Get Mystery Box with random crypto!

M.O.R East Addis Ababa Branch

የቴሌግራም ቻናል አርማ moreastaddisabababranch — M.O.R East Addis Ababa Branch M
የቴሌግራም ቻናል አርማ moreastaddisabababranch — M.O.R East Addis Ababa Branch
የሰርጥ አድራሻ: @moreastaddisabababranch
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.57K
የሰርጥ መግለጫ

Ministry Of Revenues (MOR) is the body responsible for collecting
revenue from customs duties and domestic taxes.

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-07-01 10:47:04
3.3K viewsMOR EAST, 07:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 10:46:52 ከተጨማሪ ዕሴት ጋር የተያያዙ አስተዳደራዊ ቅጣቶች

• በጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ መሰረት ለጨማሪ እሴት ታክስ መመዝገብ ያለበት ሰው ሳይመዘገብ የቀረ እንደሆነ፤ መመዝገብ ከነበረበት ቀን ጀምሮ ለመመዝገብ እስካመለከተበት ወይም በባለስልጣኑ አነሳሽነት እስከተመዘገበበት ቀን ድረስ ላለው ለእያንዳንዱ ወር ወይም ከወሩ ከፊል ለሆነው ጊዜ ብር 2 ሽህ (ሁለት ሽህ ብር) ቅጣት ይከፍላል፡፡

• በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 1 መሰረት ከሚጣለው ቅጣት በተጨማሪ፤ ንዑስ አንቀፁ ተፈፃሚ የሚሆንበት ሰው መመዝገብ ከነበረበት ቀን ጀምሮ ለመመዝገብ እስካመለከተበት ወይም በባለስልጣኑ አነሳሽነት እስከተመዘገበበት ቀን ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ በፈፀመው የተጨማሪ እሴት ታክስ የሚከፈልበት ግብይት ላይ ሊከፈል ይገባ የነበረውን የተጨማሪ እሴት ታክስ 100 % (መቶ በመቶ) ቅጣት ይከፍላል፡፡

• በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 2 መሰረት የሚጣለው ቅጣት በንዑስ አንቀፁ በተገለፀው ጊዜ ውስጥ ታከስ ከፋዩ በፈፀመው የተጨማሪ እሴት ታክስ የሚከፈልበት ግብይት ላይ ሊከፈል ይገባ የነበረውን የተጨማሪ እሴት ታክስ አያስቀርም፡፡ ሆኖም ታክስ ከፋዩ በዚህ ጊዜ ውስጥ ባከናወነው ግብይት ላይ የከፈለው የተርን ኦቨር ታክስ ካለ ተቀናሸ ይደረግለታል፡፡

• ማንኛውም ሰው ሆን ብሎ ሊከፈል የሚገባውን የተጨማሪ እሴት ታክስ ለማሳነስ ወይም በግብቱ ላይ ተመላሽ የሚደረገውን የታክስ መጠን ለመጨመር በማሰብ ትክክለኛ ያልሆነ የታክስ ደረሰኝ የሰጠ እንደሆነ ብር 50 ሽህ (ሃምሳሽህ ብር) ቅጣት ይከፍላል፡፡
• ደረሰኝ መስጠት ሲገባው ያልሰጠ ማንኛውም ታክስ ከፋይ ለገዥ ባልሰጠው ለእያንዳንዱ ደረሰኝ ብር 50 ሽህ (ሃምሳ ሽህ) ቅጣት ይከፍላል፡፡

• በታክስ ማስታወቂያ የተገለጸው የታክስ መጠን ታክስከፋዩ ሊከፍል ከሚገባው ትክክለኛ የታክስ መጠን ያነሰ እንደሆነ ( “የታክስ ጉድለት” ልዩነት እና የልዩነቱን መጠን በ10% ይቀጣል፡፡ይህንኑ ከደጋገመ ልዩነቱን ከ30-50% ይከፍላል፡፡
3.0K viewsMOR EAST, 07:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 16:35:32 ማ ስ ታ ወ ቂ ያ

ለቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ግብር ከፋዮች በሙሉ

የኢ-ፋይሊንግ (e-filing) ተጠቃሚዎች የሆናችሁ ግብር ከፋዮች በሙሉ የግንቦት ወር የግዥና ሽያጭ መረጃ በTASS System Online እንድታሳውቁና መረጃውን ማቅረብ አቋርጠው ከሆነ ወደ ኋላ ያሉ ዓመታትና ወራቶች መረጃዎችን በሃርድ ኮፒ እና በሶፍት ኮፒ እስከ ሰኔ 30/2014 ዓ.ም ማምጣት/ ማቅረብ የሚጠበቅባችሁ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን።

ይህ ሳይሆን ሲቀር በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/08 አንቀጽ 114(7) መሰረት አስተዳደራዊ ቅጣት እና በአንቀፅ 126(1)(2)(3) (ሀ)(ለ)መሰረት የወንጀል ቅጣት የሚያስከትል መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ለተጨማሪ ማብራሪያ ለም ሆቴል አካባቢ በሚገኘው ኮሜት ህንፃ 5ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 503 በመምጣት ወይም በስልክ ቁጥር 011-667-48-51 /011-668-71-74 ይደውሉ፡፡

በገቢዎች ሚኒስቴር የምስራቅ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት
2.9K viewsMOR EAST, edited  13:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ