለዚህ ግልጽ እንሁን። መታዘዝን የሚያኮሰምን የትኛውም የረቀቀ የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ፣ ሄንድርክሰን እንዳለው፣ “እንደ ጽንስ-ውርጃ” ነው። ህይወት ያለው ነገር ጀምሮ እንኳ ቢሆን፣ ፋይዳ የለውም። ሒደቱ ከንባብ ወደ መገዛት አላመጣንምና። ስለዚህ ምርጫው በመታዘዝና ባለመታዘዝ መካከል አይደለም። ይህ ልምምዳችንን ለማጽድቅ የምናደርገው መፍጨርጨር ነው። ምርጫው አልቀረበልንም። ሰማያዊቷ ጥበብ፣ በመጀመሪያ ታዳምጣለች።

ሁለተኛው የአዳንዶች “በራስ ዓይን ጥበብ» ደግሞ ይህንን ይመስላል። “ዋናው መንፈስ ቅዱስ የሚሰጥህ መረዳት ነው” የሚል ነው። አሁንም ማናችንም «ቃሉን በጥንቃቄ እናንብብ» ስንል፣ የመንፈስ ቅዱስን ሚና እንዝረፍ እያለን አይደለም። አሁንም ያልተሰጠንን ምርጫ እየመረጥን ነው። እንደ እውነቱ ከሆነ፣ “እኔ ልንበርከክ መንፈስ ቅዱስ የቤት ሥራዬን ሥራልኝ” እያልክ መሆኑን አትዘንጋ። መንፈስ ቅዱስ የልቡና መብራትን ይሰጣል። መጽሐፍ ቅዱስ ከ1500 ዓመታት በላይ የፈጀ የመንፈስ ቅዱስ የሥራ ውጤት ነው። የጻፈው እርሱ ነው። የልብ መብራት የሚሰጠው እርሱ ነው። እንድንታዘዝ የሚወቅሰንና ጉልበት የሚሰጠን እርሱ ነው። ነገር ግን፣ መንፈስ ቅዱስ መጽሐፍ ቅዱስን በጥንቃቄ አያነብልኝም። በዘመናት መካከል የበሰለ ምግብ አቅርቦልን ሳለ፣ «ኦ መንፈስ ቅዱስ ሆይ፣ እጄን ይዘህ፣ እንጀራውን አድቦልቡልና በአፍ በአፌ አጉርሰኝ» እያልን ነው። መንፈስ ቅዱስ ስንፍናችንን አይሞላም። የታዘዝነው፣ «እንደተመሰከረለት ሠራተኛ» እንድንተጋ ነው (2 ጢሞ 2:15)። ወይም መንፈስ ቅዱስ "ሹክ" እያለ “አስቀድሞ ያልተናገረውን” አዲስ ፍቺ “በግልህ” አይፈጥርልህም። ኢየሱስ “አላነበባችሁምን?”እያለ መሞገቱ፣ “ነቢያት የተናገሩትን ከማመን” በመዘግየታቸው ደቀ መዛሙርቱን መገሰጹ፣ አስቀድሞ በጽሑፉ ውስጥ የተንጸባረቀ፣ ዘመንና ሥፍራ የማይለውጠው ነባራዊ መልእክት እንዳለ ያስረዳል። ጴጥሮስም ማንም በዘፈቀደ ሊተረጉም እንደማይችል ያስጠነቀቀን ለዚህ ነው (2 ጴጥ 1:20-21)።

በመጨረሻም፣ መንፈስ ቅዱስ የሚሰጠን የውስጥ መገለጥና ብርሃን ቅጽበታዊ አይደለም። እኛ ለመረዳት ከምናደርገው ጥረት ጋር ትይዩ ነው። "እኔ የምለውን ልብ በል (ተመልከት)፣ ጌታም በነገር ሁሉ ማስተዋልን ይሰጥሃል" (2 ጢሞ 2:7)። ልብ የማለት ድርሻ የእኛ ነው፤ ማስተዋልን ግን የሚሰጥ ጌታ ነው፡፡ ሁለቱ ይጎራረሳሉ እንጂ አይጣሉም፡፡ ወይም ምሳሌ 2፡1-4 ላይ "ጆሮህን ጥበብን እንዲያደምጥ...ልብህን ወደ ማስተዋል [ብታዘነብል]....ረቂቅን እውቀት ብትጠራት...እንደ ብር ብትፈልጋት...እንደተቀበረ ገንዘብ ብትፈልጋት" ይልና በቁ.5-6 ላይ እግዚአብሔር "ጥበብን ይሰጣል" ይላል። አሁንም ቅጽበታዊ አይደለም፣ አያችሁ። የመንፈስ ቅዱስ የአብርሆትና የመገለጥ ሚና ከእኛ ድካምና ጥረት ጋር አይጋጭም። ይልቁንስ፣ ልክ እንደ ጓንትና እጅ አብረው የሚሔዱ ናቸው። ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ የስንፍናችን ማሳበቢያ አይደለም። ይልቁንስ ያለ መንፈስ ቅዱስ ብርሃን ርቀን መሔድ አንችልም። የእርሱ ብርሃን ወደ ሕይወታችን ሲመጣ ግን ያተጋል፤ ትሁት ያደርጋል፤ እንድንማር ይጠራናል።

መዘንጋት የሌለበት፡ ይህ መጽሐፍ የብዙ ቅዱሳን ሰዎች ላብና ደም ተቀላቅሎ የተጻፈው ነው። ከእኛ በጥቂቱ እንደ ቤርያ ሰዎች “ነውን?” እያልን በጨለማ እንደሚበራ ብርሃን በጥንቃቄ መያዝ ይጠበቅብናል። ይህን የምለው፣ ራሴን ጨምሮ ብዙዎቻችን በራሳችን ዓይን ጠቢባ ነን። የጎደለንን፣ “ጎድሎኛል ጌታዬ ጉድለቴን እርዳ” ከማለት ይልቅ፣ “አያስፈልገኝም” ማለት ይቀለናል። “አንብበናል፣ እናውቃለን” የምንል እንኳ በአገልግሎታችን ክደነዋል። እናውቃለን የምንለውን በአገልግሎት ፍሬ አይገለጥም፡፡ ፋይዳው ምን ላይ ነው?

ግን ለምን? ምክንያቱም ከባድ ሥራ ነው። ምክንያቱም ሰው «እንዳያዛጋብን» ስለምንፈራ ነው። አቋራጩ፣ ሰዎች መስማት የሚፈልጉትን ነገር፡ በሚፈልጉበት መንገድ መናገር ነው። ለአንዳንዶቻችን ግን ሳናውቅና ፈልገን ሳይሳካልን የምንፈጽመው ስህተት ነው። አሁንም ግን፣ ይህ ማመካኛ ሊሆን ፈጽሞ አይችልም። “መንገድ ክፈትልኝ” እንበል። ሰማይን ቧጠን ቢሆን እንኳ ክሂሉን እናዳብር። ምርጫው አሁንም አልተሰጠንምና!

ይህ ሁሉ ለምን? ምክንያቱም ከዚህ ሁሉ ድካማችን መጨረሻ፣ ራሴን ይሁን አንባቢዬን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት “አንተ ታማኝ ባርያ” እንድንባል ስለምፈልግ ነው። ሆኖም ግን ጥያቄው ይህ ነው! ለመጽሐፍ ቅዱስ ሥልጣን “እኔና ቤቴ እንገዛለን” የምንል ከሆነ፣ «መጽሐፍ ቅዱስ እንዴት ወደ እኛ መጣ? እግዚአብሔር ቃሉን እንዴት ሰጠን?» የሚሉትን የቅርጽ ጥያቄዎችንም ጠንቅቀን ማዳመጥ የግድ ነው። የቅዱስ ቃሉ ግንዛቤ፣ ይሁን ስብከታችን ቃሉ ወደ እኛ የመጣበትን እውነታ ግምት ውስጥ ማስገባት አለበት። አሊያ ከጅምሩ ፎርሿል። አሁንም፣ በራሳችን ዓይን ጠቢብ ለመሆን ካልወሰንን በስተቀር።
407 views03:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ