2023-05-04 22:57:41
በጃሌ በቴ ኡርጌሳ እና በዶ/ር ደረጄ ገረፉ መካከል በተደረገው ቃለመጠይቅ ስለተነሳው የአባጅፋር አጀንዳ ዙሪያ ትንሽ ነገር ልበል !
በመጀመሪያ ደረጃ በአባ ጅፋር ጉዳይ የተነሳውን ሀሳብ ደግፋችሁም ሆነ ተቃውማችሁ አጀንዳ የምታራግቡ በሙሉ በጨዋ ቃላት እንዲሁም በክብር ድንጋይ ራሶች መሆናችሁን ስነግራችሁ ታላቅ ደስታ ይሰማኛል።
ወደ ጉዳዩ ስገባ ጃል በቴ ኡሬጌሳ በኦሮሞ አንድነት የሚያምን ታላቅ ጀግና ታጋይ ነው። በሁሉም ቦታ ያለ ኦሮሞ አንድ ህዝብ ነው ብሎ የሚያምን በኦሮሞነት የታነፀ ሰው ነው።
አንዳንድ ድንጋይ ራሶች ግን የጃል በቴን ንግግር አጣመው በመረዳት የጅማ ኦሮሞ ላይ ቅርሻታቸውን በደንብ ሲያቀረሹ እያየን ነው። በተቃራኒው ደግሞ የጅማ ኦሮሞ ሲሰደብ እንደ ኦሮሞነት መልስ መስጠት እና መከላከል እየቻሉ የጅማን ህዝብ ከሀይማቱ ጋር አገናኝተው ለሀይማኖታችን እንቆማለን እያሉ ሌላ አጀንዳ ፈጥረው የሚጮሁ ሌላ ድንጋይ ራሶችንም እያየን ነው።
ሁለቱ ድንጋይ ራሶች ናቸው እርስ በእርስ እየተሰዳደቡ ያሉት። ሰፊው የኦሮሞ ህዝብ ለዚህ አይነት ርካሽ አጀንዳ ጆሮ አይሰጥም ስቆ ነው የሚያልፈው። የኦሮሞን አንድነት ለመናድ ኦሮሞ ውስጥ አድፍጠው የተቀመጡ እና እድል የሚሞክሩ ጩሉሌዎቼን ግን በደንብ እየታዘብን ነው።
ድንጋይ ራስ የሚለውን ቃል በመጠቀሜ ይቅርታ አድርጉልኝ ዲሲፕሊን አይደለም ግን ሌላ ስም አጣሁላቸው ለዛ ነው። አፉ በሉኝ
@my_oromia
5.6K viewsedited 19:57