Get Mystery Box with random crypto!

መንፈሳዊ ግጥሞች እና ወጎች

የቴሌግራም ቻናል አርማ melikt_weg_gitim — መንፈሳዊ ግጥሞች እና ወጎች
የቴሌግራም ቻናል አርማ melikt_weg_gitim — መንፈሳዊ ግጥሞች እና ወጎች
የሰርጥ አድራሻ: @melikt_weg_gitim
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.16K
የሰርጥ መግለጫ

✞ ይህ ቻናል መንፈሳዊ የሆኑ ግጥሞች ፣ ወጎች እንዲሁም መልዕክቶች የሚቀርቡበት ነው ✞
አስተያየት ካለ እንዲሁም ግጥም ወግ እንዲተላለፉ የምትፈልጓቸው መንፈሳዊ መልክቶች ለማድረስ https://t.me/ a3-5g5CslOkwNjBk ተጠቀሙ

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-13 08:53:07 #ስሙ_ነው_ዮሐንስ


በይሁዳ ገዢ፥በሄሮድስ ዘመን
ሰው.. ሳይረዳ፥ቆሞ ከሰይጣን ጎን
አንድም ነገር ሳያውቅ፥ለሰይጣን መላኩ
ለጣኦቱ ይሰግዳል፥ጠፍቶበት አምላኩ!

ሁለቱ ቅዱሳን፥ልዩ ነዉ ክብራቸው
አምላክን ሳይክዱ፥ፀንተው በእምነታቸው
ማመስገን ነው ሁሌ፥ልጅም ባይኖራቸው።

እኚህ ሁለት ሰዎች፥ያመኑ በወንጌል
ልጅ የተነፈጉ፥የቅዱሳን አባል
አንዱ ዘካርያስ፥የመቅደሡ ካህን
ኤልሳቤጥ እሩሩ፥ልጅ ያጣችው መካን

የሠው ልጅ እያየች፥ስሜቷ ቢነካም
ፀሎቷን አብዝታ፥መልሱ ቢዘገይም
እርሷ ታምን ነበር፥ልጅ እንሚሰጣት
መንፈስ ቅዱስ፥ወርዶ እንደ ሚባርካት፤

ታዲያ አንድ እለትም ይህ ተአምር ሆነ

ቅድስት ኤልሳቤጥም፥ስትፀልይ ለንጉስ
ዘካርያስ ሲያጥን፥የሥላሴን መቅደስ

በማዕጠንቱ ቀኝ፥መልአኩን አይቶት
በገብርኤል ግርማ፥እራሱን እረስቶት
በአንዳች ፍርሀት ዉስጥ፥እንዲያ ሲንቀጠቀጥ

መልአኩ አስቦ፥እርሱን ለማስደሰት
እንዲህ ሲል ነገረው፥የያዘውን ብስራት

አትፍራ አንተ ሰው፥ካህን ዘካርያስ
ፀሎትህን ሰምቷል፥የሠማዩ ንጉስ፤

ሚስትህ ኤልሳቤጥም፥ልጅን ታረግዛለች
የአምላክን አገልጋይ፥እርሱን ትወልዳለች
ስሙንም ዮሐንስ፥ብላ ትለዋለች፤

በማለት መልአኩ፥በግርማ ሲናገር
ቀጠለ ካህኑ፥እንዲህ ሲጠራጠር

ይህን ማመን እኔ፥እንዴት እችላለው
የሚስቴ ቀን አልፎ፥እኔም አርጅቻለው
ታዲያ ይህን እኔ፥እንዴት አምንሀለው?

ቀጠለ መልአኩ

የአምላክህ አገልጋይ፥እኔ ገብርኤል ነኝ
ለአንተ እንዳበስርህ፥እግዚአብሔር የላከኝ
አንተ ተጠራጥረህ፥ቃሌን ስላላመንህ
ይሄ እስኪፈፀም፥ዲዳ ትሆናለህ
ልጅህ ሲወለድም፥ያኔ ትፈታለህ።

ብሎ ተሰወረ፥ሀያሉ መልአክ
ዘካሪያስን ዘግቶ፥ሄደ ወደ አምላክ
ከቀናት በኋላ፥ሚስቱም አረገዘች
ማርያምም ጎብኝታት፥ልጇንም ታቀፈች፤

ወዳጅ ዘመዶቿም፥መጡ ሊጠይቋት
መውለዷ ተሰምቶ፥ከገሊላ ናዝሬት
7ቱ ቀናትም፥አለፉ በደስታ
8ተኛው መጣ፥አፉ እንዲፈታ

በእዛች ትልቅ እለት፥ዮሐንስን ሊገዝሩት
ዘካርያስ ብለው---ልጁን ሰላም ሲሉት
ኤልሳቤጥ ተቆጣች፥ስሙ ስላልሆነ
ዘካርያስም አይቷት፥ብራና ለመነ

እነእርሱም አምጥተው፥መፃፊያውን ሰጡት
ምንድነው የምትፅፈው፥በማለት ጠየቁት
እርሱም ወረቀቱን፥አዙሮ ሰጣቸው
እነእርሱም አይተውት፥እየፈራ ውስጣቸው
በደስታ ሆ ብሎ፥በሀይል አያቸው።

ከዛም ዘካርያስ
አንደበት አውጥቶ፥መናገር ጀመረ
እራሱን አዋርዶ፥ተራ ነኝ እያለ

ወደ ሰ'ውም ዞሮ፥ልጁን በመቀበል
ከፍ ባለ ድምፁ፥ተአምሩን ሊናገር
እንዲህ ብሎ አስረዳ ነገሩን በቁጥር

ስሙኝ ልንገራቹ፥አድምጡ ወደእኔ
ዲዳ ሆኜ ነበር፥ቃል ባለማመኔ

ገብርኤል በግርማ፤ሲነግረኝ ጠርጥሬው
ልጄ እስኪወለድ፥አፌን ቢለጉመው
ከቀናት በኋላ፥ሚስቴም አረገዘች
በእግዚአብሔር ፀጋ፥ልጅንም ወለደች

ታዲያ ይሄን ልጄን፥ጠራችሁት በስሜ
እንዲህ በመገረም፥የማየውን ቆሜ

መንገድ ጠራጊውን፥መላሽ ወደ ኢየሱስ
የበረሀውን ድምፅ፥ይሄ የህፃን ቅዱስ
ዘካርያስ አይደለም፥ስሙ ነው ዮሐንስ።


የቅዱስ ዩሀንስ ረድኤቱ በረከቱ የዘዉትር ሰላሙ ከሁላችን ጋር ለዘላለሙ ፀንቶ ይኑር አሜን።

29/10/2014

አብሰጠኝ ዘ-ማርያም


@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gititm

#join and #share
689 views𝓜𝓮𝓷𝓽𝓮 ²⁵, 05:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-10 06:46:40 #ቅኔና_ውዳሴሽ


ቅኔና ውዳሴሽ ምግብ መጠጣችን
ማር የሆነው ስምሽ የመንገድ ስንቃችን
ፍቅርሽ እንደ ዕሳት__ ይነዳል ውስጣችን
ንኢ ንኢ ስንል ባርኪን እናታችን።

ልቡ ያዘነውን አዳምን ሊያፅናና
ትካዜውን ሊቀብር__የሞቱን ጎዳና
ማደሪያው አድርጎሽ__የሰማዩ መና
አዳነው ክርስቶስ__ ይድረሰው ምስጋና
ከወጣበት ገነት___ ተመልሷልና።

ካንቺ ተወለደ__ ያለ ወንድ ዘር
የሔዋን እርግማን__ወድቆ ሊሰበር
ያሳታት ዲያቢሎስ__ሲዖል ሊታሰር
ሥጋ ለብሶ ታየ__ ወልደ እግዚአብሔር።

ሰው የሆነና በኛ ያደረ ቃል
ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ አማኑኤል
መሆኑን ነገረን__ነበዩ ኢሳይያስ
አየነው ተጽፎ__ በመጽሐፍ ቅዱስ።

ሰው ሆይ ደስ ይበልህ__ተነስ ለምስጋና
እግዚአብሔር ዓለሙን__እንዲሁ ወዷልና
በአንድ ልጁ እንድናምን
ልዑል ክንዱን ሰደደልን።

የነበረው የሚኖረው__የማያልፈው ለዘለአለም
ከላይ ወርዶ ሰጠን ሰላም
በሥራው ሁሉ አልተለየም
ወልደ እግዚአብሔር__ ወልደ ማርያም።

ቅድስት ሆይ ለምኝልን
በበደልነው እንዳይቀጣን
ለንሰሀ ዕድሜን ይስጠን
በኪዳንሽ ተማፀንን።

የእግዚአብሔር ቃል መለኮት
የለበትም ሦስትነት
አንድ ብቻ__ነው እውነት
የሥላሴ__ቸርነት።

እንደ አበው__ ባንበቃ
ስምሽ ሆኖን__ ዋስ ጠበቃ
ደስታችን ሆኖ__ሲቃ
ልመናችን ሰምሮ ባንቺ
አማለደሽን ሳትሰለቺ።

ተሰበሰብን ልንጠራሸ
ማርየም ሆይ ቆምን ደጅሽ
የዘለአለም ዓንባችን ነሽ
ዕርስታችን የወረስንሽ።

እመቤታችን ሆይ የቅዱስ ኤፍሬምን በረከት አሳድሪብን Amen
ኢትዮጵያን ሰላም አድርጊልን
ልመናችንን አሳ ርጊልን።


@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gititm

#join and #share
743 views𝓜𝓮𝓷𝓽𝓮 ²⁵, 03:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-08 14:58:57 #ፍልሰታ


ትፈራው ነበረ ያን መልአከሞት
የልጅሽን ፅዋ ቅመሽው አላት
ይጠፋል ኩነኔ ይጠፋል አበሳ
እንደ ፈጣሪያችን ማርያም ስትነሳ
እየባረከቻት ኢትዮጵያን በእጆቿ
በይባቤ አረገች እሷም እንደ ልጇ
ከሰው የተለየች መሆኗን ሲያበስር
ሞት በጥር ሆነ ነሃሴ መቃብር
አይሁዳዊው ቀንቶ ሲሰርቅ ሥጋዋን
የመለኮቱ ሰይፍ ቆርጠው እጁን
ብዙው ይጾመዋል የፍልሰታን ፆም
ከእህል ተከልክሎ ከሥጋ ከደም
ሐዋርያው ፊሊጶስ ትንሣኤዋን ሲሻ
ከወንድሞቹ ጋር ዕርገቷንም ሲሻ
በስሟ ተነሱ ሊፆሙ በጋራ።

የበረከት ፆም ያድርግልን!


@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gititm

#join and #share
830 views𝓜𝓮𝓷𝓽𝓮 ²⁵, 11:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-06 11:50:04 ✞ #ጾመ_ፍልሰታ ✞

እንኳን አደረሳችሁ

✞ "ፍልሰታ" የሚለው ቃል "ፈለሰ፣ ተሰደደ፣ ተጓዘ" ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን እመቤታችንም ከጌቴ ሴማኒ ወደ ገነት መፍለሷን በኃላም በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር ከነበረችበት መነሳቷን ለማመልከት አስቀድሞ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት "ተንሥእ እግዚኦ ውስተ እረፍትከ አንተ ወታቦተ መቅደስከ"(አቤቱ ወደ እረፍትህ ተነስ አንተና የመቅደስህ ታቦትም) መዝ ፻፴፩፥፲ በማለት ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት የእመቤታችንን ምልጃዋን ትንሣኤዋን አስቀድሞ በትንቢቱ ተናግሮ ነበር።

✞ የፍልሰታ ጾምም ሁሌ በየአመቱ ከነሐሴ ፩ እስከ ፲፭ ቀን ይሆናል። በነገረ ማርያም እንደተጻፈው ጥር ፳፩ ቀን አርፋ በ፷፬ ዓመት እድሜዋ በ፵፱ ዓ/ም አይሁድ ለምቀኝነት አያርፋም ነበርና ቀድሞ ልጅዋን ተነሣ አረገ እያሉ ሲያውኩን ኖረዋል አሁን ደግሞ እሷን ተነሣች አረገች እያሉ ሊያውኩን አይደለምን? "ንዑ ናውዒ ሥጋሃ ለማርያም ምስለ ዓራታ"(ኑ የማርያምን ሥጋ በእሳት እናቃጥለው) ብለው ተነሱ። ከመካከላቸውም አንድ ታውፋንያ የሚባል ጎበዝ ከሐዋርያት እጅ ለመንጠቅ የአልጋውን ሸንኮር መያዣ ሲይዝ ቅዱስ ገብርኤል በእሳት ሰይፍ እጆቹን ቆረጣቸው። እጆቹም በአልጋው ሸንኮር ላይ ተንጠልጥለው ቀሩ። ታውፋንያም ወደ ሐዋርያት ዞሮ በድያለሁ ይቅር በሉኝ ብሎ ቢማፀን፤ የምሕረት እናት የሆነች እመቤታችን አይኖቹዋን ገልጣ ቅዱስ ጴጥሮስን እጆቹን መልስለት ብላው እጆቹንም እንደ ነበሩ መልሶለት ተፈውሷል።
✞ ያን ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ በዕለተ ዐርብ ከአምላኩ በስጦታ የተሰጠችውን የአምላክ እናትን ሥጋዋን በድፍረት ሊነኩ መምጣታቸውን አይቶ ዐደራዬን አላፈርስም፤ ከርሷ ጋር እሞታለኊ በማለት ይኽነን ተናግሮ በላይዋ ላይ ወደቀ። ከዚያም ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል በታላቅ ግርማ ወርደው የቅድስት ድንግል ማርያምን ሥጋዋንና ቅዱስ ዮሐንስን በደመና ነጥቀው በገነት በሕይወት ዛፍ ሥር አኖሯት፡፡ ወዲያውኑ የወርቅ ማዕጠንት ለዮሐንስ አምጥተውለት፤ የቅድስት ድንግል የከበረ ሥጋዋን በመዓልትና በሌሊት ዕጠን አሉት፤ ዮሐንስም ይኽነን ክብር በመቀበሉ ደስ ብሎት ሥጋዋን እያጠነ ሰርክ ሲኾን ራጉኤል መልአክ ሰማያዊ ኅብስት ሰማያዊ መጠጥ እያመጣለት ያን እየተመገበ በገነት ቆይቷል፡፡ ኋላም በጌታ ፈቃድ ከተቀሩት ሐዋርያት ጋር ተገናኘ። ሐዋርያትም የእመቤታችንን ነገር እንደምን እንደኾነ ሲጠይቁት ርሱም በገነት ያየውን ነገር ነገራቸው፤ ሐዋርያትም ይኽነን ታላቅ ምስጢር ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ ብለው ሥጋዋን አግኝተው ይቀብሩት ዘንድ በአረፈች በስምንተኛው ወር ነሐሴ ፩ ሱባኤ ጀመሩ ነሐሴ ፲፬ ቀን በኹለተኛው ሱባኤ ጌታ የእናቱን ሥጋ አምጥቶ ሰጥቷቸው በምኅላና በደስታ በጌቴሴማኒ አሳረፋት።
✞ ከዚህም በኃላ በሦስተኛው ቀን ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ በተወደደች ዕለት ነሐሴ ፲፮ ሰባቱ ሊቃነ መላእክት ምድርን ይጠሯት ዘንድ አዘዛቸው እነርሱም ምድርን “ይኤዝዘኪ እግዚእነ ከመ ታውጽኢ ሥጋሃ ለእሙ ቅድስት” (ጌታችን የንጽሕት እናቱን ሥጋ ታወጪ ዘንድ ያዝሻል) አሏት፤ ያን ጊዜ ልጇ “ንዒ ኀቤየ ወላዲትየ ከመ አዕርጊ ውስተ መንግሥተ ሰማያት”(ወደ መንግሥተ ሰማያት አሳርግሽ ዘንድ እናቴ ወደኔ ነዪ) አላት፤ በልጇም ሥልጣን የቅድስት ድንግል ማርያም ነፍሷና ሥጋዋ ተዋሐዱ፤ በነሐሴ ፲፮ ዕለትም እመቤታችን ከሞት ተነሣች፡፡ ቅዱሳን መላእክትም ከሰማይ በታላቅ ግርማ ወረዱ፤ ነቢዩ ዳዊትም "ንግሥቲቱ ወርቀ ዘቦ ግምጃ ደርባ ደራርባ በቀኝኽ ትቆማለች" እያለ ይዘምርላት ነበር፤ አየሩ ኹሉ በቅዱሳን መላእክት ተመላ፤ እጅግ የሚያስደንቅ መዐዛ አካባቢን ዐወደው። በታላቅ ክብርም በመላእክት ታጅባ ወደ ሰማይ ስታርግ፤ ጥሪው ከሰዱቃውያን ትውልዱ ሕንዳዊ የሆነው ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለስ ሰማዩ ኹሉ በቅዱሳን መላእክት ተመልቶ የአምላክ እናት በክብር ስታርግ ተመለከተ፤ ያን ጊዜ ነገሩ ረቆበት ምን ይኾን እያለ ሲል ቅዱሳን መላእክት የእመቤታችን ዕርገት እንደኾነና እጅ እንዲነሣ ነገሩት፡፡ ቅዱስ ቶማስም ትንሣኤዋን ከእርሱ ሰውራ ያደረገች መሥሎት፤ “ከቶ ምን አርጌ ይኾን፤ ቀድሞ የልጇን ትንሣኤ ሳላይ ቀረኊ ዛሬ ደግሞ የርሷን ትንሣኤ ሳላይ ልቅር?” ብሎ ከደመና ተወርውሮ ሊወድቅ ወደደ።

✞ እመቤታችንም “አይዞኽ አትዘን እነሱ ሞቴን አይተዋል እንጂ ዕርገቴን አላዩም። አኹንም እመቤታችን ተነሣች፤ ዐረገች ብለኽ ንገራቸው” ብላ ለቀሩት ሐዋርያት ምልክት የሚሆን ሰበን ወይም መግነዟን ሰጥታው ተለያዩ። እርሱም በደስታ ተመልቶ ሐዋርያት ያሉበት በመኼድ የእመቤታችን ነገር እንደምን ኾነ ብሎ ጠየቃቸው፤ እመቤታችን ሞተች ቀበርናት አሉት፤ “መቼ ሞተች?” አላቸው በጥር አሉት፤ “መቼ ቀበራችኋት?” አላቸው በነሐሴ አሉ፤ ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር ተዉ ይኽ ነገር እንዴት ይኾናል? አላቸው፤ ቅዱስ ጴጥሮስም ቶማስን ቀድሞ የልጇን ትንሣኤ አላምን ብለኽ የጌታን ጐን የዳሰሰ እጅኽ ተቃጥሎ ነበር፤ አኹን ደግሞ እኛ ብንነግርኽ አላምን ትላለኽ ብሎ፤ መቆፈሪያ ይዞ ኼዶ ይቆፍር ጀመር፤ እርሱም የያዘውን ይዟልና ጸጥ ብሎ ይሰማቸዋል፤ ቈፍረው ሲያጧት ደነገጡ፤ ቶማስም አይዟችኊ አትደንግጡ እመቤታችን እኮ በመላእክት ምስጋና ወደ ሰማይ አረገች ብሎ ሰበኑን አሳያቸው፤ እነርሱም ለበረከት ሰበኑን
ተካፍለውታል፡፡ ዛሬም ሐዋርያዊት የኾነችው ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ይኽነን በማሰብ ዛሬም ቀዳሽ ዲያቆኑ ከመስቀል ሥር ከመፆሩ ጋር የሚይዘው መቀነት መሳይ ጨርቅ የእመቤታችን የሰበኗ ወይም የመግነዝዋ ምሳሌ ነው።
✞ ከዚህም በኃላ በዓመቱ ሁሉም ሐዋርያት ተሰባስበው ቶማስ ትንሣኤሽን አይቶ እኛ ሳናይ ብለው በድጋሚ ሱባኤ ከነሐሴ ፩ እስከ ፲፬ ቢጾሙ ጌታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ነፍሷን ከስጋዋ አዋህዶ ትንሣኤዋንም ዕርገቷንም አሳይቷቸዋል። ክብር ይግባውና ጌታችን በደመና ነጥቆ ወስዶ ሥርዓተ ቊርባንን ፈጽሞላቸው፤ ስለ እናቱ ዕርገት በዓለሙ ኹሉ ዙረው እንዲያስተምሩ አዝዟቸዋል፡፡ እነርሱም
ዓለምን ዞረው ወንጌልን ሲያስተምሩ የእመቤታችንን ትንሣኤና ዕርገትም ሰብከዋል አስተምረዋል፡፡ እኛም ከበረከቷ ለመሳተፍ በመላው ዓለም የምንገኝ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ የሆንን ሁሉ ከሕፃን እስከ አዋቂ ድረስ በፍቅርና በዕምነት የምንጾመው የሱባዔ ጾም ነው።
✞ እመቤታችን ከእናቷ ማሕፀን ዠምራ በመንፈስ ቅዱስ የተጠበቀች አዳማዊ ኀጢአት ያላገኛት፣ ኀጢአት አልባ የኾነች እንዲያውም አዳምና ሔዋን ከእርግማን በፊት ከነበራቸው ንጽሕና የበለጠ ንጽሕናን ገንዘብ ያደረገች ስትኾን ክብር ይግባውና አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ይኽነን ንጹሕ ሥጋዋንና ነፍሷን በመንሣት በተዋሐደው ሥጋ በመስቀል ተሰቅሎ፤ ሦስት መዓልትና ሌሊት በከርሠ መቃብር ዐድሮ፤ ሙስና መቃብርን አጥፍቶ ሞትንና ኀጢአትን ድል ነሥቷልና፤ አማናዊት ታቦቱ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምም በልጇ ሥልጣን በሦስተኛው ቀን ተነሥታለች። "በወርቅ ልብስ ተጎናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝ ትቆማለች።"(መዝ ፵፬፥፱)፡፡
1.1K views𝓜𝓮𝓷𝓽𝓮 ²⁵, 08:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 06:31:35 @Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim

#Join_and_Share
585 views𝓜𝓮𝓷𝓽𝓮 ²⁵, 03:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 06:31:35 +++ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን+++

#መቼ_ትመጣለህ ?

መቼ ትመጣለህ? ነገ ወይስ ዛሬ?በኃጢአት አልክበር ፤ ዕድሜዬን አልጨርስ ፤ አልብላው መንዝሬ።
ንገረኝ ጊዜውን ፤ ቆሜ ልጠብቅህ ፣
ግራ ቀኝ አልባክን ፤ እንዴት ነው አመጣጥህ ?
ትዘገይ እንደሆን ፤ ላትጠራኝ ቶሎ ፣
ከእፀ በለስ ልብላ ፤ ስሜቴ ገንፍሎ ፣
ምክንያቴን አብዝቼ ፤ አግዝፌ ልቆይህ ፣
ሔዋን አስታኝ ነው ፤ ሰይጣን አሳስቷት ፤
መክሯት ነው ልበልህ።
ለሥጋዬ ልስጣት ፤ ሥልጣኑን በሙሉ ነፍሴን ትበድላት ፣
ለጊዜው ትጠቀም ፤ አንተ ከዘገየህ ትሁነው እንዳሻት ።
ጊዜ አገኝ እንደሁ ፤ በተራገምኩበት መመረቅ እንድችል ፣
እስከ ጊዜው ድረስ ፤ ነፍሴ ታንጎራጉር ትንደደው ትቃጠል ።
ሰዎች ተስፋ ቆርጠው ፤ ይኸው በዚህ ሰሞን ታሪክ ያወራሉ ፣
ያ! ስምንተኛው ሺህ ፤ ከተነገረ እንኳ ቆይቷል እያሉ
ሰዉ ጽድቁን ትቷል ሁሉም በያለበት ሀሜቱን ቀጥሏል ፣
መጋደል መጣለፍ ፤ መቋሰል መቧደን ዝርፊያውም በርክቷል ፣
እንኳን ዳግም ም'ጻት የዓለም ፍጻሜ ስምህ ተዘንግቷል።
 
መቼ ትመጣለህ ነገ ወይስ ዛሬ?
                                
ግዴለም ንገረኝ ፤ ልክ እንደኖኅ ጊዜ ዘመኑን አስላና፣
ሃያዋ ብትበቃኝ ለንሰሓ ጊዜ ፤ በመቶው ልዝናና።
ገና አልበረደኝም ሰውነቴ ግሎ ውስጥ አካሌ ዘንቶ፣
ዓለሙን ያስሳል ፤ አንተ ከዘገየህ ለምን ሥራ ፈትቶ።
እበላው እንደሆን የሰበሰብኩትን ፤ ከሌላው ዘርፌ፣
እኖረው እንደሆን እንደማቱሳላ እድሜዬን አትርፌ።
ሺህ ዓመቴን ወስደህ ፤ የአንተን አንድ ቀን ትሰጠኝ እንደሆን ፣
ምናለበት ብዘርፍ ምናለ ብዘሙት ፤ መዘግየትህ ላይቀር ።
ከምድር እሰከ ሰማይ ፤ ተዘርግቶ 'ማያልቅ ለበዛው ኃጢአቴ ፣
ጊዜ ካበደርከኝ እንዲሰረዝልኝ ፤ እንዲፋቅ ጥፋቴ ፣
ልክ እንደ ኢያሱ ፤ ፀሐይን አቁመህ ከጠበቅኸኝ በቃኝ ፣
ዛሬን ልዝናናበት ፤ ኃጢአት ልጨማምር  ጨለማ ሳይወርሰኝ ፣
ይኸው ሰዉ ሁሉ ነገሩን ዘንግቶ ፤ ሁሉ ሆድ ብሶታል ፣
"ይዘገያል " አሉ እያለ ያወራል ፤ ኃጢአት ይሸምታል።
እኔም በቀደም 'ለት ፤ ከደጀ ሰላሙ ብዙ ጉድ አይቼ፣
ገዛሁት በርካሽ ፤ ኃጢአትን ከደጅህ ፤ ከቤትህ አግኝቼ።
ግዴለም ንገረኝ ፤ ሃያው ይበቃኛል በሌላውስ ላትርፍ ፣
እንዴት ከሌላው ህዝብ ፤ እኔ ተለይቼ እንደ ጅል ልንከርፈፍ ?

   መቼ ትመጣለህ ነገ ወይስ ዛሬ?
                                     
ሌላውን ልበድል ፤ ነገርን ልዶልት ህዝብህንም ልቁጠር ፣
ከድንኳን ደጃፍ ፤ ተቀምጬ ላሹፍ ፤ ዘፈን ላንጎራጉር ።
ጊዜ ከሰጠኸኝ ፤ የምለይበትን ዘፈንን ከመዝሙር ፣
ንሰሐ ገባለሁ ልክ ስትመጣ ፤ ዛሬን ግን ልጨፍር።
ከጥብርያዶስ ባሕር ፤ ኃጢአት ዓሣን ላጥምድ፣
ትዘገይ እንደሆን ምናል ይህን ብትፈቅድ?
ይኸው ሰዉ ሁሉ ፤ ግራ ያጋባኛል ነገር እያማታ ፣
ኃጢአትን አግብቶ ፤ ትዳርን መስርቶ ጽድቅን እየፈታ ።
በክፋት ላይ ክፋት ፤ በዚያ ላይ ስምህን በፍፁም ደርቦ ፣
ጽድቅና ኃጢአትን ባንድ እያካሄደ በደስታ ተከቦ ፣
ጻድቅ ሲሸማቀቅ አንገቱን ሲደፋ ፤ ተመልካችም ሲያጣ ፣
እንዳሻው በመሆን ፤ ኃጥእ ሲዝናናበት ሲስቅ በለበጣ ።
ዘመናት አለፉ ፤ ይኸው ዛሬም የስምህ አጥፊዎች፣
ሥራቸውን ሰደው ፤ በደንብ ተስፋፍተው ዙሪያውን ብዙዎች ፣
ከደሃው ላይ ሰርቀው ፤ ምስኪን አስለቅሰው ለታቦት ሲያገቡ ፣
ወገን ጦሙን አድሮ ፤ ሲበሉ ሲጠጡ ሲያገቡ ሲጋቡ ።
እንኳንስ መምጣትህ ፤ ስምህ ተዘንግቶ አዳሜ ሲጨፍር ፣
እኔስ ምን ተዳዬ ፤ ከዚህ ህዝብ መሃል ተለይቼ ልቅር ?
ይልቅስ ንገረኝ ፤ ትመጣ እንደሆን ፀሐይ ሳትገባ ፣
አሊያም ልደባለቅ ከምድር ወገኖቼ ፤ ከወጣው ወጥቼ  ከገባው ጋር ልግባ ።
                            
  መቼ ትመጣለህ ነገ ወይስ ዛሬ?
                                    
የበራፌ ጥላ ከበር እስኪከተት ፤ 'ማትመጣ ከሆነ፣
አሸንክታብ ላርዝም ክብሬንም ልፈልግ ፤ ጊዜዬ ባከነ ፣
ዓለሙን ልከተል የዛሬን ልደሰት ፤ ነገ እመለሳለሁ ፣
አንተ ዛሬ ትመጣ ፤ ወይም እንደምትቀር በምን ዐውቀዋለሁ ?
ይኸው በዚህ ሰሞን ፤ ሰዎቹ በሙሉ ታሪክ ያወራሉ፣
እሱ ቀርቷል ብለው፣ ባንተም ላይ ደርበው ጣዖት ያመልካሉ።
ይኸው በዚያ ሰሞን ፤ ሥጋ ቤቱ ደጃፍ ሁሉ ተኮልኩሎ ፣  
በሁዳዴ ምድር ቁርጥ ያወራርዳል ፤ መስቀል አንጠልጥሎ ።
እኔስ አያምረኝም ? አንተ እንደው አትመጣ ፤ ብበላ ምናለ ፣
ጠበል እረጫለሁ ፤ ወደፊት ጾማለሁ አንተ ከዘገየህ ፣
እንዲሁ በከንቱ ጊዜ ከሚባክን ፤ ቅዳሴ አስቀድሼ ዳንኪራ ቤት ብሄድ    
ጽድቅን እንደሆነ ፤ መቼም አላጣትም ለኃጢአት ብሰደድ ፣
የልቤ ግድግዳ ቢጠቁር በክፋት ፤ ደግሞም ቢበሰብስ ፣
ዛሬ አንተ ካልመጣህ ነገ እታጠባለሁ ፤ ንሰሐ ሳሙና እስካለልኝ ድረስ!
ምናለ ብሳደብ ሌላውን ብጎዳ ፤ ማንም እናዳይነካኝ ፣
ግዴለም ለነገ ግራዬን ቢያጮሉኝ ፤ ቀኜን ሰጣለሁኝ።
እንደ  ሕፃን በርሬ ያሻኝ ቦታ ልድረስ ፤ ያሻኝን ልተንፍስ ፣
አኩኩሉ ልበል ፤ በኃጢአት ጫካ እስክትመጣ ድረስ ።

  መቼ ትመጣለህ ነገ ወይስ ዛሬ?
                                           
ምናለ እንደ ዴማስ ፤ ይህችን ዓለም ብወድ አንዴ ብተፈቅድልኝ ?
በኋላ መጣለሁ ልክ እንደ ድሮዬ ፤ አገለግላለሁ ቆመህ ከጠበከኝ።
ትዘገይ እንደሆን ፤ በቶሎ ማትመጣ አሊያ የምትቀር ፣
ምናል ሳማ ሰንበት ፤ ብሄድ ለሽርሽር ?
ቢራዬን ገዝቼ ፤ ቱታዬን አጥልቄ ፣
ልክ እንደ ቱሪስቶች ፤ ምግቤንም ሰንቄ ፣
በውጭዎች ፈሊጥ ፤ እየተቀናጣሁ ደርሼ ብመለስ፣
ምናለ ባልጸልይ ፤ ምናል ባላስቀድስ ?
ይኸው ትናንት እንኳ ፤ ትናንትና ማታ
ሰዎች ተኮልኩለው ፤ ከዐውደ ምሕረቱ ፣
አየሁኝ ሲጣሉ ፤ በቡድን ተከፍለው ነገር ሲዶልቱ።
እኔስ ምን አለበት ፤ በነሱ ብጽናና በኃጢአት ባድግ፣
አንተ እንደሁ አትመጣ ፤ ስንት ዘመን ሆነኝ ቆሜ ሳደገድግ ።
ፍጹም ልመሳሰል ከዚህ ዓለም ጋራ ፤ ማንነቴ ጠፍቶ ፣
አንተ ከዘገየህ ፤ ምናል ይህ አካሌ ቢኖር ሕይወት አጥቶ ?
ጊዜዬን ልስራበት ለኃጢአት ልነሣ ፤ ለጽድቅህም ሞቼ ፣
ክርስትናው እንደው መቼም አይቀርብኝ ፤
ነገ እቆርባለሁ በምርኩዝ መጥቼ ።

       መቼ ትመጣለህ ነገ ወይስ ዛሬ?
                           
ይኸውና ዛሬ ሁሉ ቀላል ሆኖ ፤ መፈራትህ ጠፍቶ ፣
የነዲዮስቆሮስ የነጴጥሮስ እምነት ፤ ከኋላ ተገፍቶ፣
ሰው ሰውን እያየ በሥጋ ሲጽናና ፤ አምላክን ረስቶ ፣
ከዐውደ ምሕረቱ አንተ ተሸፍነህ ፤ እኔን ስሙኝ በዝቶ ፣
እምነት እንደፋሽን ራሱን ተኩሎ ፤ ራሱን ቀብቶ ፣
በደፋሮች ጩኸት መቅደስህ ታውኮ ፤ መቅደስህ ሲረክስ ፣
ዐዋቂ አንገቱን በደፋበት መድረክ ፤ ታዋቂ ሲነግሥ።
ነጠላና ቀሚስ የጽድቅ መገለጫ ፤ በሆኑበት ዘመን፣
በስሜት ተነድቶ በስም ብቻ ሲሮጥ ፤ ህዝብህም ሲባዝን ፣
እኔስ ምን ተዳዬ ፤ ለግዜው ብደሰት ?
ሆ! ካለው ሆ ብዬ አብሬው ብዘምትም ፤ ሆሳዕና ብዬ ዛሬ ብዘምርም ፣
ከሳምንት በኋላ በዚያው አንደበቴ ፤ ይሰቀል !ይሰቀል! ማለቴ አይቀርም ።
እምነቱ ባይገባኝ ፤ እኔ ምን አገባኝ ?
ዝም ብዬ ሮጣለሁ
ምን ችግር አለበት አንተ ከዘገየህ ፣ ምስጢረ ሥላሴን ውዳሴ ማርያምን ፤
ቀስ ብዬ እማራለሁ ፣
አንተ እንደ ምትመጣ ፤ ወይ እንደ ምትቀር በምን ዐውቀዋለሁ ???????
660 views𝓜𝓮𝓷𝓽𝓮 ²⁵, 03:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 07:26:12
771 views𝓜𝓮𝓷𝓽𝓮 ²⁵, 04:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 12:56:52 #ቅዱስ_ገብርኤል


የንጉስ ጭካኔ ፥ ክንዱ ቢበረታ፤
ለጣዖት ሳንሰግድ፥ እኛ ሳንረታ፡፡
የምናምነው አምላክ፥ ሊያድነን ወደደ፤
ገብርኤል መጣና፥ እሳቱ በረደ፡፡

ፍላፃና ሠይፉን፥ አጠፈው መላኩ፤
ሰላም ይዞ መጣ፥ ባለም ለታወኩ፡፡
አትጠራጠሩ፥ ምልጃው ያስምረናል፤
የሚነደው እሳት፥ ሳይነካን ወተናል፡፡

የሰልስቱ ደቂቅ፥ የእጠሉጣ ብርታት፤
የድንግል አብሳሪ፥ የቂርቆስ ረዳት፡፡
በሚመጣው አለም፥ እንዳይበላኝ እሳት፤
አማልደኝ ከጌታ፥ ነፍሴን እንዲምራት፡፡

የነገርኩህ ሁሉ፥ በቀኑ ደረሰ ፤
በዘብር ገብርኤል፥ እንባዬ ታበሰ፡፡
ና ልጄ ስትለኝ፥ አልልህም እንቢ፤
ስለቴን ተቀበል፥ አባቴ ቁልቢ፡፡

የልቤን ነግሬህ፥ የቁልቢው ገብርኤል፤
ሳትረሳ ፈፀምከው፥ ስለቴን ተቀበል፡፡
ለንግስ እንመጣለን፥ አንተ አትረሳምና፤
ደሞ የዛሬ አመት፥ አድርሰን በደህና፡፡


እንኳን ለሃያሉ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ የንግስ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!!


@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gititm

#join and #share
839 views𝓜𝓮𝓷𝓽𝓮 ²⁵, 09:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 08:48:20 ሐምሌ 19

ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ

ሐምሌ ዐሥራ ዘጠኝ በዚህች ቀን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ በሰማዕትነት መከራ ተቀበሉ። ይህም ሕፃን ዕድሜው ሦስት ዓመት ሲሆነው ከሮሜ አገር ወደሌላ ሀገር እናቱ ይዛው ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኰንን አገኘችው

ሰዎችም ነገር ሠሩባት ወደርሱ አስቀረባትና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኰንን ሆይ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነው ሕፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እርሱን ጠይቅ አለችው

ሕፃኑም ወደአለበት ጭፍራውን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሕፃኑንም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ሕፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው። ሕፃኑም መልሶ አዎ ለእኔ ደስታ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ኀዘንና ልቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏልና አለው እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስከ አስደነገጣቸው ድረስ ንጉሡን መኳንንቱንና ጣዖታቱን ረገማቸው ከብርታቱም የተነሣ አደነቁ

መኰንኑም በአፈረ ጊዜ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ሥቃይን አሠቃየው እናቱንም ከርሱ ጋር እንደ እርሱ አሠቃያት እግዚአብሔርም ያለምንም ጉዳት ያነሣቸው ነበር። ብዙዎች አሕዛብም ይህን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማዕትነት ሞቱ የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበሉ

በሕፃኑ ላይም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት። ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው

ከዚህም በኋላ መኰንኑ በታላቅ የናስ ጋን ውስጥ ውኃ ጨምረው በእሳት ያፈሉት ዘንድ አዘዘ የፍላቱም ድምጽ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ሆነ ያን ጊዜም ፍርሀትና የሃይማኖት ጉድለት በእናቱ ላይ ደረሰባት ሕፃኑም ስለ እናቱ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ

ያን ጊዜ ጌታችን ልቧን ወደ ሰማይ አሳርጎ ለቅዱሳን ሰማዕታት የተዘጋጁ የብርሃን ማደሪያዎችን አየች ከዚህም በኋላ ጸናች እግዚአብሔርንም አመሰገነችው ልጅዋንም ልጄ ሆይ ከእንግዲህ አንተ አባቴ ነህ እኔም ልጅህ ነኝ አለችው

ያቺ ከኔ የተወለድክባትም ቀን የተባረከች ናት አለች ወደዚያ ወደ ጋኑ ውስጥ በገቡ ጊዜም የውኃው ፍልሐት እንደ ንጋት ጊዜ ውርጭ ቀዘቀዘ ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና

ከዚህም በኋላ መኰንኑ ሥጋቸው ተቆራርጦ እስከሚወድቅ ድረስ በመቃጥን ውስጥ አድርገው እንዲጐትቷቸው አዘዘ ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ አዳናቸው መኰንኑም በታላቅ ሥቃይ ያሠቃያቸው ዘንድ አስቦ እስኪመክር ድረስ በወህኒ ቤት ዘጋባቸው

ያን ጊዜም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሕፃኑ ቂርቆስ ወርዶ አጽናናው አረጋጋውም። ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውን ለሚያደርግ ቃል ኪዳን ሰጠው

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ቂርቆስና በኢየሉጣ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን

ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ
853 views𝓜𝓮𝓷𝓽𝓮 ²⁵, 05:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-23 06:50:14 #ኪዳነ_ምህረት_እናቴ 


አውቃለሁ እኔ ጎስቋላ ነኝ
ምንም ጽድቅ ያልሰራሁኝ
ህይወቴን በሃጢያት ያሳለፍኩኝ
ዛሬም መመለስ የተሳነኝ
ራሴን መግዛት ያቃተኝ
አውቃለሁ አንዳችም ምግባር እንደሌለኝ።
             ደንግል በኪዳንሽ ልብሽ ይራራልኝ
             እንደ በላኤ ሰብዕ የሚያደርገኝ
             አንቺ ግን እንኳንስ ለሰው
             አምላክ በአምሳሉ ለፈጠረው
                 አይደለሽም እንዴ?
               ለውሻ እንኳን ያዘንሽ
         ውሀ ጽሙንም ያስታግስሽ።
አንድ ቀን በድንገት ቢጠራት
ነፍሴን ለፍርድ ቢያቆማት
አውቃለሁ በስራዋ እንዳትሟገት
በጽድቋም እንዳታገኝ ምህረት።
ግን አንዲት መመኪያ አለቻት
ዋስ ጠበቃዬ ምትላት
             ከእሳት ለመዳን ከልቧ ምትጠራት
             እርሷም አንቺው ነሽ ኪዳነ-ምህረት
            አደራ ድንግል እንዳትተያት
           ለነፍሴ መዳን ምክንያት ስለ ሆንሻት።

  እኔም እወድሻለሁ ልበል እንደልጅነቴ
  ንጽሕት ዘሥጋ ወነፍስ ኪዳነ ምህረት እናቴ

               ✞ወስብሐት ለእግዚአብሔር✞
                    ✞ወለወላዲቱ ድንግል✞
                     ✞ወለመስቀሉ ክቡር✞
                             ✞አሜን✞


@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gititm

#join and #share
996 views𝓜𝓮𝓷𝓽𝓮 ²⁵, 03:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ