Get Mystery Box with random crypto!

ነሲሐ ለሱኒዋ እህቴ !!

የቴሌግራም ቻናል አርማ nasiha_lesuniwa_ehete — ነሲሐ ለሱኒዋ እህቴ !!
የቴሌግራም ቻናል አርማ nasiha_lesuniwa_ehete — ነሲሐ ለሱኒዋ እህቴ !!
የሰርጥ አድራሻ: @nasiha_lesuniwa_ehete
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 463
የሰርጥ መግለጫ

https://t.me/joinchat/Vh2x3RbmuMMafY3f

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-06 05:33:15 አላህን መፍራት
┄┄┉┉✽‌»‌ »‌✽‌┉┉┄┄

(ክፍል 1)
•┈• ❁ •┈•

አላህን መፍራት (ኸውፍ ሚናሏህ) የዒባዳ ፍሬና አላማውም ጭምር ነው። ተቅዋ (አላህን መፍራት) በአንድ ሠውና በአላህ ቁጣ መካከል የሚኖር መከላከያ ነው። ይህ እንዲሆን የሚያደርገው ደግሞ ትክክለኛ የአላህ ፍራቻ ነው።

يَا أَيُّهَا النَّاسُ اتَّقُوا رَبَّكُمْ وَاخْشَوْا يَوْمًا لَا يَجْزِي وَالِدٌ عَنْ وَلَدِهِ وَلَا مَوْلُودٌ هُوَ جَازٍ عَنْ وَالِدِهِ شَيْئًا إِنَّ وَعْدَ اللَّهِ حَقٌّ فَلَا تَغُرَّنَّكُمُ الْحَيَاةُ الدُّنْيَا وَلَا يَغُرَّنَّكُمْ بِاللَّهِ الْغَرُورُ
“እናንተ ሰዎች ሆይ! ጌታችሁን ፍሩ። ወላጅም ከልጁ (በምንም) የማይጠቅምበትን፤ ተወላጅም እርሱ ወላጅን በምንም ጠቃሚ የማይሆንበትን ቀን ፍሩ። የአላህ ቀጠሮ እውነት ነውና። ቅርቢቱም ሕይወት አትሸንግላችሁ። በአላህም (መታገስ) አታላዩ (ሰይጣን) አያታልላችሁ።” ( ሉቅማን 31፤33)

ቁርአንም ሆነ ሐዲሶች በማስጠንቀቅያ እንዲሁም ስለዕለት ቂያማና ስለሑኔታዎቿ በሚተርኩ አንቀፆች የተሞሉ ናቸው።

فَاعْبُدُوا مَا شِئْتُمْ مِنْ دُونِهِ قُلْ إِنَّ الْخَاسِرِينَ الَّذِينَ خَسِرُوا أَنْفُسَهُمْ وَأَهْلِيهِمْ يَوْمَ الْقِيَامَةِ أَلَا ذَٰلِكَ هُوَ الْخُسْرَانُ الْمُبِينُ لَهُمْ مِنْ فَوْقِهِمْ ظُلَلٌ مِنَ النَّارِ وَمِنْ تَحْتِهِمْ ظُلَلٌ ذَٰلِكَ يُخَوِّفُ اللَّهُ بِهِ عِبَادَهُ يَا عِبَادِ فَاتَّقُونِ
“ከእርሱ ሌላ የሻችሁትን ተገዙ። ከሳሪዎች ማለት እነዚያ በትንሣኤ ቀን ነፍሶቻቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ያከሰሩ ናቸው። ንቁ! ይህ እርሱ ግልጽ ከሳራ ነው” በላቸው። ለእነርሱ ከበላያቸው ከእሳት የኾኑ (ድርብርብ) ጥላዎች አልሏቸው። ከበታቻቸውም ጥላዎች አልሏቸው። ይህ አላህ ባሮቹን (እንዲጠነቀቁ) በእርሱ ያስፈራራበታል። “ባሮቼ ሆይ! ስለዚህ ፍሩኝ።” (አል-ዙመር 39፤15-16)

ረሡል /ሰ.ዐ.ወ/ መጨረሻችን እንዳያስጠላ እንዲህ ያስጠነቅቁናል፡-

فوالله الذي لا إله غيره إن أحدكم ليعمل بعمل أهل الجنة حتى ما يكون بينه وبينها إلا ذراع فيسبق عليه الكتاب فيعمل بعمل أهل النار فيدخلها وإن أحدكم ليعمل بعمل أهل النار حتى ما يكون بينه وبينها إلا ذراع فيسبق عليه الكتاب فيعمل بعمل أهل الجنة فيدخلها متفق عليه

“ከሱ ውጪ ሌላ ጌታ የሌለ በሆነው አላህ ይሁንብኝ አንደኛችሁ የጀነት ሠዎችን ስራ ይሰራና ለሞት አንድ ክንድ ያህል ሲቀረው የተደነገገው ይቀድመዋል ከዚያም የእሳት ሠዎችን ስራ ይሰራና እሳት ይገባል። አንድኛችሁ የእሳት ሰዎችን ስራ እየሰራ ይቆይና ለመሞት አንድ ክንድ ሲቀረው የጀነት ሰዎችን ስራ ይሰራና ጀነት ይገባል” ( ቡኻሪና ሙስሊም)

በሌላ ሃዲስ ረሡል (ሰ.ዐ.ወ) አንዲህም ብለዋል:-

والله لو تعلمون ما أعلم لضحكتم قليلاً ولبكيتم كثيرًا وما تلذذتم بالنساء على الفرش ولخرجتم إلى الصعدات تجأرون إلى الله تعالى) رواه الترمذي(

“በአላህ ይሁንብኝ የማውቀውን ብታውቅ ኖሮ ትንሽ ስቃችሁ ብዙ ባለቀሳችሁ ነበር። እንዳችሁም በአልጋ ላይ ጨዋታ ደስተኛ አይሆንም ነበር። (ከዚህ ይልቅ) ወደ ሜዳዎች ወጥታችሁ ወደ አላህ አቤት ትሉ ነበር። ( ቲርሚዚ)

በሌላ ዘገባም

شيبتني هود وأخواتها) رواه الترمذي

“ሁድና አምሳያዎቹ አሸበቱኝ” ( ቲርሚዚ)

እንዲሁም

ما وجدت منظرًا إلا والقبر أفظع منه

“እንደቀብር ያለ አስደንጋጭ ቦታ የትም አምሳያውን አላገኘሁለትም!”

ዑመር አንድ ቀን በጣም አለቀሱ:: በዚሁ ለቅሷቸውም ለህመም ተዳርገው ሰዎች ጠየቋቸው። ነገር ግን ለለቅሶና ለህመም የዳረጋቸው ሌላ ሳይሆን

إِنَّ عَذَابَ رَبِّكَ لَوَاقِعٌ
“የጌታህ ቅጣት በእርግጥ ወዳቂ ነው፤ (የማይቀር ነው)።” ( አጥ-ጡር 52፤7) የሚለውን የቁርአን አንቀፅ በማዳመጣቸው ነበር።

አላህን የመፍራት ፍሬዎች
•═══••• •••═══•

1.አላህን መፍራት ዕውቀት ለማግኘት ትልቁ መሳሪያ ነው።

إِنَّمَا يَخْشَى اللَّهَ مِنْ عِبَادِهِ الْعُلَمَاءُ إِنَّ اللَّهَ عَزِيزٌ غَفُورٌ
“አላህን ከባሮቹ ውስጥ የሚፈሩት ዐዋቂዎቹ ብቻ ናቸው። አላህ አሸናፊ መሓሪ ነው።” ( ፋጢር 35፤28)

ይህ ጌታውን ተገዥ የሆነ አዋቂ ባህሪይ ነው። ይህ አዋቂ የጌታውን ደረጃ በዕውቀቱ አማካኝነት አውቆ እሱን ይፈራዋል፣ ይጠነቀቀዋልም።

2.አላህን መፍራት የሰው ልጅ ባህሪይ ብቻ ሳይሆን የመላኢኮችም ነው።

يَخَافُونَ رَبَّهُمْ مِنْ فَوْقِهِمْ وَيَفْعَلُونَ مَا يُؤْمَرُونَ
“ጌታቸውን ከበላያቸው ሲኾን ይፈሩታል። የታዘዙትንም ሁሉ ይሠራሉ።” ( አን-ነሕል 16፤50)

3.አላህን መፍራት፣ ስራቸውን ለአላህ ብቻ ያደረጉ የዳዕዋ ሰዎች መገለጫ ነው።

الَّذِينَ يُبَلِّغُونَ رِسَالَاتِ اللَّهِ وَيَخْشَوْنَهُ وَلَا يَخْشَوْنَ أَحَدًا إِلَّا اللَّهَ وَكَفَىٰ بِاللَّهِ حَسِيبًا
“ለእነዚያ የአላህን መልእክቶች ለሚያደርሱና ለሚፈሩት ከአላህ በስተቀርም አንድንም ለማይፈሩት (ተደነገገ)። ተቆጣጣሪም በአላህ በቃ።” ( አል-አሕዛብ 33፤39)

4.አላህን መፍራት፣ የሙዕሚኖች ምልክትና መታወቂያ ነው


إِنَّمَا ذَٰلِكُمُ الشَّيْطَانُ يُخَوِّفُ أَوْلِيَاءَهُ فَلَا تَخَافُوهُمْ وَخَافُونِ إِنْ كُنْتُمْ مُؤْمِنِينَ
“እንዲህ የሚላችሁ ሰይጣን ብቻ ነው። ወዳጆቹን ያስፈራራችኋል። አትፍሩዋቸውም። ምእምናንም እንደኾናችሁ ፍሩኝ።” ( ኣሊ-ዒምራን 3፤175)

የአላህ ፈሪዎች ሁሉ አለቃ ረሡል (ﷺ) እንዲህ ይላሉ፡-

أنا أعلمكم بالله وأشدكم له خشية

“እኔ አላህን እጅግ በጣም አዋቂና ፈሪ ነኝ”

ይ'ቀ'ጥ'ላ'ል'★ـ{ـــــــــــــــــــــ ـــــــــــــــــــــ}ـ★
4 views02:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 23:27:52 ይህ የረሱል ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ታላቅ ምክር ነው።

አንድ ሰው ወደ ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ጋ መጣና "ለዱንያም ሆነ ለአኼራ የሚጠቅም ንግግር ለመጠየቅ መጣው" አላቸው ።
እሳቸውም ደግሞ "የመጣልህን ጠይቅ"
አሉት።

"ከሰው ሁሉ አዋቂ ለመሆን እፈልጋለው?"
እሳቸውም "አላህን ፍራ" አሉት

"ከሰው ሁሉ ሀብታመ ለመሆን እፈልጋለው?" ሲላቸው።
"ባለህ ነገር ተብቃቅተ አላህን አመስግን" አሉት

"ትክክለኛ ፈራጅ እና ታማኝ ሰው ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል
"ለራስህ የምትወደውን ለሰዎች ውደድ"
አሉት።

"ከሰው ሁሉ ብርቱ ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል
"በአላህ ተወከል"አሉት

"በአላህ ዘንድ ብቸኛ ተመራጭ ለመሆን
እፈልጋለው" ሲላቸው?
"ዚክር አብዛ" አሉት።

"ከሰው ሁሉ በላጭ ለመሆን እና ጥሩ ሰው ለመሆን
እፈልጋለው?" ሲል
"ለሰው ጠቃሚ ሁን" አሉት።

"የተከበረና ቸር ሰው ለመሆን እፈልጋለው?" ሲላቸው
"ችግርህን ለፍጡር አትንገር" አሉት።

"ረሱል እና አላህ እንዲወዱኝ እፈልጋለው?" ሲል
"አንተም እነሱ የወደዱትን
ውደድ" አሉት::

"ከወንጀል የጠራው ሁኜ አላህንመገናኘት እፈልጋለው" ሲል
"ጀናባህን በደንብ ታጥበ እስቲግፋር አብዛ ማልቀስ መተናነስ መታመም
አለብህ" አሉት።

"ከበጎ ሰሪወች ለመሆን እፈልጋለው"
ሲላቸውም
"አላህን ልክ እንደምታየው ሁነክ ተገዛው" አሉት።

"ኢማኔ እንዲ ሞላ
እፈልጋለው" ሲል
"ፀባይህን አሳምር" አሉት።

"እርዝቄ እንዲሰፋ እፈልጋለው" ሲል
"ተዋዱዕ አዘውትር" አሉት።

"ዱዓዬ ሙስተጃብ እንዲሆንልኝ እፈልጋለው?" ሲላቸው
"ሀራም አትብላ" አሉት::

"አላህን ከሚታዘዙ ሰዎች ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል
"ግዴታዎችህን ፈፅም" አሉት።

"በአላህ ዘንድ ትልቁ ሀሠና ወይም ደግ ሥራ የቱ ነው?" ብሎ ሲጠይቃቸው
"መልካም ፀባይ መተናነስ እና በበላ ላይ ሰብር ማድረግ ነው" አሉት።

"በአላህ ዘንድ የትኛው ስርዓት ነው መጥፎ ሥራ?" ሲል ሲጠይቃቸው
"መጥፎ ፀባይና ፍላጎትን መከተል ናቸው" አሉት

"በዱንያም ሆነ በአኼራ የአላህን ቁጣ የሚያበርድ ምንድነው" ሲል ጠየቃቸው?
"ድብቅ ሰደቃ እና ዘርን መቀጠል ናቸው" አሉት።

"የቂያማ ቀን በአላህ ኑር ለመሰብሰብ
እፈልጋለው?" ሲል
"ሰውን አትበድል" አሉት

"የቂያማ እለት አላህ እንዲያዝንልኝ እፈልጋለው?"
"ለአላህ ባርያዎች እዘን" አሉት።

"የቂያማ ቀን የጀሀነም እሳት የሚያጠፋው ምንድነው?" ብሎ ሲጠይቃቸው
"በችግር ላይ ወይም በሙሲባ ላይ ትህግስት መሰድረግ ነው" አሉት።

"የቂያማ እለት ነውሬ እንዲሸፈንልኝ እፈልጋለው?" ሲል
"የወንድምህን አይብ ሸፍን" አሉት።

"የቂያማ ቀን ከአላህ ቁጣ ሰላም ለመሆን
እፈልጋለው?" ሲል
"በአንድም ፍጡር አትቆጣ" አሉት።
26 views20:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 16:22:44 خُطْبَةُ الْجُمُعَةِ
የጁሙዓ ኹጥባ

يومُ نجى الله فيه موسى
አሏህ ሙሳን ነፃ ያወጣበት ቀን

ደሴ አል-አዝሐር መስጂድ

محرم/7 / 1444

አቡ ረይስ ሙሀመድ ኢብኑ ኢማም
↓↓↓
31 views13:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 13:31:46 https://t.me/Nasiha_lesuniwa_ehete
35 views10:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 12:46:20 ሹሩጡ ሶላት ክፍል {17} በኢብኑ ኸይሩ
35 views09:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 18:11:54 #ሶስት ነገራቶች በቀልድ ይሁን በምር ጊዜ ይፀድቃሉ

①) አንድ ሰው ለቀልዱም ይሁን የምሩ ልጄ ድሬሀለሁ ካለ ይፀድቃል።
②) አንድ ሰው ለቀልዱም ይሁን የምሩ ሚስቴን ፈታሁ ካለ ይፀድቃል።
③) አንድ ሰው ለቀልድም ይሁን የምሩ ሚስቱን ከፈታ በሗላ መለስኩኝ ካለ ይፀድቃል።
ለዚህም ነው ነብያችን እንዲህ ያሉት
【ثلاث جدهن جد وهزلهن جد: النكاح والطلاقق والرجعة】
48 views15:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 11:24:10 ሹሩጡ ሰላት ክፍል { በአቡ አብደሏህ ኢብኑ ኸይሩ
https://t.me/+I24JPm3D99hkNmY0

https://t.me/+b9vHubxXvqtiZTU0

https://chat.whatsapp.com/I1xVRl4Yf6J9s1SIVZs3aV

https://chat.whatsapp.com/I1xVRl4Yf6J9s1SIVZs3aV
50 views08:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 11:23:10 ሹሩጡ ስላት ክፍል {16} በኢብኑ ኸይሩ
47 views08:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ