Get Mystery Box with random crypto!

Natinael Mekonnen

የቴሌግራም ቻናል አርማ natinaelmekonnen21 — Natinael Mekonnen N
የቴሌግራም ቻናል አርማ natinaelmekonnen21 — Natinael Mekonnen
የሰርጥ አድራሻ: @natinaelmekonnen21
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.15K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ቻናል ቴሌግራሜ hacked በተደረገበት ሳት ለግዝያዊነት የከፈትኩት ቻናል ነው ለችግር ጊዜ ይጠቅማል ተቀላቀሉ
በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ከፈለጉ @NatnaelMekonnen7 በማለት መረጃዎችን ይላኩልን
Facebook.com/natnaelmekonnen.et
Instagram.com/natnaelmekonnen21
Telegram https://t.me/NatinaelMekonnen21

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-09-01 14:20:56 "ኹለቱም ወገኖች" በሚል የሚወጡ መግለጫዎች ከእውነታው ያፈነገጡ በመሆናቸው ተቀባይነት የላቸውም ሲል የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።

የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ዛሬ ባወጣው መግለጫ፤ "በሕወሓት ቡድን እየደረሱ የሚገኙ ጥፋቶችን ለማስቆም መንግሥት ለሰላማዊ አማራጭ ያደረጋቸው ጥረቶች ኹሉ እየመከኑ ባሉበት ሁኔታ፣ አሸባሪውን ሕወሐት መጫን ሲገባቸው "ኹለቱም ወገኖች" በሚል የሚወጡ መግለጫዎች ከእውነታው ያፈነገጡ በመሆናቸው ተቀባይነት የላቸውም።" ሲል ገልጿል።

ሕወሓት ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪዎችን ገፍቶ በየአቅጣጫው በለኮሰው እና ዛሬም እያስፋፋ ባለው እሳት ንጹሐን እየተገደሉ ነው፣ ሕዝብ እየተፈናቀለ፣ ንብረትም እየወደመ እንደሚገኝም አስታውቋል።

"አሁን እንደሚታየው ሕወሓት ከአገር አጥፊነት ተግባሩ የማስቆም ግዴታ በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ላይ ወድቋል።" ያለው አገልግሎቱ፤ የዚህንም ምክንያት እንደሚከተለው በዝርዝር አስቀምጧል፦

=> የሽብር ቡድኑ ሰላማችንን እንዳያደፈርስና አገራችንን እንዳያፈርስ መከላከል ስለሚገባ፤

=> ሕወሓት ወደ ትግራይ የሚላከውን እርዳታ ለተቸገረው ሕዝብ እንዳይደርስ፣ በተቃራኒው እርዳታው ለጦርነት እንዲውል እያደረገ በመሆኑ መንግሥት እርዳታው ለተረጂው ሕዝብ እንዲደርስና ትግራይ ውስጥ ምቹ ኹኔታ በመፍጠር ሕዝቡን ከችግር የመከላከል ግዴታ ስላለበት፤

=> ሕወሓት በእኩይ ተግባሩ ሕዝብን በረሃብ ለመቅጣት ዐቅዶ ተደጋጋሚ ጦርነት የሚከፍተው በክረምት የግብርና ወቅት በመሆኑ፤ መንግሥት ወረራውን እየተከላከለ ያለው ሕዝብን ከረሃብ የማዳን ግዴታ ስላለበት ጭምር ነው። ሲል ገልጿል።

በመሆኑም ሕወሓት ተደጋጋሚ የሰላም አማራጮችን በመግፋት የከፈተው ጥቃት አገራችንን እንዳይበትን፣ የመከላከያ ኃይላችን በኹሉም አቅጣጫ የተከፈተበትን ወረራ ከሰላም ወዳዱ ደጀን ሕዝብ ጋር በመሆን በጽኑ ጀግንነት በመከላከል ላይ እንደሚገኝ የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት በመግለጫው አስታውቋል።
1.9K views11:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 14:20:56 Breaking News Loading.........
1.9K views11:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 14:14:29
የወልቃይት ጠገዴ ጀግኖች አሸባሪውን ለመፋለም እንዲህ ተምመዋል!
1.9K views11:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 14:14:28
“መንግስት የሀገሪቱን ሉአላዊነት ለማስከበር በአሸባሪው ሕወሓት ላይ የትኛውንም እርምጃ ይወስዳል”
አቶ ደመቀ መኮንን
1.9K views11:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 11:12:27 በላይኛው መርጦ ፤ በታችኛው ኩሌ
ስንት ይሆን ርቀቱ መቀሌ - #ከአበርገሌ !!!
2.2K views08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 11:12:27 መድፍ፣ ታንክና ሌላም ከባድ መሳሪያ የታጠቀ በ10 ሺዎች የሚቆጠር የፌዴራል ጦር ኤርትራ ገብቷል- ታደሰ ወረደ። I’m dead sure ይህ ጦር ትግራይ ገብቶ መግቢያ መውጪያ ሲያሳጣቸው ኤርትራ ወጋችን ይላሉ። TPLFን ለማጥፋት አይደለም ኤርትራ ሲኦል እንወርዳለን!
2.2K views08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 20:44:36 ታሪክ የማይረሳው ተጋድሎ!

ህወሓት ወያኔ በራያ ግንባር እስካሁን ባለው መረጃ ከሁለት መቶ ሺህ የማያንስ ኃይል ይዞ መጥቷል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ የምስራቅ አማራ ፋኖ እና ሚሊሻው የታገለው ከዚህ ኃይል ጋር ነው። ባለፈው ቆቦን፣ ትናንት ወልዲያን ለመያዝ የአሸባሪው ቡድን ብዙ ኃይል አልቆበታል። በህዝብ መአበል የጀመረው ጦርነት ለወገን ጦር ከፍተኛ ግፊት የፈጠረ ቢሆንም በጀግንነት ሲፋለም ከርሟል።

ፌስቡከኛው ሰግቶ የሸሸ ወገናችን ፎቶ ይለጥፋል እንጅ ብዙ የሚነገርለት ጀግናም ሞልቷል። ለሰራዊቱ ደጀን የሆኑ ወጣቶች፣ ምግብ እያበሰሉ የሚያቀርቡ እናቶች፣ ሰብሉን ትቶ ከሰራዊቱ ጎን የተሰለፈው አርሶ አደራችን ታሪክም በደማቅ ታሪክ የሚፃፍ ነው። እነዚህ ጀግኖች ለክብራችን ተዋድቀዋል። ሌላው ህዝባችን እንዳይጎዳ በርካታ ዋጋ ከፍለውልናል።

በአካል፣ በስልክ፣ በፌስቡክ የማውቃቸውን የራያ፣ የወልዲያ አካባቢ ወገኖች ደውዬ አነጋግሬያለሁ። ብርታታቸው የሚገርም ነው። ቤተሰቦቻቸው የተገደሉባቸው፣ የተዘረፉባቸው፣ ቤተሰቦቻቸው ይሙቱ ይኑሩ የማያውቁ ናቸው። ብዙ ነገሮችን እምቅ አድርገው ችለው መንፈሳቸውን ያበረቱ ጀግኖች ናቸው። የቤሰተቦቻቸውን ሕመምና ስጋት በሚገባ ያልተረዳናቸው፣ ነገር ግን በርካታ ፅኑ ወገኖች አሉን። አሉባልታና ወሬ፣ ሰበርና አሳዛኝ ዜና ከሚለጠፈው በላይ የእነዚህ ጀግኖቻችን ፅናት ብዙ ትርጉም ነበረው። ለእኛ ሲሉ በየጥሻው ትህነግ ጋር ተናንቀው መስዋዕትነት የከፈሉ ጀግኖች፣ በአካባቢው ንቅንቅ ሳይል ለሰራዊቱ ደጀን የሆነው በርካታ ሕዝባችን ፅናት ሊያስተምረን፣ ላላወቀው ልናሳውቅ ሲገባ እንቶፈንቶው ሊያጨቃጭቀን አይገባም ነበር።

ጌታቸው ሽፈራው
1.3K views17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 20:44:36 ወያኔ አማራ ንቃ ካለ ነገር አለ ማለት ነው

አሸው አንበሳው
1.3K views17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 20:44:36
ከሱዳን ደብቀን ልናስገባ የነበረውን የጦር መሳሪያ የኢትዮጵያ አየር ሀይል አጋይቶብናል

He looks high
1.3K views17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 20:44:36 የተከፈተብንን ዘርፈ ብዙ ጦርነት ሁሉም ዜጋ በኅብረ ብሔራዊ አንድነት መመከት አለበት – ዶ/ር ለገሰ ቱሉ

የውስጥ ባንዳዎችና ታሪካዊ ጠላቶቻችን ተቀናጅተው የከፈቱብንን ዘርፈ ብዙ ጦርነት ሁሉም ዜጋ በኅብረ ብሔራዊ አንድነት መመከት አለበት ሲሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ዶክተር ለገሰ ቱሉ ገለፁ፡፡

ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት፥ ባንዳዎቹ በአፈቀላጤዎቻቸው በአንድ በኩል “ጦርነቱ አንተን አይመለከትም” እያሉ ይገዘታሉ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ሂሳብ እናወራርደለን፣ ኢትዮጵያን ለማፍራስ ሲኦልም ቢሆን እንገባለን እንደሚሉ ጠቁመዋል።

“ከአማራ ህዝብ ጋር ፀብ የለንም እያሉ የአማራን ሴቶችና ሕጻናት ይደፍራሉ፣ ንብረቶቻቸውን ይዘርፋሉ፣ በአደባባይ ያዋርዳሉ፣ መሰረተ ልማቶቻቸውን ያወደማሉ” ነው ያሉት።

በተመሳሳይ የአፋር ህዝብ እየታገለም፣ ንብረቱ እየወደመበትም፣ ራሱ እየተራበም ቢሆን ለትግራይ ወንድሞቹ ሰብአዊ እርደታ ሳይስተጓጓል እንዲቀርብ እያደረገ ከቀዬው እንዲፈናቀል፣ የዘር ፍጅት እንዲደርስበት ማድረጋቸውን አስደርተዋል።

ኦሮሞው፣ ሶማሌው፣ ጉሙዙ ወዘተ ወዳጆቻችንና አጋሮቻችን ናቸው እያሉ ከቅጥረኛ ሽብርተኞችና ታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር ተቀናጅተው እርስ በርስ እንዲፋጁ፣ መሰረተ-ልማቶቻቸው እንድወደም፣ ሃብት ንብረታቸው እንዲዘረፍ ያደርጋሉ ብለዋል፡፡

ለመሆኑ ይህ እኩይ ድርጊታቸው የቅድስና ስራ ነው እንዴ? ሲሉ የጠየቁት ሚኒስትሩ፥ ሰብአዊ እርዳታን እንደመሳሪያ ተጠቅመው በኋላ ቀር የጦርነት ስልት የትግራይን ህጻናት፣ አዛውንቶችና ሴቶችን ሲማግዱ ምነው የኢትዮጵያ ወጣት ወደ ጦርነት አትግባ ብለው የራራው አንጀታቸው ለትግራይ ሲሆን ምነው ጠነከረ? ሲሉም ጠይቀዋል።

የህወሓት መሪዎች እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል እንዳለችው እንስሳ ምቾት እና ድሎታቸው አይጓደል እንጂ የትግራይ ህዝብ እና ወጣት እንደአቧራ ቢቦኑ፣ እንደጉም ቢተኑ፣ እንደ ቅጠል ቢረግፉ ለቅፅበትም ያህል አይገዳቸውም ብለዋል።

አሸባሪው ህወሓት ለትግራይ ህዝብ የሚያመጣው አንዳችም ተስፋ እንደሌለ ሚኒስተሩ ተናግረዋል።

በትግራይ ህዝብ ስም ተለምኖ የመጣን የዕርዳታ ስንዴ እና ነዳጅ በመስረቅ ለጦርነት መጠቀም የኖረበት የቡድኑ አስነዋሪ ገፅታ እንደሆነ በማወቅ የትግራይ ወጣት ቡድኑን በማውገዝ ሞት እና ስደት እንዲቆም የጋራ ድምፁን ሊያሰማ ይገባል ሲሉም አሳስበዋል፡፡

ህዝባችን ሆይ ንቃ ያሉት ሚኒስትሩ፥ ሀገር በጦርነት ውስጥ ሆና ገለልተኛ ነኝ ብሎ መቀመጥ ከአንድ ሀገር ወዳድ ዜጋ እንደማይጠበቅ አመልክተዋል፡፡

ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሚችለው አቅም ኢትዮጵያ ላይ የተከፈተውን ፈርጀ ብዙ ጦርነት መመከት በማለት፥ በጦር ግንባር፤ በደጀንነት፤ በሳይበር ውጊያ እና በሌሎችም መንገዶች ኢትዮጵያ ላይ የተከፈተውን ጦርነት ለመመከት በጋራ መቆም የህልውና ግዴታ እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡

“ሀገር ሁሉም ነገር ናት! ሀገር መኖሪያ ናት፤ ሀገር እኛነታችን የተገነባባት እሴት ናት፤ ሀገር አብሮ በሚኖር በምንወደው በምናከብረው ህዝብ ትገለጻለች፤ ሀገር የልጅ ልጆቻችን የሚረከቧት የትናንት ታሪካችን፤ የዛሬ ሀብታችን እና የነገ ተስፋችን ናት” ብለዋል።

እኛነታችንን የቀረፀች፣ መኖሪያችን የሆነች እና የነገ ተስፋችንን የሰነቀች ሀገራችን እንድትጠፋ በተለያዩ መስኮች ጦርነት ተከፍቶባታል ያሉት ዶክተር ለገሰ፥ እኛነታችን የሆነችው ኢትዮጵያችን እንደ ጠላት ፍላጎት እንዳትጠፋ ሁላችንም ከመንግስት ጎን በመሆን የምንችለውን ሁሉ ማድረግ አለብን ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ሠራዊታችን ጀግንነት መገለጫው፤ ድል መዳረሻው፤ ህዝባዊነት ስንቁ የሆነ የኢትዮጵያ ጀግና፤ ፅኑ ዘብ መሆኑንም ገልፀዋል።

በማንኛውም ጊዜ እና ሁኔታ ለመከላከያ ሰራዊታችን ያለንን ክብር ያለስስት ማሳየት አለብን ያሉት ሚኒስትሩ፥ ከምንም በላይ ውድ የሆነውን ህይወቱን ለሚሰጠን ጀግናው ሰራዊታችን ደጀንነታችንን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ልናሳየው ይገባል ሲሉ አሳስበዋል፡፡

ሰራዊታችን የሀገሩን ረሀቧን እየተራበ፤ ጥሟን እየተጠማ፤ መከራዋን እየተሸከመ ኢትዮጵያን እየጠበቀ ያለ ብሔራዊ ክብራችን እና ሀብታችን ነው ብለዋል፡፡
1.3K views17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ