Get Mystery Box with random crypto!

መሢሑ ኢየሱስ ክርስቶስ

የቴሌግራም ቻናል አርማ mesiwueyesus — መሢሑ ኢየሱስ ክርስቶስ
የቴሌግራም ቻናል አርማ mesiwueyesus — መሢሑ ኢየሱስ ክርስቶስ
የሰርጥ አድራሻ: @mesiwueyesus
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196
የሰርጥ መግለጫ

“እርሱ አስቀድሞ የራሱን ወንድም ስምዖንን አገኘውና፦ መሢሕን አግኝተናል አለው፤ ትርጓሜውም ክርስቶስ ማለት ነው።”
— ዮሐንስ 1፥42
ክርስትና ማለት ክርስቶስ ነው ክርስትያን ነኝ ካሉ መኖር ነው ክርስቶስ ለኛ ሲል ከሞተ እኛ ለሱ ስንል መኖር ነው::

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-04-19 15:48:56 https://www.facebook.com/100060217009604/posts/379068200777077/
80 views12:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-14 08:59:10 ➨ አለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር እግዚአብሔር በእኛ ላይ አላማ ነበረው።
➨ ወላጆቻችን ሳንወለድ በእኛ ላይ አላማ ይኖራቸው ይሆናል። አላማቸው ግን ስሜን ያስጠሩልኛል የምል ይሆናል።

➨ እርሱ የህልውናና የስም መገኛ ነውና እጠፋለሁ ብሎ ስሙን እናስጠራ ዘንድ አልፈጠርንም።
ገና ህልውናና ስም ሳይጀመር ወደደን።
➨ ከመፈጠራችን በፊት የወደደን
ከመገኘታችን በፊት የመረጠን
ወላጆቻችን ሳያውቁን ያወቀን ወላጆቻችን ሳይወለዱ የወደደን ድንቅ አምላክ ነው።

➨ ወላጆቻችን ተወልደን ብያዩን ሳሱልን፣
እሱ ግን ደም ሳይረጋ አጥንት ሳይሰካ ከማኅፀን ህልውናችን ሳይጀመር ወደደን።
➨ ወላጆቻችን አድገን ቁም ነገራችንን መዝነው ወደዱን።
➨ እሱ ግን ገና ደግና ክፉ ሳንሰራ ዓለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር አፈቀረን።

➨ ከዓለም በፊት ወዶናልና ዓለም ሲያልፍም ይወደናል።
ከዘመን በፊት ወዶናልና ዘመን ሲታጠፍም ይወደናል።
ከዓለም በፊት ግዜ አልነበረም ➨ከጊዜ ውጪ ወዶናልና ፍቅሩ በግዜ የማያበቃ ዘላለማዊ ነው።

ጸጋ ይብዛላችሁ
124 views05:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-05 18:12:04 የጽድቅ እውነት፦

•  ጽድቅ በሂደት የሚመጣ መንፈሳዊ #ብስለት አይደለም!!

• ጽድቅ ወደ ፊት የምንደርስበት #ግብ አይደለም!!

• ጽድቅ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስን ከሙታን እንዳስነሳው #በማመን ብቻ ይገኛል!! (ሮሜ 4፥24-25)

• ጽድቅ በእምነት የተቀበልነው #ስጦታ ነው እንጂ ሽልማት ወይም የሥራችን ክፍያ አይደለም!!

• ጽድቅ ፍሬዎች አሉት እንጂ ፍሬ አይደለም!! (ፊልጵ. 1፥9-11)

• ጽድቅ ትምህርት ወይም የሆነ አስተሳሰብ አይደለም!!

• ጽድቅ በክርስቶስ ሆነን የሆነው ማንነታችን ነው!! (2ቆሮ. 5፥21)

• ጻድቃን ብቻ አይደለንም፤ የእግዚአብሔር ጽድቅም እንጂ!!

• መንግሥተ ሰማያት ጠቅለን ስንሄድ አሁን ከሆነው የበለጠ ጻድቃን አንሆንም!!

• በክርስቶስ ያገኘነው ጽድቅ በእኛ መልካም ሥራ የሚጨምር፤ ከእኛ ድካም የተነሳ የሚቀንስ አይደለም!!

• አሁን በእግዚአብሔር አቆጣጠር ክርስቶስ ኢየሱስም እኛም የእግዚአብሔር ጽድቅ ነን!!

• ጽድቅ ግለሰብ (Person) ነው፤ እርሱም፦ በሥጋ የተገለጠው አምላክ ክርስቶስ ነው!! (1ቆሮ. 1፥30)

ጸጋ ይብዛላችሁ
102 views15:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-05 17:37:32 የመባረካችን እውነታ


ቤተክርስቲያን #ሄደህ_ሊነገርህ የሚገባው መባረክህ፣ መወደድህ፣ #መመረጥህ፣ #መጽደቅህ ነው!! #በክርስቶስ_የሆነን ሰው "የዘር መርገም አለብህ" ማለት የዘሩን የጥራት ደረጃ አለማወቅ ነው! #የተባረክነው_ሊረገም #በማይችል_ማንነት ነው! የተወለድነው ሊጠፋ ከማይችል ዘር ነው!

• #በክርስቶስ_የተባረከ_በምንም #ሊረገም_አይችልም!

እስራኤል ገና ተስፋውን እንኳን ይዞ ... መረገም አልቻለም።

“ እግዚአብሔርም በለዓምን፦ ከእነርሱ ጋር አትሂድ፤ የተባረከ ነውና ሕዝቡን አትረግምም አለው።”
  — ዘኍልቁ 22፥12

#እነርሱ ተስፋ ይዘው መረገም ካልቻሉ እኛ በእርሱ ውስጥ ሆነን ልንረገም አንችልም!

• ቤተክርስቲያን የእባቡን ትምህርት ማስተጋባት ማቆም አለባት!

#የሰይጣን_ሽንገላ #በክርስቶስ #የሆንከውን #እንዳልሆንክ፣ #የተሰጠህን እንዳልተቀበልህ ማንጸባረቅ ነው። በዚህ ዘመን በሚያሳዝን ሁኔታ አማኞችን "#እርግማን_አለባችሁ፤ ኑ #ልስበርላችሁ" #ማለት_የእርግማን #ሰብራ_ኮንፍረንስ_ማዘጋጀት ተለምዷል። #ከዚህ የሚከፋው #የሚበልጣቸው አገልጋይ ጾምና ጸሎት ይዘው የሚረግሙ አሉ። ሰይጣን ምን ያህል እያታለለ እንዳለ አስተዋላችሁ?

እውነቱ ግን ... #የተባረከ_አይረገምም! #የተባረከ_ይባርካል #እንጂ አይረግምም! ክርስቶስ እርግማን ሆኖ እርግማንን #ሰብሯል #የሚለው ቃል የታመነ ነው።

“በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማን ሆኖ ከሕግ እርግማን ዋጀን፤” — ገላትያ 3፥13

ጸጋ ይብዛላችሁ
81 views14:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-30 00:02:15 እንዲያው #በጸጋው መጽደቅ!!

"ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤ በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ።" (ሮሜ 3:23-24)

የአዳም ልጆች ሁላችንም በኃጢአት ተጠያቂ ነበርን! በዚህም ምክንያት የእግዚአብሔር ክብር ጎድሎን ነበር! ጌታችን ኢየሱስ በሠራው የቤዛነት ሥራ በኩል ለኃጢአታችን ሙሉ ይቅርታ አግኝተናል! ምንም መሥራት ሳይጠበቅብን በእምነት ጸድቀናል! አሁን የእግዚአብሔር ክብር በእኛ ዘንድ ተገኝቷል። በልጁ ሥራ ከብረናል!!
84 views21:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-27 13:07:47 እርሱ ያልበደለ ሳለ የኛን በደል ተሸክሞ ሲሞት እኛ ግን የገዛ ጥፋታችንን ማመን ተስኖናል። እርሱ ለጠላቶቹ ይቅርታ ሲለምን እኛ ግን ወዳጆቻችንን መውደድ አቅቶናል።

የእኛ ፍቅር እንደ ጠዋት ጤዛ ሲረግፍ የእርሱ ፍቅር ግን እንደ ጸኑ ተራሮች ዛሬም ቀና ሲባል የሚታይ ነው። ብዙ ወዳጆች ቀየርን፤ እግዚአብሔርን ግን የሚተካ አላገኘንም። ብዙ ደጆች ደርስን ስንመለስ ተዘጉ፤ እግዚአብሔር ግን በእኛ ላይ በሩን አልዘጋም።

በብዕር ፍቅሩን የሚገልጥልን ወዳጅ አጥተናል፣ በደም ነጠብጣብ እወዳችኃለሁ የሚለንን ውድ ግን አግኝተናል።

<<ጌታ ሆይ ምን ያህል ትወደኛለህ?>> ብንለው። የእሾህ አክሊል የደፋውን ራስ፣ ችንካር የነደላቸውን እጆች፣ በጦር የታመሰውን ጎኑን፣ በአየር ላይ የተጠለጠሉትን እግሮች ያሳየናል። እኛስ እንወደዋለን? መልሱ ለእናንተው ይሁን

ዲያቆን አሸናፊ መኮንን
88 views10:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-21 11:11:42 በመሰቀል ላይ የሞተውን ማመን።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

#ለንግስናው_ዙፋን_መሰቀል #የመረጠው_በትረ_መንግስትና #የወርቅ #ካባ የለው_እርቃኑን ተሰቅሎ #ተጠማው_እያለ የናዝሬቱ ኢየሱስ #እዳዬን ከፈለው የናዝሬቱ ኢየሱስ እዳዬን ከፈለው

#ዓለም_ገዳይን እንጅ ሞችን አታምንም
አሳዳጅን እንጅ ተሳዳጅን አታምነውም
#ዓለም_ገሎ_ፎካር_ናት አጥፍቶ ጥፊ ናት

#በመሰቀል_ላይ_የሚሞትን_ማመን_ግን ዋጋ ያሰከፍላል። አዳኝ ነው የአብ ልጅ የሃጢያት መዳንት ነው ብሎ ማመን ሞኝነት የመሰላል። #እንደ እውነቱ ከሆነ ግን #ከሰማይ በታች ለሃጢያት #ሞትና ደሞዙ በመሰቀል ላይ የሞተውን እመኑ ተብለናል። #የሚሞትን ማንም አያምንም የሚገልን #ማመን #ለዓለም_ቀላል ነው። #ዓለም_ገላ_ስትፎክር_ኢየሱስ_ሞትን ገሎ ፎካሪ ነው ሞት ሆይ መወጋ የታለ #ያለው_የትንሳኤ_መጀመሪያ ነው።

#አሁን_በበረት_ተወልዶ_በመሰቀል ላይ #የሚሞትን_ማን_አዳኝ_ነው ብሎ ያምናል? #አንዴ_ከአብ_ዘንድ_ወጥቼ #መጣቻለው ይላል #አንዴ_የሰው_ልጅ #ልሞት_ይገባል ይላል። አንዴ #የህይወት እንጀራ እኔ ነኝ ብሎ #በዛው #አፉ_ራበኝ_ይላል_ወደኔ #የሚመጣ ከቶ #አይጠማም_ብሎ_መሰቀል_ላይ #ተጠማው_ይላል፣ #ማን_ይህን ያምናል? #እሱ_ግን_የተሸነፍ_መሰለ #እሱ_በእሱነቱ_ዘላለማዊ_ነው #የክብር #ጥግ_የፍጥረታት_መጋቢ ነው። አለ #ሳይሉት_የኖረ_ሳይጣላ_አሸናፊ_ሳይዋጋ ድል ነሺ #ዙፋኑን_ድንጋይ_ሳይወቅር የሰራ #ሰማይን ያለ #መሶሶ_ያቆሜ #ወርቅ_ሳያቀልጥ #መንገዱን #የዘረጋ #ሰማይናምድርን_ሞልቶ #የተረፈ #የእውቀት_ሁሉ ምንጭ #የጥበብ #መጀመሪያ ነው።

እሱ በወልደቱ አማኑኤል ነው አማኑኤል ከእኛ ጋር ሆነ። በሞቱና በትንሳኤው በእኛ ውስጥ ሆነ።

#ገሎ_የሞተ_እንጅ_ለገዳዎች_የሞተ #አይተን ሰመተን አናውቅም #እሱ_ግን #የመጨረሻውን_ሞት_ያውም_የመሰቀል #ሞት #እየሞተ_ለገዳዎች_ምህረት #አድራጊ_ነው። #ምህረት ከርሱ #ውስጥ_ይፈልቃል_ምህረት_ዓለሙን #ለማዳን_ተሰቀለ። #እሱ ክብር ነበር፣ክብር ነው ክብር፣ክብር ልያለብሰን ተሰቀለ። #በመሰቀል ላይ የዋለው #በአብ_ዙፋን የምያሰቀምጥ ነው እሱ #የአብ_ወሬ ነው_አብ_የምያወራው በርሱ ነው #የምወደው ልጄ እሱ ነውና እርሱን ስሙት አለን።

#በመሰቀል_ላይ_የሞተውን_ማመን #የአብ ልጅ ሆኖ መኖር ነው በመሰቀል ላይ የሞተውን ማመን የእግዚአብሔር ጽድቅ ሆኖ መገለጥ ነው በመሰቀል ላይ የሞተውን ማመን አድስ ፍጥረት መሆነ ነው በመሰቀል ላይ የሞተውን ማመን በመንፈስ ቅዱስ መታተም ነው። በመሰቀል ላይ የሞተውን ማመን በሞት ላይ መሳቅ ነው።---------

ሞቶ ነበር እንጅ ሞቶ አለቀራም!
95 views08:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-21 08:45:36 #ከኢየሱስ )_ውጭ_መንገድ_ከታየን #እየታወርን_ነው!!


#ኢየሱስ_የሆነ_መንገድ_አልጠቆመም፤ #የነገረን_ራሱ #መንገድ መሆኑን ነው!

❝ ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።❞ —ዮሐንስ 14፥6።

ኢየሱስ "#መንገድ" ነኝ ሲል ማለፊያ መንገድ አይደለም፤ #መድረሻም እንጂ!! ሕይወት ነኝ ሲል የሆነ ጊዜ የሚቆም #ሕይወት አይደለም!! እውነት ነኝ ሲል የሆነ አስተሳሰብ አይደለም!!

ኢየሱስ አሁንም ህያው #መንገድ ነው፤ በእርሱ ሥራ ነው ወደ አብ ሙላት የገባነው! በእርሱ ነው ልጅነት እና ክብር ያዬነው! #ከኢየሱስ #ውጭ #መንገድ #ከታየን #እየታወርን ነው! ከእርሱ ውጭ ገባን የምንለው እውነት ካለ እየሳትን ነው! ከእርሱ ውጭ ሕይወት ያለ ከመሰለን እየሞትን ነው!

ኢየሱስ ዛሬም #እውነት ነው፤ #የዘመን #መብዛት አያስረጀውም! እርሱን የሚያስጥለን አዲስ እውነት የለም! መንፈስ ቅዱስ የመጣው በየዕለቱ ራሱን ኢየሱስን #ሊያበራልን ነው!

#ኢየሱስ የማይጠፋ ሕይወት ነው፤ ሕያዋን የሆነው በእርሱ ነው! #ሞትን የተሻገርነው በእርሱ ነው! ኢየሱስ እንዳለው ሕይወት ሆኖልናል፤ በዝቶልናል!

#በእርሱ_ወደ አብ ስንመጣ አብ ጋር ሆኖ ተቀበለን፤ #እርሱ_መሄጃ ብቻ #ሳይሆን_መድረሻም_ነው፤ ኢየሱስ መግቢያ ብቻ ሳይሆን መኖሪያም ነው!
80 views05:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-19 14:20:32 የተከተለነው ኢየሱስ


“ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰላቸው፤ “እውነት እላችኋለሁ የምትፈልጉኝ እንጀራ ስለ በላችሁና ስለ ጠገባችሁ እንጂ፣ ታምራዊ ምልክቶችን ስላያችሁ አይደለም።”
— ዮሐንስ 6፥26 (አዲሱ መ.ት)

#ክርስትና_መከተል_ነው ታድይ_ስንከተል #ያስከተለን_አካል አለ ማለት ነው በመከተል ውስጥ ማስከተል አለ #ሐዋርያት የተከትሉት ተከተሉኝ ያላቸውን አስከታይ አግንቶ ነው የሚያስከትል ብቃትና ችሎታ አልነበራቸውም


#ዓለም_ስትመርጥ _መስፈርት አስቀምጣ ነው መስፈርት የሌላት ዓለም በመስፈርት ትመርጣለች #መስፈርቱን #ያላሟላ አይመረጥም።

#ኢየሱስ #ስያስከትላቸው ከላይ የተላኬ #እላይ_ልያስቀምጣቸው_ነው #ሰው ከፍ ቢል #አብ ቀኝ ነው #ቢወርድ_ሲኦል #ነው ከዚህ አያልፍም #ኢየሱስ_ከፍ ካለ ዙፋን ወጥቶ #የመጨረሻውን #ጥልቀት #ሲኦል #የነካ_ብቸኛ ነው። #መከተል #ለሐዋርያት _ብቻ _ለቀርም እኛጋም ደርሰዋል ታድያ የተከተልነው ጌታ #መርጠን #ሳይሆነ_መርጦን ነው። ለመከተል ያደርግነው አስተዋጽኦ የለም። #በዛን_ግዜ_በኢየሱስ_ታምር_እንጀራ የበሉ 5000ሺ ከዛ በላይ ነበሩ። ብዙዎች ከእጁ በለቶ እሱን ሥይበሉ ተመለሱ ኢየሱስ እንጀራን ባርኮ የምሰጥ ታምረኛ ብቻ ሳይሆን ራሱ የዘላለም እንጀራ ነው #እሱን_ለመብላት_መገለጥ #ያስፈልጋል #እሱን ለመመገብ በአብ መሳብ አለብን #አብ_ካልሳበን #ኢየሱስ በሰናከያ ነው #እነዛ ሲመለሱ። ከኢየሱስ በለተው ነው።
#የአለማችን_ትልቁ_ኪሳራ #ኢየሱስ #ጋር ደርሶ #መመለስ ነው። #ኢየሱስን ሳይበሉ ቀሩ ዛሬም ቢሆን እንዲህ ነው

#ኢየሱስ_መገለጥ_እንጅ በጭፍን #የምንከተለው #አይደልም #ከኢየሱስ #በለተው_ከሚመለሱ_ሳይሆን_ኢየሱስን በለቶ ከቀሩ ነኝ።
87 views11:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ