2022-08-02 21:47:09
የአላህን እዝነት ተመልከቱ!!
ከቁርኣን አንድ ሀርፍ የቀራ ሰው 10 አጅር ያገኛል። «አሊፍ፣ ላም፣ ሚም» ያለ ሰው 30 አጅር ያገኛል።
«ቁል ሁወ‘ላሁ አሀድ»ን የቀራ ሰው የቁራኣንን 1/3 እንደቀራ ይፃፍለታል።
ሰላሳ አያዎችን ያላትን «ሱረቱል ሙልክ»ን የቀራ ሰው… ታማልድለታለች፣ ወንጀሉም ይማራል።
አላህን ሚያስታውስ ሰው አላህ ያስታውሰዋል።
በአላህ መንገድ ከመግደልና ከመገደል በላይ ዚክር ማድረግ በላጭ ነው።
ሱብሀነላህ፣ አልሀምዱሊላህ፣ ክኢላሀ ኢለላህ፣ አላሁ አክበር… ፀሀይ ከወጣባቸው ቦታዎች ባጠቃላይ በላጭ ናቸው። የጀነት ተክሎችም ናቸው።
100 ጊዜ ሱብሀነላሂ ወቢሀምዲሂ ያለ ሰው… ወንጀሉ የበህር አረፋ ቢያህል እንኳን ይማርለታል።
100 ጊዜ ‘ላ ኢላሀ ኢለላህ ወህደሁ ላ ሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሀምዱ ወሁወ አላ ኩሊ ሸይዒን ቀዲር’ ያለ ሰው… 10 ባሪያ ነፃ እንዳወጣ ይያዝለታል። 100 ወንጀል ይማርለታል፣ 100 ምንዳ ያገኛል፣ ከሸይጣን ይጠበቃል፣ ማንም የሱን ያህል ምንዳ አያገኝም እሱ ያለውን ያህል ያለ ወይም ከሱ በላይ ያለ ሰው ሲቀር።
‘ላሀውለ ወላ ቁወተ ኢላ ቢላህ’ የጀነት ተክል ነው።
በነቢዩ ላይ አንዲትን ሰለዋት ያወረድ አላህ በሱ ላይ 10 ያወርዳበታል።
ውዱእን አስውቦ ያደረገ ሰው ወንጀሉ ይማርለታል። ፊቱን ሲታጠብ በአይኑ ያየው ወንጀሉ ይገርፋል። እጁን ሲታጠብ በጁ የሰራው ይወጣል፣ እግሩን ሲታጠብ በእግሩ ወደ ወንጀል የሄደበት ወንጀሉ ይጠራል። (ከወንጀል ጠርቶ እስኪወጣ ድረስ።)
ቤቱ ውድዕ አድርጎ ወደ መስጂድ የሚሄድ ሰው በአንድኛው እርምጃው ወንጀሉ ይታበሳል፣ በሌላኛው አጅር ይፃፍለታል።
ውዱኧን፣ ኩሹኧን፣ ሩኩኣን አስተካክሎ ዋጂብ ሰላትን የሰገደ ሰው ያለፈው ወንጀሉ እንዳለ ይማርለታል። (ከባኢሮች ሲቀሩ።)
ውዱእ ሳይፈታ እዛው የሰገደበት ቦታ ላይ የዘወተረ ሰው… መላኢካዎች ምህረትን ይጠይቁለታል። ‘አላህ ሆይ! ማረው፣ አላህ ሆይ! እዘንለት!’ ይላሉ።
ኢሻን በጀመኣ የሰገደ ሰው ሌሉትን ግማሽ እንደቆመ ይፃፍለታል፣ ፈጅርን በጀመኣ የሰገደ ደግሞ ሌሊቱን በሙሉ እንደሰገደ ይፃፍለታል።
በፈጅርና በኢሻ ውስጥ ያለን ምንዳ ሰዎች ቢያውቁ ኖሮ በእንብርክካቸውም ቢሆን ይመጡ ነበር።
የፈጅር ሱና ከዱንያን ውስጡ ካለው ነገር ባጠቃላይ በላጭ ናት።
በአላህ ላይ ምንዳውን ተሳስቦ ለይልን የቆመ ሰው ያለፈው ወንጀሉ እንዳል ይሰረያል።
ፆመኛን ያስፈጠረ ሰው… የፆሚን ምንዳ ያገኛል።
ከነዚህ ገራሚ የነብዪ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሀዲስ ቡኋላ አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ… አጅሮቹ አላጓጉህም?!… በርግጥም እንደኔ ወንጀሉ የበዛ ሰው እነዚህን ተግባራት ለመስራት እንደሚነሳሳ ተስፋ አደርጋለሁ።
ተነሳሳችሁም፣ አልተነሳሳችሁም… አንድ ነገር ልንገራችሁ። እንበልና ‘እኚህን ተግባራት አንዲት ሌሊት ሰርታችሁ ግን ለ1000 ወራት ከሚሰራ መልካም ስራ በላይ ይያዝላችኃል’ ቢባልስ? አሁንስ አይኑን የሚያሽ አለ??
እንግዲያውስ ፈፅሙት! ችሮታው ሰፊ የሆነው ጌታችሁ ይህንንም አድርጎል። አንዲትን ሌሊት ከ1000 ወራት በላይ አብልጧታል። በሷ ውስጥ ሚሰሩ መልካም ስራዎችን 83 አመት ከሚሰሩ መልካም ስራዎች አልቆታል።
አንተ ዝንጉ ሰው ሆይ!
:
የአደም ልጅ ሆይ! እመነኝ፣ ጀነት ከጫማ ማሰሪያህ በላይ ወዳንተ ቅርብ ናት።
64 views18:47