Get Mystery Box with random crypto!

መንፈሳዊ ግጥም ብቻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ mgetem — መንፈሳዊ ግጥም ብቻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ mgetem — መንፈሳዊ ግጥም ብቻ
የሰርጥ አድራሻ: @mgetem
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 20.79K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል ላይ በየቀኑ ኦርቶዶክሳዊ ግጥሞችን ያገኛሉ
.
.
.
.
.
.
.
.
ለአስተያየትና ግጥም እንዲፖሰትላችሁ የምትፈልጉ ለመላክ
@Mgetem_Bot
@Mgetem_group

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 14

2022-06-21 17:47:10

7.2K viewsK, 14:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 07:56:15 ሚተራሊዮን ትረካ
የዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ እሸቴ አምስተኛው መጽሐፍ "ሚተራሊዮን" ትረካ

ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 1



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 2



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 3



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 4



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 5



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 6



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 7



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 8



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 9



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 10


7.9K viewsSol, 04:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 08:33:05
አዲስ የምርቃት መዝሙር
«ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ»
ዘማሪ ዳንኤል ጥበበሥላሴ
ግጥም:-ዲ/ን ከሣቴብርሃን ገ/ኢየሱስ(ዶ/ር)
ዜማ:- ዘማሪ አብርሃም ድረስ
ቅንብር፦ ዲ/ን ዘላለም ታከለ(ዘጎላ ዲጂታል ስቱዲዮ
የጽምጽ አጃቢዎች -ዘማሪት ሲስተር ሕይወት ተፈራ | ዲ/ን ዘላለም ታከለ
*****በቅርብ ቀን*****
11.1K viewsK, 05:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-25 16:18:45 እስቲ ገድሉን እዚያ ያለውን እናንብ” እላቸዋለሁ። “ጥሩ!” ይላሉ ገዳማውያኑ እያበሉ ዐሥራ አምስት ቀን ወይ ሳምንት ተቀምጬ ነው እንጂ የገባሁበት ገዳም ዝም ብዬ አልሄድም። በበዓል አይደለም የምሄደው። ከተጓዦች ጋር አይደለም የምሄደው። ከዚያ ሳሊ ገበያ አጠገብ ወፍ ዋሻ የምትባል አለች። የዝማሬ መዋሥዕት መማርያ ናት። እዚያ የተማረ ዙር አምባ ሄዶ ይመረቃል። ዝማሬ መዋሥዕት አልሞከርንም።
እዚያ ጋይንት የኔታ እጅጉ የሚባሉ ዘንድ ዜማ በጥቅሉ ከአራት መምህራን ዘንድ ዜማ ተማርንና እኔም ጓደኛዬም አንለያይም። ሰባክያን ሲሰብኩ ምን ሲሉ ደስ አለን። መንፈስ ቅዱስ መራን። ትርጓሜ ለመማር ደሞ የት እንሂድ ብለን አየን። እዚያም መካነ ኢየሱስ ነበሩ አንድ ታላቅ አባት። አባትህ እዚያ ተምረዋል መልአከ ምሕረት። የትግሬ ሰው ናቸው። የኔታ ገብረ ጊዮርጊስ ነው ሚባሉ። የቅኔና የመጽሐፍ መምህር ናቸው። አዪ! ወንበር አይደርስም። በዚህ ላይ ሰውየው ጸሎተኛ ስለሆኑ ወደ ቅኔ ማስነገሩ እንጂ ወደ መጽሐፉ አይደሉም። ስንጠይቅ “መጽሐፍ ድሮውንም እዚህ አይደለም ሂዱ ጎጃም ዲማ” ተባለ።

ቅኔስ።

መርጡለማርያም ጥሩ የሆኑ አባት ነበሩ። አለቃ ኢሳይያስ ይባላሉ። ዋድሌ ናቸው። መምህር የሆኑ ፤ አባት የሆኑ በእውነት! ትንቢተ ኢሳይያስ ናት ልጃቸው። ቅኔ ትቀኛለች። አታሲዝም። ትንቢተ ኢሳይያስ ነው ስሟ። እዚያ ገባን። እዚያም ደግሞ አሁን ግብረ በላ ነኝ እኔ። አይለቁኝም በእድሜ ስላነስኩኝ። ሌላ የለም እኮ አዪ እኔ ደሞ ወደ ትምህርት ስል ዛሬ ቅፈፋ ሲሉ አዪ እላለሁ። ጓደኛዬ ይሄዳል ያኔውኑ። የእኔንም ለእርሱ ስጡ ብዬ ለመንደሮቹ ስላሳወቅኩ ይሰጡታል የሁለታችንንም እንጀራ። የሚሰጡት ምንድነው ለእኔ ሲባል ቅርብ ቦታ መደቡኝ። ለእኔ አምስት ቤት ለእርሱ አምስት ቤት ዐሥር ቤት። ከዐሥር ቤት አንዳንድ እንጀራ እየታጠፈ ነው ሚሰጠው። ጨው ስጡኝ ካለ አንዳንድ ጭልፋ ጨው ይሰጣሉ። ጨው ማለት እዚያ ድልህ ነው። ያንን ይዞ ይመጣል። “አዪ እንጀራ በጨው አይደለም ና ና አንተ” ይሉኛል። ልክ እንደ የኔታ ይኄይስ አሁንም እዚህ ግብረ በላ ነበርኩ። የኔታ እጅጉ ቤት ግብረ በላ አይደለሁም። ወንድሜ ያመጣል እንጀራ። እንዲያው አንዱ የገብስ እንጀራ እንኳን ለሁሉ ይበቃል። መንደራቸው የራቀ ልጆች ይሳተፋሉ ከእኛ ጋር። እንግዳ ሲመጣ እናሳትፋለን። እግር አጥበን ራት ሰጥተን እናበላለን። የኔታ እጅጉ ቤት አልበላሁም። የኔታ ምትኬና ሸዋ ላይ የጠቀስኳቸው መምህራን ንባብ ያስተማሩኝ ጋርም አልበላሁም። ወላጆቼ አካባቢ ስለሆነ አንጎለላ መምሬ ዳምጤም አያቴ ቤት አጠገብ ስለሆኑ ቤቴም ቅርብ ስለሆነ እንጀራ ከቤቴ ነው ምበላው። አንጎለላም ደጀ ሰላም ሁሉ አለ አልሄድም። ልምድ የለኝም የደጀ ሰላም። ከዚያ እንግዲህ በየዓመቱ ደብረ ሊባኖስ አንቀርም እኔም ወንድሜም።

እንግዲህ ቅኔ የኔታ ኢሳይያስ ዘንድ ግሩም በሚያሰኝ ሁኔታ ተቀኘሁ። እዚያ ብሉይ መጻሕፍትን ተማርኩ። “እማራለሁ እይዛለሁ አይ የኔታ ይጠይቁኝ እንጂ እኔ ይኼንን ሁሉ በቃል ሳጠና አልገኝም። በቃል ለምን አጠናለሁ እኔ መጽሐፍ አለ አይደለም ወይ? ያስረዱኝ ይጠይቁኝ” እላቸዋለሁ። ደስ ይላቸዋል በቃ። ከዚያ ጀምሮ ነው እንግዲህ በቃል ትምህርት ላይ ያለኝ አቋም እንዲያ የሆነው።
በዚህ ሁኔታ አራቱን ብሔረ ነገሥት ስምንቱን ብሔረ ኦሪት የኔታ ኢሳይያስ ዘንድ ከቅኔ ጋር እኔና ወንድሜ ተምረን እዚያ እንግዲህ ዜማ ተውን። ዜማ ለምን ተዋችሁ ብለኸኝ ታውቃለህ? የተውኩበትን ምክንያት ነግሬአችኋለሁ? አልነገርኳችሁም።
አሁን ከአንጎለላ ጀምሮ በደቡብ ጎንደር የተማርኩት የቤተልሔም ዜማ ነው። ቁሙ ማለት ነው። አቋቋም አልተማርኩም። አቋቋም መማር ከቅኔ በኋላ ስለተባለ ወደ ጎጃም መጣሁ ማለት ነው። የኔታ ገብረ ጊዮርጊስ ዘንድ ብንሄድ ወንበራቸው ፈጣን አይደለም። ዋልን አደርንና እንዲህ ነው ሚማሩት አዎ አይ እንሂድ አልን መርጡለማርያም መጣን ኢሳይያስን አገኘን። ባለቤታቸው እንዴት ያሉ ናቸው። እንዴት መጣችሁ ወንድሞች አሉ። የት ናችሁ ሸዬዎች ናችሁ አሉ። ያውቁናል በመልካችን ባነጋገርም።
“እንዴት መጣችሁ?”
“ኧረ እንዲያውም ጋይንት ድረስ እንዲህ ሄደን ነበረ።” ብለን ስንላቸው ገረማቸው።
“አንተም እዚያ ሄድክ?”
“አዎ”
“አዪ ቅኔ ለመማር ነው?”
“አዎ”

ጭናቸውን መታ መታ አድርገው ቅኔ ሲጀምሩ ቀድመን እንገኛለን። የቅኔው ተማሪ ሲሄድ መጽሐፍ ያስተምራሉ። ቁጭ!
“ምነው?”
“እኛም እንማራለን!”
እንዳጋጣሚ ኦሪት የጀመሩ ነበሩ። ከነእርሱ ጋር ሄድን። ዳዊትን ከጨረስን በኋላ መጽሐፈ ነገሥት ከተማርን በኋላ ሐዲሳት ልንማር ብለን ቅባቶች ናቸው እዚያ ያሉት።
ዜማ የተውንበት ምክንያት ይኽ የጎጃም ዜማ አጫብር ፣ ወጨሬ ሦስተኛም አለ ስሙ ጠፋኝ እንዲህ ያለ ነው። ርዝመቱ አንጀት ይበጥሳል። ዜማው ጥሩ ነው። ግን ማይዘለቅ ነው ርዝመቱ። ልብ ያፈርሳል። ወረብም ስንገባ ለመወረብ የጎንደሮች አጭር አጭር ናት።
የነሱ እንደዚያ ሲሆንብን ዜማ ተውን ተውን ተውን!

ከዚህ የቀጠለውንና የተረፈውን በEOTC TV ከተላለፈው የአንደበታቸው ምስክርነት ያድምጡ።
13.1K viewsK, 13:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-25 16:18:45 የመጋቤ ምሥጢር መሠረት ተሰማ የንባብና ዜማ ትምህርት ሕይወት ፤ በራሳቸው አንደበት ሲተዘት
፨፨፨፨፨፨፨፨፨

አርታኢ ወአስተጋባኢ፦ዲ/ን ከሣቴብርሃን ገ/ኢየሱስ


መንደርደሪያ

ታኅሣሥ ፳፪ ቀን 2013 ዓ.ም
ከኮሮና አመጣሽ የዘጠኝ ወር አሰልቺ እረፍት መልስ የተጀመረው ትምህርት እየተጧጧፈ ያለበት ጊዜ በመሆኑ እኔም ሆነ ወንድሜ አብነት የተወጣጠረ ጊዜ ላይ እንደነበርን አስታውሳለሁ።
ይህ አስቸጋሪ ወቅት ሊቁ መምህራችን እንደልብ ለመጠየቅ አላስቻለንም። እንዲህ ባለው ጊዜ ነው እንግዲህ “ባስቸኳይ እፈልጋችኋለሁ” የሚል መልእክት በልጅ ልጃቸው ዲያቆን ናታን በኩል የተላለፈልን።

እንዲህ ያለ አስቸኳይ ጥሪ ስላልተለመደ ወዲያው ወደ ቤታቸው ሄድን። ከሳሎኑ ስንገባ ከሳሎኑ ስንገባ በተለመደ ሞቅ ያለ ሰላምታ ተቀበሉን። እንደሌሎቹ ጊዜያት ግን ትንሽ ትልቅ በማይመርጥ ትኅትና ቆመው ለማስተናገድ ቤት ያዋላቸው መጠነኛ የእግር ሕመም አላስቻላቸውም።
ከዚህ በኋላ ያሉን ነገር ቃል በቃል አይረሳኝም።

“እንግዲህ ነገ የሚፈጠረው ነገር አይታወቅም። እናንተ የመጨረሻ ልጆቼ ናችሁ። ይኼን ሁሉ ጊዜ ደክማችሁ አንድ ነገር ብሆን ልፋታችሁ ከንቱ ሆኖ እንዳይቀር የተማራችሁትን ዘርዝራችሁ ጽፋችሁ እንድታመጡልኝና የምስክሩን ወረቀት እንድሰጣችሁ ነው የጠራኋችሁ። እሱን ከያዛችሁ እንግዲህ አቅም እስከፈቀደና ነፍስ እስክትወጣ ድረስ ትቀጥላላችሁ።” ነበር ያሉን።

በጊዜው ንግግሩ ከማስደንገጥ ይልቅ አስገርሞን ነበር። ”ትንሽ እግራቸውን ያዛቸው እንጂ አሳሳቢ የሆነ የጤና እክል አልገጠማቸውም። ለምን እንዲህ አሉ?” ብለን ግራ እንደ መግባት አለን። ወዲያው ግን መምህር ደረጀ ከ4 ወይም ከ5 ወር በፊት የጉባኤ ቤታቸውን(በኋላ መካነ መቃብራቸውን) ሁኔታ እንዲመለከትና ጥገናም ያስፈልገው እንደሆነ እንዲያየው ያደረጉትን ነግሮኝ “እኚህ አባት ምን ታይቷቸው ነው?” ያለኝን አሰብኩና “ምናልባትም ለበቁ አበው ቀድሞ የሚሰጥ ነገር አለ።” በሚል እምነት የታዘዝነውን ግዴታ ፈጽመን ከ2 ቀን በኋላ ታኅሣሥ ፳፬ ቀን የምስክር ወረቀቱን ይዘን ሄድን። ጽሕፈቱን በሚገባ ተመልክተው ሁሉም ሳይጓደል መካተቱን ካረጋገጡ በኋላ “የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ማኅተም በቅድሚያ ማረፍ አለበት። ሂዱና አስመቱ” ብለውን ያንን አስደርገን ከሁለት ቀን በኋላ ተመልሰን በመምጣት የራሳቸውን ማኅተምና ፊርማና ማኅተም አኑረውልን ሁለቱን ኮፒ ለእኛ ቀሪውን ሁለት ኮፒ ለራሳቸው ካስቀሩ በኋላ እንዲህ አሉ።

“እንኳን ደስ አላችሁ። ይኼን በብዙ ድካም የጨረሳችሁት መንፈስ ቅዱስ ስላበረታችሁ ነው። እኔም ደግሞ በተጋድሎ ሳይሆን ሥራዬ ግዴታዬ ስለሆነ ጤንነት ሰጥቶኝ እኚህን ዓመታት (5 ዓመታት) ማንም የማያገኝውን ዕድል መንፈስ ቅዱስ ሰጥቷችሁ ተማራችሁ። ወንጌልን ብቻ ለመማር አምስት ዓመትም የማይጨርሱ አሉ። እናንተ ግን ሐዲሳትን ሙሉ ትርጓሜያቸውን ከብሉይ የዳዊትን ትርጓሜ አጠናቃችሁ እንዲያውም ቅዳሴንና ሃይማኖተ አበውን ጨምራችሁ እዚህ ደርሳችኋል። ታዲያ እናንተ እዳ አለባችሁ። ‘በከንቱ የተቀበላችሁትን በከንቱ ስጡ’ ይላልና ቃሉ።”
ይኼን ካሉ በኋላ ለእኛ በከንቱ የሰጡትን ዕውቀት በከንቱ የሰጧቸውን መምህራን ሊዘረዝሩ ፣ የአብነት ትምህርት ሊተርኩ ገቡ። እኔም ይኼንን እንደወረደ ምንም ማሻሻያና ጭማሪ ሳላደርግ አቅርቤዋለሁ።
ልክ መንግሥቱ ለማ ለ48 ሰዓት ከሊቁ አባታቸው ጋር ያደረጉትን ቃለ መጠይቅ ምንም ሳይጨምሩ ቃል በቃል “መጽሐፈ ትዝታ ዘአለቃ ለማ ወልደ ታሪክ” ብለው እንዳሳተሙት በተለይ የመጋቢን አንደበተ ርቱዕነትና የቋንቋ አጠቃቀም ፣ የጊዜውንም መንፈስ በሚገባ ያሳያልና ይልቁንም በEOTC TV ላይ ከተላለፈላቸው በራሳቸው አንደበት ከተገለጠው የሕይወት ታሪክ አንጻርም ዘርዘር ያለ ገለጻ ያለው በመሆኑ ሰፊ ግንዛቤ ያስጨብጣል ብዩ አምናለሁ። ከዚህ ቀጥሎ ያለው ሙሉ በሙሉ የእሳቸው ቃል ነው።



ተቀምጦ ማስተማር

እኔ ለአባቴ ለአስተማሪዬ ትንሽ ልጅ ሆኜ እንደ በኵር እንደ በኵረ ተማሪ እቆጠር ነበር። የመጽሐፍ መምህሬን። እጃቸውን ይዤ አብሬያቸው ተቀምጬ ነበር ምውል። ያ ነው አሁን እኮ ተቀምጦ ተማሪዎችን ለማስተማር የረዳኝ የልጅነቴ ጊዜ ሁኔታ ነው።
ያኔ መቀመጥ ያልተማረ ልቅሶ መሄድ ሠርግ መሄድ ሚያበዛ ዛሬ መቀመጥ አይችልም። እኔ ልቅሶ አልሄድም። ሠርግ አልሄድም።የታመመ አልጠይቅም። የታሠረ አልጠይቅም። አስተማሪ ነኝ አስተምራለሁ።



ንባብ ዜማና ቅኔ

ስንት መምህራን ዘንድ ተምሬያለሁ? ንባብ ከተማርኩባቸው መምህራን የመጀመርያው የተከበሩ አባት መምሬ ዳምጤ ገብረ ጊዮርጊስ ናቸው። ከፊደል ጀምሮ ዳዊት ያስደገሙኝ። በጥቂት ጊዜ ውስጥ። “እንደገና ዳዊት ደግሞ መከለስ አለብኝ እነ አርጋኖን እነ ሌሎችም ንባብ ማስፋፋት አለብኝ” ብዬ ያስተማሩኝ ክቡራን አባቶቼ መምሬ ሣህሌ አባ ፋንታዬ አባ ገብረወልድ ጠቅላላ ከእኚህ አራት አባቶች ዘንድ ንባብ ከጨረስኩ በኋላ እዚያው የተወለድኩበት ሃገር አንጎለላ መጣሁ። እንደ እድሌ ሆኖ ከንባብ በኋላ በዜማ ቤት በመጽሐፍ ቤት ያስተማሩኝ መምህራን ዓይነስውራን ናቸው። ሦስቱ።
ከዚያ አሁን ዜማ ፤የቤተልሔም ዜማ ይባላል፤ የኔታ ምትኬ ዘንድ። አባቴ እንድማርለት ይወዳል። እዚያችው ቤተክርስቲያን አጠገብ አክስት አሉኝ ፤ ወይዘሮ አስካለ ገብረሕይወት የሚባሉ ፤ እንደ በግ እየጠበቁኝ ሲያገኙኝ እዚያው ሲያገኙኝ
“አለ?”
”አዎ”
“ይማራል?” እያሉ እየተቆጣጠሩኝ የኔታ ምትኬ ጋር ቀጸልኩ።
ዓይነ ሥውር ናቸው የኔታ ምትኬ። ከየኔታ ምትኬ ዘንድ ደግሞ ጾመ ድጓ ጀመርኩና የቃል ትምህርት የሚባል አለ። መስተጋብዕ። ከሰኞ እስከ ዓርብ ድረስ። ጾመ ድጓ ጀምሬ ልጆች እንሂድ ሲሉ ጅሩ ዳዋ የሚባል ሃገር አለ ሃገራችን። ዳዋ ኢየሱስ ይባላል። አለቃ ወልደ አብርሃም ዘንድ። አለቃ ወልደ አብርሃምም ዓይነ ስውር ናቸው። እሳቸውም ደግሞ ዘንድ ጾመ ድጓ ስናጋምስ እንሂድ ተባለና በጌምድር ። ጎንደር ማለት ነው። ሰሜን ጎንደር። ገና ዓባይን ሻገር ስንል ምክሬ ማርያም የምትባል አለች። እሷ ጋር የኔታ ይኄይስ የሚባሉ አሉ። በጣም በጣም በጣም ግሩም የሆኑ መምህር ናቸው። መንደር ሰጥተውን እንደ ወንድሜ የሆነ ጓደኛዬ አለ። የማንለያይ። አብረን ስንሄድ ለእርሱም ስም ለእኔም ስም አውጥተው እሱን ዜናዊ እኔን ጸዳለብርሃን ብለው ሰይመው እኔን በተለይ ባለቤታቸውም ሆኑ እሳቸው በጣም ይወዱኝና ያቀርቡኝ ነበር።መምህር ናቸው። ጸሐፊ ናቸው። እማራለሁ እላቸዋለሁ።ለምሳ ሲገቡ “ና እንጀራ ብላ” ይሉኛል “አልበላም የኛ እንጀራ ምን ሁኖ ነው” እላቸኋለሁ። ያመጣላ ዜናዊም። በግድ ያስገቡኛል። እና እዚያ ሳልለይ ከማዕዳቸው ተምረን ጾመ ድጓ ዘለቅን። የቃል ትምህርት ክሥተት አርያም የሚባል አለ መወድስ ያንን ሁሉ ተማርንና እንደገና አሁን ደጋ ወጣሁ ጋይንት። ይኼ ቆላ ነው። አንዳቤት ይባላል። ሰሜን ጎንደር ነው ይኼም። ከዚያ ከአንዳቤት ምክሬ ሐናን ለቀቅሁና የጥጆ ማርያም የምትባል ዙርአምባ የሚባል የአቡነ አረጋዊ ገዳም አለ። ከዚያ በአፋዛዥ ናት። የገዳሙን ተራራ እንደዚህ እንደ ጭላሎ ተራራ ነው ምናየው። የሁለት ሰዓት መንገድ አይሆንም በእኛ አካሄድ። ሂጀ አልሳምኩም እዚያ። ጓደኛዬ ሄዶ “ዙርአማባ የተባለውን ዞረን አይተን መጣን።” ይለኛል። ግድ የለኝም እኔ። እንደ አጋጣሚ ሲሆን ብዙ ገዳሞችን ረግጫለሁ። “ይኼ ገዳም ማነው?” “እገሌ ይባላል” “ፍቀዱልን
10.8K viewsK, 13:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 21:38:38 I'm on Instagram as @kesatebirhanzetewahdo. Install the app to follow my photos and videos. https://www.instagram.com/invites/contact/?i=ejmta97uag4s&utm_content=bu74q8u
9.8K viewsK, 18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 09:12:30 ሚተራሊዮን ትረካ
የዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ እሸቴ አምስተኛው መጽሐፍ "ሚተራሊዮን" ትረካ

ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 1



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 2



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 3



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 4



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 5



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 6



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 7



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 8



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 9



ሚተራሊዮን ትረካ ክፍል 10


5.3K viewsSol, 06:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ