Get Mystery Box with random crypto!

ነገረ ወንጌላውያን

የቴሌግራም ቻናል አርማ negere_evangelical — ነገረ ወንጌላውያን
የቴሌግራም ቻናል አርማ negere_evangelical — ነገረ ወንጌላውያን
የሰርጥ አድራሻ: @negere_evangelical
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.86K
የሰርጥ መግለጫ

በወንጌላውያን አማኞች ዘንድ የሚፃፉ ፅሁፎች፣ ዘገባዎችና ዜናዎች ይቀርባሉ! ትምህርቶች፣ መረጃዎችና ምካቴ እምነቶች በዚህ ቻናል ይስተናገዳሉ! በተለያዮ ሶሻል ሚዲያዎች የሚገኙ ፀሐፊያን የሚፅፉቸው ፅሁፎችን እናጋራለን።

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-06-27 22:14:38 የከበሬታ ነገር!

በአገልግሎት ምክንያት ያገኘኋት አንዲት የባለቤተስኪያን ሚስት ጋር እናወራለን፡፡ ግንኙነታችን ገራም እና ደኅነኛ ስለነበር፣ በጥሩ የወዳጅት መንፈስ እናወራለን፡፡ በእኔ በኩል የመቀራረባችን ምክንያት እንደው አንዳንድ ወጣ ወጣ ያሉ ነገሮችን በመቀራረብ መግራት ይቻል እንደሁ ከሚል የዋሕነት ነበር፡፡

ልጅቱ አብዝታ አገልጋዮች ከበሬታ ይገባቸዋል የሚል ሙግት ታነሳለች፡፡ ከበሬታውም በልዩ ልዩ መንገድ መገለጥ አለበት ባይ ነች፡፡ ለምሳሌ የተመረጠው እና የተሻለው ነገር ሁሉ ለአገልጋዮች ይገባል፤ የተሻለ መኪና መንዳት፣ በተሻለ ቤት መኖር፣ የተሻለ መብላት፣ መልበስ...
ይሄ ሁሉ መሆኑ የከፋ ባልሆነ፤ ነገር ግን ይህ ሁሉ የሚሆነው በሕዝብ ጫንቃ መሆኑ ነው አሳዛኙ ትራጀዲ፡፡ ይህን መሳዮቹ አገልጋዮች ግባቸው ይኸው ስለሆነ ይህንን ለማሳካት ሁሉን ነገር ከዚህ አንጻር ይቃኙታል፡፡ ስብከቱ፣ መዝሙሩ፣ መዋቅሩ ሁሉ ከዚህ አንጻር ይገነባል፡፡

የምእመናን ስኬትም ይሁን ውድቀት ለ“አገልጋዮቹ” ካለ ከበሬታ ጋር እንደሚያያዝ አድምተው ይለፍፋሉ፡፡ ምእመናን ወጥተው የሚገቡት በእነሱ ጥላ ከለላነት እንደሆነ አድርገው ያሳምናሉ፤ ቡራኬያቸው የምእመናን ወጥቶ መግቢያ ቀለብ እንደሆነ በየምእመኖቻቸው ልብ ውስጥ አጽንተዋል፡፡

ራሳቸውን በየተከታዮቻቸው ልብ ውስጥ አግዝፈው፣ ዙፋናቸውን ዘርግተዋል፡፡ “ከመረቅሁሁ” የሚል ማበራቻ ብቻ ሳይሆን፣ “ከረገምሁህ” የሚል ማስፈራሪያም አላቸው፡፡ ምእመናን መጋቢው፣ ነቢዩ ወይም ሐዋርያው እንዳይረግመው /ቃል እንዳያወጣበት ፀጥ እና ዝግ ብሎ ይኖራል (በ“አገልጋዩ” ፊት) እግዚአብሔርን በቅጡ አያውቀውም፤ ካወቀውም አገልጋይ ተብዬው በሳለለት ልክ እንጂ የመጽሐፉን እግዚአብሔር አያውቀውም፡፡ በክርስቶስ ነጻ እንደወጣ ሰው ሳይኾን፣ ልክ በአንድ ዓይነት ባዕድ አምልኮ እንደተተበተበ ሰው ዓይነት ድንብርብሩ እየወጣ ይኖራል፡፡ የእርሱ እግዚአብሔር ሁልጊዜ በእርሱ “አገልጋይ” በኩል ብቻ የሚፈስ ነው፡፡ አገልጋይ ተብዬዎቹም ምእመናቸው ከዚህ እንቅልፉ እንዲነቃ አይፈልጉም፡፡ ቅምጥል ኑሯቸውን ባንቀላፉ ምእመናን ላይ መስርተዋል፡፡

የቸርቻቸውን ዙሪያ በገዛ ፎቷቸው ያጥራሉ፤ ቢሮው እና መድረኮቻቸው ሳይቀር በተንቆጠቆጡ ምስሎቻቸው ይሞላሉ፡፡ አንዳንዶቹ ሚስት እና ልጆቻቸውን ሳይቀር ቸርች ባሉት ይዞታቸው ላይ ይሰቅላሉ፡፡ አንዳንዶቹም ምስሎቻቸውን አትመው በየዋሌቱ እንዲያዝ ያድላሉ፡፡ በዚህም ያለ ልክ ተንሰራፍተው፣ የጌታን ጌትነት ተጋፍተው በየሰዎቻቸው ላይ ይነግሣሉ፡፡

በዚህም ያን ያነገቡትን የቅንጦት ኑሮ ይኖራሉ፡፡ “ምርጥ ምርጡን ለሕፃናት!” እንደተባለው ዓይነት በምርጥ ምርጡ ይምነሸነሻሉ፡፡ ልዕልናቸውን ያለ ልክ ከፍ አድርገው “መጡ መጡ፤ ገቡ ገቡ” ይባልላቸዋል፡፡ በማንኛውም መንገድ ልዕለ ሰብ እንደሆኑ ያውጃሉ፡፡ ተራ በሚሉት ምእመን ላይ ጢባ ጢቤ ይጫወታሉ፡፡

መቸም መከባበር ክርስቲያናዊ እሴታችን ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያዊነት ትርፉታችንም ነው፡፡ እርስ በርስ ለመከባበርም ደግሞ የቃለ እግዚአብሔር መመሪያ አለን፡፡ ቢሆንም አገልጋዮች በተለየ መንገድ ይደግደግላቸው የሚል መመሪያ ግን ጨርሶውኑ የለንም፡፡

መሪ መምህራችን ጌታ ኢየሱስ አብዝቶ ካስተማራቸው ነገሮች መካከል ስለ ዝቅታ እና ትሕትና ያስተማረውን የሚያህል ያለ አይመስለኝም፡፡ ለተወሰኑ ጊዜያት በእኔ እበልጥ እና በፉክክር መንፈስ ይንገላቱ የነበሩትን ደቀመዛሙርቱን ደጋግሞ ገስጿል፡፡ ማገልግል በራሱ የታችኛውን ስፍራ መምረጥ ነው፡፡ ጌታችን ስለ ራሱ እንኳን ሲናገር “የሰው ልጅ ሊያገለግል፣ ነፍሱንም ስለ ብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም” ብሏል፡፡ በዚህም አገልጋይነት ባርነት መሆኑን አጽንቷል፡፡

ከዚህም ሲያልፍ መምህር እና ጌታ የሆነው እርሱ በእውነተኛ መዋረድ እና ዝቅታ ወገቡን አሸርጦ የደቀ መዛሙርቱን እግር አጥቧል፡፡ ይህም የተወሰኑ ኦኬዥኖች እየጠበቅን ለማስመሰል ድራማ እንድንሠራ ሳይሆን፤ አገልጋይነት የሁልጊዜ የሕይወት ሥርዓታችን እንዲሆን የተሰጠ ትምህርት ነው፡፡

ይህንኑ ፈለግ የተከተሉትም ደቀመዛሙርት ይህንኑ ቅኝት ጠብቀው ነበር ሲያገለግሉ የነበሩት፡፡ አገልግሎታቸውን የገዛ ፍላጎታቸው መሙያ ሲያደርጉ ለአፍታም እንኳ አናይም፡፡ በማንኛውም መንገድ ራሳቸውንም አላሻሻጡም፡፡ በገዛ ቃላቸውም “ክርስቶስ ኢየሱስ ጌታ እንደሆነ እንጂ ራሳችንን አንሰብክም!” ብለው መስክረዋል፡፡ በስማቸው የተቋቋመ ቡድንንም አምርረው ኮንነዋል፡፡ አለፍ ብሎም የተለየ ከበሬታ በተዘጋጀላቸው ወቅትም በመንቀጥቀጥ ልብሳቸውን ቀደዋል፡፡
ግባቸው አንድ እና አንድ ክርስቶስ ኢየሱስ በአገልግሎታቸው እንዲገለጥ እና የሁሉን ሕይወት እንዲወርስ ብቻ ነበር፡፡ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ይህ አገልግሎት የሚጠይቀውን ዋጋ በደስታ ከፈሉ እንጂ፣ ማንንም ዋጋ አላስከፈሉም፤ ሰማይ ሙሉ ዋጋ ይዞ እንደሚጠብቃቸው ግን እርግጠኞች ነበሩ፡፡ በአገልግሎታቸውም በአንዳች ስንኳ ማሰናከያ አልሰጡም ነበር፡፡

ከበሬታን ግብ ያደረገ አገልግሎት ጨርሶውኑ ከጌታ አይደለም፡፡ የእኛ ክብር የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ የከበረ ‘ለታ ብቻ ነው፡፡ በተለያየ መንገድ ራስን ማሻሻጥ በሚመስል መልኩ እርሱን ጋርዳችሁ የደመቃችሁ ሆይ ወዮላችሁ፡፡ ምስሉን እያደበዘዛችሁ፣ ምስላችሁን በየሰዉ ልብ ለማተም የምትታትሩ ሆይ ወዮላችሁ፡፡ እራሳችሁን እያዋደዳችሁ ዙፋናችሁን ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ልትገነቡ ያማራችሁ ሆይ ወዮላችሁ፡፡ የጌታ ቤት ባላችሁት ቸርቻችሁ ላይ ደማቅ ምስላችሁን ሰቅላችሁ ራሳችሁን ያነገሣችሁ ሆይ ወዮላችሁ፡፡
ቀን ሳይጨለም ለልባችሁ ሰው መሆናችሁን ንገሩት፤ ከፍ ብላችሁ በመፋነን ፋንታ የዝቅታን አገልግሎት ምረጡ፡፡ በጌታ ዘንድ ራሱን ከፍ ከፍ ሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳል፤ ራሱንም የሚያዋርድ ከፍ ይላል፡፡
ጆሮ ያለው ይስማ!!

ማገናዘቢያ፡ ማቴ 20÷20-28፣ ሉቃ 14÷11፣ ዮሐ 13÷12-15፣ 2 ቆሮ 4÷5፣ 1 ጴጥ 5÷6

መጋቢ ስንታየሁ በቀለ
490 views19:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 06:52:44

603 views03:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 06:43:23
503 views03:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 06:43:18 እንደ ክርስቲያን ማኅበረሰብ፣ “እግዚአብሔር ለምን ዝም ይላል?” የምንልባቸው አሳሳቢ አገራዊ ጉዳዮች አሉን። በቅዱስ ቃሉ ውስጥ እንደምናነበው፣ እኩይ ተግባር ሕይወታቸውን በድንገት ሲያጨልመው፣ ፍትሕ ሲዛባ፣ ምድር ሁሉ ዐዋቂና ቻይ የሆነ እግዚአብሔር የሚገዛት ሳትመስል ስትቀር፣ “እግዚአብሔር ወዴት ነው? ትድግናውስ ለምን ዘገየ?” የሚሉ የግልና አገራዊ ጥያቄዎችን በማንሣት መልስ ፍለጋ ብዙዎች ታግለዋል።

ዘማሪው አሳፍ፣ ስለእግዚአብሔር ያለውን መረዳትና የራሱን የግል ሕይወትም እንቆቅልሽም ሆነ እስራኤል በወቅቱ የነበረችበን አዘቅትና መከራ ማስታረቅ ስለተቸገረ፦ "እግዚአብሔር ልባቸው ንጹሕ ለሆነ፣ ለእስራኤል እንዴት ቸር ነው! እኔ ግን እግሬ ሊሰናከል፣ አዳልጦኝም ልወድቅ ጥቂት ቀረኝ።" በማለት ስለውስጥ የነፍሱ ትግል ዘምሯል (መዝ 73:1)።

ነቢዩ ዕንባቆም ተመሳሳይ ጥያቄ አስተጋብቷል፤ “አቤቱ እኔ ስጮኽ የማትሰማው እስከ መቼ ነው? “ግፍ በዛ” ብዬ እየጮኽሁ፣ አንተ የማታድነው እስከ መቼ ነው . . . እንዴትስ ግፍ ሲፈጸም ትታገሣለህ? . . . ሕግ ላልቶአል፤ ፍትሕ ድል አይነሣም፤ ፍትሕ ይጣመም ዘንድ፣ ክፉዎች ጻድቃንን ይከባሉ . . . ዐይኖችህ ክፉውን እንዳያዩ እጅግ ንጹሓን ናቸው፤ አንተ በደልን መታገሥ አትችልም፤ ታዲያ፣ አታላዮችን ለምን ትታገሣለህ? ክፉው ከራሱ ይልቅ ጻድቅ የሆነውን ሲውጠውስ፣ ለምን ዝም ትላለህ? አንተ ሰዎችን በባሕር ውስጥ እንዳለ ዓሣ፣ ገዥ እንደሌላቸውም የባሕር ፍጥረታት አደረግህ” (1፥1-14)።

ወንድማችን ኢዮብ፣ እግዚአብሔርን አግኝቶ በሙግት መርታት ፈልጎ ነበር። “ነገር ግን ሁሉን ከሚችል አምላክ ጋር መነጋገር እፈልጋለሁ፤ ከእግዚአብሔርም ጋር መዋቀስ እሻለሁ። (13፡3)። “ዛሬም ሐዘኔ መራራ ነው፤ እያቃሰትሁ እንኳ እጁ በላዬ ከብዳለች። እርሱን የት እንደማገኘው ባወቅሁ፤ ወደ መኖሪያውም መሄድ በቻልሁ! ጒዳዬን በፊቱ አቀርብ ነበር፤ አፌንም በሙግት እሞላው ነበር።” (23:2-4)።

ዳዊት በመዝሙሩ፣ “አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ? እኔን ከማዳን ከመቃተቴም ቃል ለምን ራቅህ?” (መዝሙር 22፥1) በማለት ያነሣውን ጥያቄ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ባሰማው የጣር ድምፅ ወስጥ ተስጋብቷል።

አሳፍ የኋላ ኋላ ግን ዞር በሎ ሲያስውል፡- "ቀኝ እጄንም ያዝኸኝ። በአንተ ምክር መራኸኝ፤ ከክብር ጋር ተቀበልኸኝ" (73:23-24)፣ በማለት የእሮሮውን ምዕራፍ በምስጋና ዝግቶታል። በዚህ ምድር ላይ፣ የእርሱን የሕይወት ጥያቄዎች ጨምሮ፣ ሁነቶች በሙሉ፣ በእግዘአብሔር ሉዓላዊ ማዕቀፍ ውስጥ መያዛቸውን በመረዳቱ ነበር ልቡ ያረፈው። ዕንባቆም ከብዙ ትግል በኋላ መልሱ “ጌታ እግዚአብሔር ኀይሌ ነው” (3:19) የሚል ነበር። ምክንያቱም “እግዚአብሔር ግን በተቀደሰ መቅደሱ አለና!” (2:20)። ኢዮብም መሻቱን አግኞት ነበር፤ እግዚአብሔርን በሙግት የመርታት ዕድል! ሉዓላዊው እግዚአብሔር “እስቲ እንደ ወንድ ወገብህን ታጠቅ፤ እኔ ልጠይቅህ፣ አንተም መልስልኝ (38:3)። እናም የኢዮብ የመጨረሻ ድምዳሜ፣ “አንተ ሁሉን ማድረግ እንደምትችል፣ ዕቅድህም ከቶ እንደማይሰናከል ዐወቅሁ። አንተ፣ ‘ያለ ዕውቀት ዕቅዴን የሚያደበዝዝ ይህ ማን ነው’ አልኸኝ፤ በእርግጥ ያልገባኝን ነገር፣ የማላውቀውንና ላስተውለው የማልችለውን ጒዳይ ተናገርሁ . . . ጆሮዬ ስለ አንተ ሰምታ ነበር፤ አሁን ግን ዐይኔ አየችህ። ስለዚህ ራሴን እንቃለሁ፤ በትቢያና በዐመድ ላይ ተቀምጬ ንስሓ እገባለሁ።”። (42:1-6)

ተስፋችን የተመሠረተው በእርሱ ሉዓላዊ ገዥነትና ሁሉን ዐዋቂነት ላይ ነው። በሚታየውና በማይታየው ዓለም ግዛት ላይ፣ እግዚአብሔር "ጌታ" ያለሆነበ አንዲትም አዪታ ክፍተት የለም። እግዚአብሔር ዓለማትን በፈጠረበትና ደገፎ በያዘበት በዚያው የሥልጣኑ ቃል የእኛንም ሕይወት ደግፎ መያዙን ሳናስብ ልባችን ያርፋል። በርግጥ እርሱ በሁሉ ቦታ አለ፦ "እንደ ንስር የንጋትን ክንፍ ብወስድ፥ እስከ ባሕር መጨረሻም ብበርር፥ በዚያ እጅህ ትመራኛለች፥ ቀኝህም ትይዘኛለች።" (መዝ. 139:9)።

. . . እናም በዚህ ሕይወት ብርቱ ሰልፍ በሆነባት ምድር፣ ለጥያቄያችን ሁሉ መልሱ ሁሉን ዐዋቂ እግዚአብሔር ሉዓላዊ መሆኑ ብቻ እንጂ፣ የእኛን በአምንክዮ ሞግቶ የሚያሳምን መልስ ማግኘታችን አይደልም። ቢገባን ባይገባንም እግዚአብሔር ጻድቅ ነው። ልባችንም ማረፍ ያለበት በእርሱ ሉዓላዊነት ላይ ብቻ ነው። በግል ሕይወታችን ውስጥ ስላሉት ሰልፎችም ሆነ፣ አገራችንን ጨምሮ ዓለም ዐቀፋዊ የሰላም መረበሽና የፍትሕ ቀውስ እየከረረ በመጣበት በዚህ ዘመን እንደ ክርስቲያን ተስፋ የምናደርገው እግዚአብሔርን ነው። በሕይወት የምንኖረው፣ ነገሥታትም፣ እኛም ስለፈቀድን አይደለም። ነገር ግን ከልዑል አምላክ በሚወጣ የምሕረትና መግቦታዊ የቸርነት ቃል ነው። ተስፋችን የተመሠረተው "ምድርና ሕዝቦቿ ሁሉ በሚናወጡበት ጊዜ፣ ምሰሶቿን አጽንቼ የምይዝ እኔ ነኝ።" ባለው ጌታ ላይ ነው። (መዝ 75:3)። የእርሱ መንግሥት ሁሉን ትገዛለችና!

ዓለም በልዑል እግዚአብሔር እጅ እንጂ፣ በሰው እጅ አይደለችም፤ የእኛን የግል ሆነ፣ የዓለምን ታሪክ በሉጋም የያዘ ጌታ ነው የምናመልከው። እግዚአብሔር፣ ጊዜን ሁሉ - ትላንትናን ዛሬና ነገን በአንድ ጊዜ በእጁ የያዘ አምላክ ነው። እርሱ በመገርምም ሆነ በድንጋጤ አይያዝም፤ ነገነም በሥጋት ወይም በተስፋ አይጠብቅም! እርሱ በሰማይና በምድር ሁሉ ላይ ሉዓላዊ ነው፤ ክብር ጐድሎበት፣ ፍጥረትን ክብር አይለምንም፤ በማንም አይደገፍም፤ ለሥራውና ውሳኔው ትክክለኛነት ማንንም አያስፈቅድም፤ ማስተዋሉ ፍጹም፣ ምክርም ማንንም አይጠይቅም፤ ዕውቀት አይጨመርለትም፤ አልገባኝም አስርዱኝ አይልም - ነገሮች ሳይጀመሩ ፍጻሜያቸውን ያውቃልና! አሳቡም አይከለከልም:

ጌታችንም ከአማልክት ሁሉ እንደሚበልጥ ዐውቃለሁና።
በሰማይና በምድር፣
በባሕርና በጥልቅ ሁሉ ውስጥ፣
እግዚአብሔር ደስ ያሰኘውን ሁሉ ያደርጋል። (መዝ. 135; 5-6)

እንግሊዛዊው የወንጌል ሰባኪና ጸሐፊ፣ ዊንክ (1886-1952) እንዳለው - እርሱ ከሁሉ በላይ ነው፤ ". . . God, being infinitely elevated above the highest creature, is the Most High, Lord of heaven and earth. Subject to none, influenced by none, absolutely independent; God does as He pleases, only as He pleases always as He pleases. None can thwart Him, none can hinder Him." (A. W. Wink, The Attributes of God). እናም ውሉ እንደጠፋ የሸማኔ ማግ ውስብስብ ባልብን የአራችንም ሆነ የግል ጉዳያችን፣ እስቲ ለልዑል፣ በቻው ማዳን ለሚቻለው ዕድል እንስጠውና እንረፍ - መውጫውን ያውቃልና!

ከዘማሪ ተስፋዬ ጋር እንዲህ በለን ብንዘምርስ?

“ከአቅምህ በላይ ሆኖ የሚከብድህ
ለመፈታት ከቶ የሚያስቸግርህ
ምን ችግር አለ የሚያዳግትህ
ሁሉን ቻይ የሆንክ ኤልሻዳይ አንተ ነህ . . .”

አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ የሆነብንን አሰብ (ሰቆቃው 5:1)፤ አሜን!

ግርማ በቀለ (ዶ/ር)
507 views03:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 10:42:57
533 views07:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 10:42:50 ስሑትና አሳች ትርጕማን

የ1980ዎቹ የኢኦተቤ/ክ መጽሐፍ ቅዱስ ትርጕም የመጀመሪያውም እንደገና የታተመውም የሄደበት የአተረጓጐም ስልት የሚደንቅም የሚያስደነግጥም ነው። ትርጕም ከምንጭ ወደ ተቀባይ ይፈስሳል እንጂ ከተቀባይ ተነሥቶ ወደ ምንጭ ቋንቋ አይሄድም። በዚያ ትርጕም ውስጥ እንዲህ የተደረጉ በጣም ብዙ ቢኖሩም አንድ ሦስት ምሳሌዎች ብቻ እንይ።

አንደኛ፥ ቲቶ 1፥5 ሽማግሌ የሚለውን ቄስ ወይም ቀሳውስት ብለው በመለወጥ በግርጌ ማስታወሻ፥ #የግሪኩ #ሽማግሌዎች #ይላል።’ ብለው ጽፈዋል። ከየትኛው ነው የተረጐሙት ማለት ነው? ግሪኩ ይህን ካለ፥ ግሪኩ የግርጌ ማስታወሻ አማርኛው ዋና መሆኑ ነው ማለት ነው? አማርኛ ከግሪኩ መብለጡ ነው ማለት ነው? የግሪኩ ሽማግሌ ያለውን የአማርኛ የቀደሙት ተርጓሚዎችና ሊቃውንትም ሽማግሌ ያሉትን በኋላ የመጣው ተርጓሚ ሊለውጥ ድፍረትን ከወዴት አገኘ? ስሑት ትርጕም።

ሁለተኛ ምሳሌ፥ ይህኛው ወደ ምንጩ ወደ ግሪክም፥ ወደ ጎን ወደ ግዕዝም የሚሄድ ነው። ማቴ. 5፥6 ‘ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ’ የሚለውን፥ በመጀመሪያ ‘በግዕዙ፥ ‘ስለ ጽድቅ የሚራቡና የሚጠሙ’ የሚል የግርጌ ማስታወሻ ተጽፎለታል። በቀጣዩ ደግሞ፥ ‘በግሪኩ፥ ‘ስለ ጽድቅ የሚራቡና የሚጠሙ ይላል’ ተብሎ የግርጌ ማስታወሻ ተቀምጦለታል። እውነት ይላል? የትኛው ግዕዝ እንደሚል አልተገለጠም። ታትሞ የተሰራጨው የግዕዝ አዲስ ኪዳን፥ ‘ብፁዓን እለ ይርኅቡ ወይጸምኡ ለጽድቅ።’ ይላል። ጽድቅን እንጂ ስለ ጽድቅ አይልም። ወደ ግሪኩ ስንመጣም ስለ ጽድቅ ይላል? አይልም። ታዲያ ለምን ተባለ? ምናልባት ስለ ጽድቅ ሲባል ወይም ለመጽደቅ ሲባል ወይም ጽድቅን ለማግኘት ሲባል መራብና መጠማትን ለማስተማር ይመስላል። በማመን ሳይሆን በመከራና በጉስቍልና ለመጽደቅ የሚደረግ ጥረትን ትክክለኛ ለማስመሰል ያልተባለው እንደተባለ የተደረገ ነው የሚመስለው። ስሑት ትርጕም።

ሦስተኛ፥ ሮሜ 8፥34 ‘ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።’ የሚለውን፥ ‘ደግሞ ስለ እኛ የሚፈርደው ኢየሱስ ነው።’ ካሰኙት በኋላ በግርጌ ማስታወሻ፥ #ግሪኩ #የሚማልደው #ይላል።’ ብለዋል። ማለቱን አምነው ግን ለውጠውታል። ከሌላ ቋንቋ ጋር ተስተያይቶ፥ ለምሳሌ፥ እንግሊዝኛው ወይም ጉራግኛው እንዲህ ይላል ቢሉ አንድ ነገር ነው። ዋናው የተጻፈበት፥ ኦርጅናሌው፥ ‘ግሪኩ እንዲህ ይላል’ ብሎ ያ የምንጩ ቋንቋ ያላለውን መተርጐም ስነ ጽሑፋዊ ወንጀል ነው። መንፈሳዊ ዕብለቱን ትተን።

አዲስ ኪዳን የተጻፈው እኮ ሲጀመርም በግሪክ ነው። በግሪክ እንደዚያ ካለ፥ በምን ምክንያትና ሥልጣን ነው እኛ፥ ‘የግሪኩ የሚማልድ ይላል፤ እኔ ግን ይፈርዳል ብዬዋለሁ።’ ወይም፥ ‘የግሪኩ ሽማግሌ ይላል እኔ ግን ሊቅ፥ ሊቃናት፥ ቄስ፥ ቀሳውስት፥ ቀሲስ ብዬዋለሁ።’ ወይም፥ ‘የግሪኩ ጽድቅን ብሏል፤ እኔ ግን ስለ ጽድቅ ብያለሁ።’ የምንለው? ይህ አላዋቂነት ብቻ ሳይሆን፥ ድፍረትም ብቻ ሳይሆን፥ የትርጕም ሕግን መተላለፍ ብቻም ሳይሆን፥ አላዋቂዎችን የማሳት የአሳችነት አካሄድ ነው። የኑፋቄ የመጀመሪያው እርምጃ ነው፤ ትልቅ እርምጃ!

መጽሐፍ ቅዱሳችንን በአክብሮት እንማረው፤ ትርጕሙም፥ አተረጓጎሙም፥ ትርጓሜውም ጤነኛ ሆኖ እንጠብቀው።

ዘላለም ነኝ።
486 views07:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 22:33:14

750 views19:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 08:19:51
861 views05:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 08:19:45 ስለ እኛ ምን ይሰማል? ምስክርነታችንስ ምን ይመስል ይሆን?

“ከዚህም የተነሣ በመቄዶንያና በአካይያ ለሚገኙ ምእመናን መልካም ምሳሌ ሆናችኋል። የጌታ ቃል ከእናንተ ወጥቶ በመቄዶንያና በአካይያ መሰማቱ ብቻ ሳይሆን በእግዚአብሔር ያላችሁ እምነት በሁሉ ቦታ ታውቆአል፤ ስለዚህ እኛ በዚህ ጒዳይ ላይ ምንም መናገር አያስፈልገንም፤ በእንዴት ያለ አቀባበል እንደ ተቀበላችሁንና ሕያውና እውነተኛ የሆነውን አምላክ ለማገልገል ከጣዖታት ወደ እግዚአብሔር እንዴት እንደ ተመለሳችሁ እነርሱ ራሳቸው ይናገራሉ፤ ደግሞም ከሙታን ያስነሣውንና ከሰማይ የሚመጣውን ልጁን፣ ከሚመጣውም ቍጣ የሚያድነንን ኢየሱስን እንዴት እንደምትጠባበቁ ይናገራሉ።” (1 ተሰ. 1:7-10)

በተሰሎንቄ ቤተ ክርስቲያን የነበሩ አማኞች የእምነታቸው ጽናት፣ መልካምነታቸውና ምስክርነታቸው ከከተማቸው ወጥቶ በዙሪያቸው ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ የታወቀ ነበር። ትንሽም ቢሆኑ፣ “የጨውነትና የብርሃንነት” አርአያ መሆናቸው የታወቀ ነበር። የማይሸፈን፣ የማይከለከል፣ የማይደበቅ የክርስቶስ ሽታ ነበሩ። አንድ ጸሐፊ (MacLaren's Expositions) እንዳለው፣ “የእግዚአብሔር መለከት – God’s Trumpet” ነበሩ። በአምስት ዐበይት ምክንያቶች ሐዋርያው ጳውሎስ ያመሰግናቸዋል፦

1) በመልካም ምሳሌነታቸው (τύπον / ታይፖን)። ሞዴል፤ የትክክለኛነት መለኪያ፤ ምልክት፤ ፈለግ (pattern) ደረጃ የሚል ሀሳብ አለው። በዕብራውያን 8:5 ላይ “ምሳሌ” የሚለው ቃል በዋለበት አግባብነት ማለት ነው። “እነርሱ ያገለገሉት በሰማይ ላለችው መቅደስ ምሳሌና ጥላ በሆነችው ውስጥ ነው፤ ሙሴ ድንኳኒቱን ለመሥራት በተነሣ ጊዜ፣ በተራራው ላይ በተገለጠልህ ምሳሌ መሠረት ሁሉን ነገር እንድታደርግ ተጠንቀቅ’ የሚል ትእዛዝ የተሰጠው በዚህ ምክንያት ነበር።” የተሰሎንቄም አማኞች፣ የእውነተኛ ክርስቲያናዊ ሕይወት፣ ኅብረት፣ ፍቅር፣ አንድነት፣ ትጋት፣ ቅድስና መሰጠት፣ ተስፋና ጽናት ምሳሌ ነበሩ።

2) የጌታን ቃል በታማኘት በመስማትና በማሰራጨታቸው።

3) በእምነት ጽናት - በመከራና በተቃውሞ መካከል በእግዚአብሔር ላይ የጸና እምነት በማሳያታቸው።

4) በተለወጠ ሕይወት - ቀድሞ ከነበሩበት የጣዖታት አምልኮና ዓለማዊነት ሥር ነቀል በመሆነና በሚታይ መልኩ የመለወጣቸው ዜና በመሰማቱ። ፈጽሞውን በቀድሞ ሕይወታቸው አይታወቁም፤ ፍጹም ተለውጠዋልና! የስም ሳይሆን፣ የአድራሽና የአገዛዝ ለውጥ አድረገዋል። ከጨለማው ወደ ብርሃኑ መንግሥት ዞር ብልዋል፤ የጣዖታትን ጌትነት በመካድ፣ ክርስቶስን መድኅንና ጌታ አድርገው ሰይመዋል፤ ለክርስቶስ ለመኖር ብቻ ሳይሆን፣ ለመሞትን በቆረጠ መሰጠት ወሰነዋል። በርግጥ ክርስቶስን ጌታና መድኅን ያደረጉ፣ እንደ ቀድሞ ሕይወት መኖር አይችሉም።

5) የክርስቶስን ዳግም ምጽአት በጽናት፣ በሕይወት ምስክርነትና በናፍቆት በየዕለቱ በመጠባበቅ በመኖራቸው።

እኛስ?

“ጌታ ሆይ፣ ምስክርነታችንን አድስ!” አሜን!

ግርማ በቀለ (ዶ/ር)
806 views05:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ