Get Mystery Box with random crypto!

M.O.R East Addis Ababa Branch

የቴሌግራም ቻናል አርማ moreastaddisabababranch — M.O.R East Addis Ababa Branch M
የቴሌግራም ቻናል አርማ moreastaddisabababranch — M.O.R East Addis Ababa Branch
የሰርጥ አድራሻ: @moreastaddisabababranch
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.57K
የሰርጥ መግለጫ

Ministry Of Revenues (MOR) is the body responsible for collecting
revenue from customs duties and domestic taxes.

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-08 17:46:34
እንኳን ለዒድ አል-አድሐ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

በገቢዎች ሚኒስቴር የምስራቅ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች እና ሰራተኞች ለቅርንጫፍ ጽ/ቤታችን ሙስሊም ሰራተኞች፣ ለእምነቱ ተከታይ ግብር ከፋዮች እንዲሁም ለመላው ሙስሊም ማህበረሰብ እንኳን ለ1443ኛው የዒድ አል-አድሐ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቱን ይገልፃል!

መልካም በዓል ይሁንላችሁ!ዒድ ሙባረክ!!
887 viewsMOR EAST, 14:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 17:12:25

984 viewsMOR EAST, 14:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 14:55:06
1.2K viewsMOR EAST, 11:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 14:54:48 ተጨማሪ ሶስት ባንኮች ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር ስምምነት ተፈራረሙ

የታክስ አሰባሰቡን አገልግሎት ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግና ደንበኛውም በኦንላይን በየትኛውም ጊዜና ቦታ ሆኖ ግብሩን መክፈል የሚያስችል ስምምነት በዛሬው ዕለት ከደቡብ ግሎባል ባንክ፣ ከእናት ባንክ እና ከቡና ባንክ ጋር የፊርማ ስነ-ስርዓት ተካሂዷል ፡፡

የፊርማ ስነ-ስርዓቱን ያካሄዱት የገቢዎች ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የየባንኮቹ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች ናቸው፡፡

በገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ የታክስ አስተዳደር ስርዓቱን ዓለም በደረሰበት ቴክኖሎጂ በመደገፍ ግልፅ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ በሆነ መንገድ ለግብር ከፋዮች አገልግሎት በመስጠት እና የህግ ተገዥነትን ከፍ በማድረግ የተቋሙን ራዕይ እና ተልዕኮ ለማሳካት የዲጂታል የገቢ አስተዳደር ስርዓት የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው የግብር ስርአቱን ይበልጥ ለማዘመን ሌሎች ባንኮችም ወደ ስርዓቱ እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ቀደም ሲል የግብር አከፋፈል ስርዓቱ እንግልት ያለበት እንደነበር ያነሱት በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ጉታ ግብር ከፋዮች ማንኛውንም አገልግሎት ካሉበት ቦታ ሆነው እንዲጠቀሙ ከአራት ዓመት በፊት ደራሽ የተሰኘ መተግበሪያ አልምቶ ወደ ስራ መግባቱን በስምምነቱ ወቅት ገልፀዋል፡፡ በዚህም ከዘጠኝ ሺ በላይ ግብር ከፋዮች እየተጠቀሙ እንደሚገኙም ነው የተገለጸው፡፡

አሁን ላይ ከ29 ሺ በላይ ግብር ከፋዮች ኢ-ታክስ ተጠቅመው ግብራቸውን እያሳወቁ ሲሆን ከ13 ሺ በላይ ግብር ከፋዮች ደግሞ ክፍያቸውንም በዚሁ የቴክኖሎጂ ውጤት አማካኝነት እየከፈሉ እንደሚገኙ የገለጹት በገቢዎች ሚኒስቴር የመረጃና ቴክኖሎጂ ማዕከል ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ማሞ ያለባንኮች እገዛ እና ጥረት ይህ ቴክኖሎጂ እውን ሊሆን እንደማይችል ተገንዘበው ሁሉም ባንኮች ለተግበራዊነቱ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ስምምነቱን የፈፀሙት የባንኮቹ ተወካዮች በበኩላቸው ገቢዎች ሚኒስቴር የሀገር ገቢ በአግባቡ እና ደህንነቱ በተጠበቀ እንዲሁም እንግልትን በቀነሰ መልኩ ለመሰብሰብ እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀው አገልግሎቶችን በኦንላይን በመፈጸም የደንበኞችን እርካታ ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት አጋዥ በመሆን ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት በሙሉ አቅማቸው እንደሚሰሩም ቃል ገብተዋል፡፡
እስካሁን ድረስ የዛሬዎቹን ሶስት ባንኮች ጨምሮ አስራ ሁለት የግል እና መንግስት ባንኮች የኢ-ፔይመንት አገልግሎት ለግብር ከፋዮች ለመስጠት ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር ስምምነት አካሂደዋል ሲል የገቢዎች ሚኒስቴር ዘግቧል፡፡
1.2K viewsMOR EAST, 11:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 14:50:16 የእርጅና ቅናሽ ስሌት ዘዴዎች

ግብር ከፋይ ለግብር አከፋፈልና ለሌላ አላማ ለሚያዘጋጃቸው የሂሣብ ሪፖርቶች በፋይናንስ ሪፖርት አቀራረብ ደረጃዎች መሠረት አንድ ዓይነት የእርጅና ቅናሽ ዘዴ መጠቀም አለበትዋጋቸው ለሚቀንስ ሀብቶች ሁሉ መጠቀም ያለበት አንድ ዓይነት የእርጅና ቅናሽ ዘዴ ነው፡፡

ሁለት አይነት የእርጅና ቅናሽ ዘዴዎች ያሉ ሲሆን
ቀጥተኛ የእርጅና ቅናሽ እና
ዋጋው እየቀነሰ የሚሄድ የእርጅና ቅናሽ ዘዴ በመባል ይታወቃሉ፡፡
ታክስ ከፋዮች የሚፈቀድላቸውን የእርጅና ቅናሽ በቀጥተኛ ወይም ዋጋው እየቀነሰ በሚሄድ የእርጅና ቅናሽ ዘዴ መሠረት ሊወስኑ ይችላሉ፡፡
ቀጥተኛ የእርጅና ቅናሽ ዘዴ
የሚከተሉት ሀብቶች የእርጅና ቅናሽ መሰላት ያለበት በቀጥተኛ የእርጅና ቅናሽ ዘዴ ብቻ ይሆናል፡፡
• ግዙፋዊ ሀልዎት የሌላቸው የንግድ ሥራ ሀብቶች፣
• በማይንቀሳቀስ ሀብት ላይ የሚደረግ ማሻሻያ፤
በማይንቀሳቀስ ሀብት ላይ የሚደረግ ማሻሻያ የእርጅና ቅናሽ ሲሰላ በማይንቀሳቀስ ሀብት ላይ የሚደረግ ማሻሻያ ወጪ ማሻሻያው ያረፈበትን መሬት ወጪ መጨመር የለበትም፡፡
ማንኛውም ግብር ከፋይ “አስተላላፊ” ተብሎ ከሚጠራ ግንኙነት ያለው ሰው ላገኘው እና በአስተላላፊው ሙሉ የእርጅና ቅናሽ ላገኘበት ዋጋው የሚቀንስ ሀብት ወይም ግዙፋዊ ሀልዎት የሌለው የንግድ ሥራ ሀብት የእርጅና ቅናሽ ማግኘት አይችልም ፡፡
ለአንድ ግብር ከፋይ በአንድ የግብር ዓመት ዋጋው ለሚቀንስ ሀብት ወይም ግዙፋዊ ሀልዎት ለሌለው የንግድ ሥራ ሀብት የተፈቀደው በቀጥተኛ የእርጅና ቅናሽ ዘዴ መሠረት የሚወሰን የእርጅና ቅናሽ መጣኔ በሀብቱ ወጪ ላይ ተፈጻሚ በማድረግ ይሰላል፡፡
ዋጋው እየቀነስ የሚሄድ የእርጅና ቅናሽ ዘዴ
• ለአንድ ግብር ከፋይ በአንድ የግብር ዓመት ዋጋው ለሚቀንስ ሀብት የተፈቀደው ዋጋው እየቀነሰ በሚሄድ የእርጅና ቅናሽ ዘዴ መሠረት የሚወሰን የእርጅና ቅናሽ መጣኔ በዓመቱ መጀመሪያ ባለው የሀብቱ የተጣራ የመዝገብ ዋጋ ላይ ተፈጻሚ በማድረግ ይሰላል፡፡
• በአንድ የግብር ዓመት ዋጋው በሚቀንስ ሀብት ላይ ተፈጻሚ ከሆነ፣የሀብቱ የተጣራ የመዝገብ ዋጋ ሀብቱ በግብር ዓመቱ የንግድ ሥራ ገቢን ለማግኘት ብቻ ጥቅም ላይ እንደዋለ በመውሰድ ይሰላል፡፡
• የግብር ከፋዩ ዋጋው የሚቀንስ ሀብት ቀሪ ዋጋ ከብር ሁለት ሺህ በታች ከሆነ በአንድ ጊዜ በወጪነት ይያዛል፡፡
• ዋጋው እየቀነሰ የሚሄድ የእርጅና ቅናሽ መጠን የሚሰላው በግብር ዓመቱ መጀመሪያ በነበረው የተጣራ የመዝገብ ዋጋ ላይ የእርጅና ተቀናሽ መጣኔውን በማስላት ይሆናል፡፡
በግብር ዓመቱ መጀመሪያ የነበረው የተጣራ የመዝገብ ዋጋ ማለት፡- ከመጀመሪያው የመዝገብ ዋጋ በየጊዜው የተቀነሱ የእርጅና ተቀናሾች ከተቀነሰ በኋላ የሚገኝ ዋጋ ነው፡፡
1.2K viewsMOR EAST, 11:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 18:13:45 ለአዳዲስ ግብር ከፋዮች የተሰናዳ ስልጠና በፓወርፖይንት
1.7K viewsMOR EAST, 15:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 15:36:30 መዝገብ የመያዝ ግዴታዎች

የማንኛውም የንግድ ሥራ ዋና ዓላማ ከሚያካሂደው የንግድ ሥራ እንቅስቃሴ ትርፍ አግኝቶ የንግድ ሥራውን ማስፋትና ማሳደግ ነው፡፡ ይህን ዓላማ እውን ለማድረግ ከሚያግዙ ተግባራት ውስጥ አንዱ መዝገብ በአግባቡ መያዝ ነው፡፡ ለታክስ ሕግ ዓላማ ሲባል አንድ ታክስ ከፋይ በታክስ ሕግ መያዝ ያለባቸውን ሰነዶች በኤሌክትሮኒክ መልክ ጨምሮ የመያዝ ግዴታ ያለበት ሲሆን እነዚህም ሰነዶች የሚያዙት በአማርኛ ወይም በእንግሊዝኛ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ እና የታክስ ከፋዩን የታክስ ግዴታ በግልጽ ለማረጋገጥ በሚቻልበት ሁኔታ መሆን አለበት፡፡ ሰነዱ በአማርኛ ወይም በእንግሊዝኛ ቋንቋ ተዘጋጅቶ ካልቀረበ በባለሥልጣኑ በጽሑፍ በሚሰጥ ማስታወቂያ በሚወስነው ጊዜ ውስጥ ሰነዱ በባለሥልጣኑ ተቀባይነት ባለው ተርጓሚ በታክስ ከፋዩ ወጪ ወደ አማርኛ ወይም ወደ እንግሊዝኛ ቋንቋ ተተርጉሞ እንዲቀርብ ባለሥልጣኑ ታክስ ከፋዩን ሊያዘው ይችላል፡፡

አንድ ታክስ ከፋይ ሰነዶችን ከሚከተሉት ረጅም ለሆነው ጊዜ፤ በንግድ ሕግ ለተወሰነው የሰነድ መያዣ የጊዜ ርዝማኔ ወይም ሰነዶቹ አግባብነት በሚኖራቸው የታክስ ጊዜ የታክስ ማስታወቂያ ለባለሥልጣኑ ከቀረበበት ቀን ጀምሮ ለአምስት ዓመታት ይዞ የማቆየት ግዴታ ያለበት ሲሆን የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች ለሶስት ዓመታት ነው፡፡ ይህ ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ለሚደረግ ክርክር ሰነዱ የሚያስፈልግ ሲሆን ታክስ ከፋዩ ሁሉም ክርክሮች እስከሚጠናቀቁ ጊዜ ድረስ ሰነዱን ይዞ የማቆየት ገዴታ አለበት፡፡
2.0K viewsMOR EAST, 12:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 19:48:19
አስቸኳይ ማስታወቂያ
2.2K viewsMOR EAST, 16:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 18:33:36
ውድ የቻናላችን ተከታዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ወደ እናንተ በሚያደርሳቸው የታክስ መረጃዎች እና ትምህርቶች ምን ያኸል ይረካሉ?
Anonymous Poll
10%
በጣም ዝቅተኛ
11%
ዝቅተኛ
51%
ከፍተኛ
28%
በጣም ከፍተኛ
1.0K voters2.0K viewsMOR EAST, 15:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 16:09:26
በመጨረሻው ምዕራፍ ለቡድን ሁለት የሞጁላር ሰልጣኞች የመመዘኛ ፈተና ተሰጠ

በገቢዎች ሚኒስቴር የምስራቅ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በመጨረሻው ምዕራፍ ለቡድን ሁለት የሞጁላር ሰልጣኞች ሰኔ 28 ቀን 2014 ዓ.ም የመመዘኛ ፈተና ሰጥቷል፡፡

የመመዘኛ ፈተና የወሰዱ ግብር ከፋዮች በ3 ምዕራፍ ተከፋፍሎ ሲሰጡ የነበሩ የታክስ ትምርቶችን በሚገባ ተከታትለው ያጠናቀቁ ሲሆኑ በምዕራፍ አንድ ከመቀጠር ሚገኝ ገቢ ግብር፣ የቤት ኪራይ እና የንግድ ስራ ገቢ ግብ እና ቅድመ ግብር በምዕራፍ ሁለት ተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ተርን ኦቨር ታክሰ፣ኤክሳይ ታክስ፣ ቴምብር ቀረጥ እና ሱር ታክስ እንዲሁም በምራፍ ሦስት የታክስ ከፋይ ምዝገባ፣ ስረዛ እና ክሊራንስ አሠጣጥ፣ ደረሰኝ እና ሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ አጠቃቀም፣ የታክስ ማስታወቅና ቅጻ ቅጾች፣ የታክስ ስሌት፣ሌሎች ክፍያዎችን ስለ ማስከፈል እና ተመላሽ አሰራር ፣የታክስ አስተዳደር እና የወንጀል ቅጣት እና ተያያዥ ጉዳዮችን የሚሉ ርዕሰ ጉዳዮችን 90 Credit Hours በሚሸፍን ጊዜ መሰልጠን ችለዋል፡፡

የገቢዎች ሚኒስቴር በ2014 ዓ.ም ከሁሉም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ተከታታይ የሞጁላር ስልጠና የወሰዱ ግብር ከፋዮችን ለማስመረቅ የተለያዩ ቅድመ ሁኔታዎችን እየከወነ ሲሆን ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ከ200 በላይ የሚሆኑ ሰልጣኝ ግብር ከፋዮችን የሚያስመርቅ ይሆናል፡፡
2.3K viewsMOR EAST, 13:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ