Get Mystery Box with random crypto!

መንፈሳዊ ግጥሞች እና ወጎች

የቴሌግራም ቻናል አርማ melikt_weg_gitim — መንፈሳዊ ግጥሞች እና ወጎች
የቴሌግራም ቻናል አርማ melikt_weg_gitim — መንፈሳዊ ግጥሞች እና ወጎች
የሰርጥ አድራሻ: @melikt_weg_gitim
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.16K
የሰርጥ መግለጫ

✞ ይህ ቻናል መንፈሳዊ የሆኑ ግጥሞች ፣ ወጎች እንዲሁም መልዕክቶች የሚቀርቡበት ነው ✞
አስተያየት ካለ እንዲሁም ግጥም ወግ እንዲተላለፉ የምትፈልጓቸው መንፈሳዊ መልክቶች ለማድረስ https://t.me/ a3-5g5CslOkwNjBk ተጠቀሙ

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 23:20:19 ከአክራሪ እስልምና ወደ ክርስትና
#በእውነተኛ_ታሪክ_ላይ_የተመሰረተ
ክፍል 2
#ባለታሪክ_እና_ጸሀፊ
ናሕድ ማሕሙድ ሙቱዋሊ
#ተርጓሚ ዲ/ን ዳንኤል ክብረት

ናታኒም ቲዩብ SUBSCRIBE በማድረግ አገልግሎቱን ያበረታቱ ናታኒም ማለት የእግዚአብሔር ቤት ጠራጊ ታናሽ አገልጋይ ማለት ነውና።






18 viewsማኔ ቴቄል ፋሪስ, 20:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 21:12:58 ከአክራሪ እስልምና ወደ ክርስትና
#በእውነተኛ_ታሪክ_ላይ_የተመሰረተ
ክፍል 1
#ባለታሪክ_እና_ጸሀፊ
ናሕድ ማሕሙድ ሙቱዋሊ
#ተርጓሚ ዲ/ን ዳንኤል ክብረት

ናታኒም ቲዩብ SUBSCRIBE በማድረግ አገልግሎቱን ያበረታቱ ናታኒም ማለት የእግዚአብሔር ቤት ጠራጊ ታናሽ አገልጋይ ማለት ነውና።






41 viewsማኔ ቴቄል ፋሪስ, 18:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 18:55:06 የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ


ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
ዘማሪ አርቲስት ይገረም ደጀኔ
ዘማሪ ገ/ዮሐንስን ገ/ፃዲቅ
ቀሲስ ምንዴዬ ብርሀኑ
ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ
ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ
ዘማሪ ዲ/ን ሮቤል ማቲያስ
ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን
ዘማሪት አቦነሽ አድነው
ዘማሪት ዶ/ር ሔለን ተስፋዬ

እና የሌሎችንም ...........

ዘማሪዎችን መዝሙሮች እና አዳዲስ
መዝሙሮችን ለማግኘት ከስር OPEN
የሚለውን ይጫኑት።

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
█ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █
█ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █
█ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
69 viewsኦርቶዶክስ ፕሮሞሽን ❖ ፪, 15:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 06:38:33 #እኔ_ነኝ


ለሞቴ መሞትህን ዘንግቼ
በፍቅርህ መዳንን 'ረስቼ
ይቅርታህ ደጋግሞ ቢምረኝ
በሀጥያት ሁሌ እንደቆሸሽኹኝ

አለሁኝ ከቃልህ እርቄ ወድቄ
ፍቅርን ስትሰብከኝ ጥላቻን አርግዤ
ይቅርታን ስትሰብከኝ ቂም በሆዴ ይዤ
ቸርነት እንዳደርግ ሁሌ ብትመክረኝ
ራስ ወዳድ ቆንቋና ስስታም የሆንኩኝ
ወንድምህን ውደድ ብለህ ብትለኝም
ጥላቻዬ ገፍቶት ወንድምም የለኝም
ከቶ እንዳትጨነቅ ብለህ አጽናንተኸኝ
ዛሬም ጭንቀታም ነኝ ከቶ ተስፋ የለኝ
ማታ ከዳንኪራ ጠዋት ከመቅደስህ
ማዳንህ አጽናንቶ ፍቅርህ ያላደሰኝ
ሰምቶ እንዳልሰማ ጆሮ ዳባ ብዬ
ሰው መስዬ የምታይ ሀጥያትን አዝዬ
ሀጥያቴን ሸፍነህ ይቅር ብትለኝም
የወንድሜን ጉድፍ ማየት አልተውኹኝም
ኗሪ መሳይ ከንቱ ቋሚ መሳይ ሟች ነኝ
ከንስሀ ይልቅ ልብሴን የማጠራ
አምሮ ለመታየት ከሰው ልጆች ጎራ
ሞትህ ግን ያልገባኝ አማኝ መሳይ ከንቱ
ሌላ ማንም አይደል እኔ ነኝ አቤቱ!!

ኢይዝራኤል


@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gititm

#join and #share
434 views𝓜𝓮𝓷𝓽𝓮 ²⁵, 03:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 09:33:06 #እቴ_ውቤ


እቴ ውቤ ሙሽራዬ/2/
የባሕርየ መመኪያዬ
የክብር አክሊል መጽናኛዬ፡፡
ምሥራቅ ሆነሽ ፀሐይን ወልደሽ
ደኅንነት ሰላም በእጅሽ ይዘሽ
ለዲያብሎስ መርዶ ሆነሽ፡፡
ሻማ ሆነሽ ልታበሪ
ድርሺልኝ ስትበሪ፡፡
ሱላማጢስ አንቺ እናቴ/2/
ፈጥነሽ ነይ እመቤቴ
በአንቺ ሊጠግ የአዳም ቁስሉ
ሊጠፋልን ሊከስምልን
ያ የሲኦል ነበልባሉ፡፡
እቴ ውቤ እመቤቴ/2/
ፍጠኚልኝ ነይ በሞቴ
ለእርቃኔ ልትሆኚኝ ልብስ
ለሕመሜ ልትሰጪኝ ፈውስ
ረሀቤም እንዲታገስ
ሕብስት ይዘሽ ሆነሽ መቅደስ
ውዴ ነይ ከሊባኖስ፡፡
ክብር ሰጥቶሽ ህያው ልጅሽ
ወረቅ ለብሰሽ ተጎናፅፈሽ
የምትቆሚ በልጅሽ ቀኝ
እኔ ኃጡኧን አማልጅኝ አክብሪኝ
ውዴ እርሺው ያን ቤትሽን
የቀድሞውን ያባትሽን፡፡
ውቤ ውዴ እመቤቴ/2/
የክብር ማማ ሰገነቴ
መርሕ ፋና ለህይወቴ
ፈጠኚልኝ ነይ በሞቴ/2/


@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gititm

#join and #share
465 views𝓜𝓮𝓷𝓽𝓮 ²⁵, 06:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 07:20:29
ድንግል አርጋለች
.

.
መጥቁል በተንኮል - ከማይደርስበት
ሄሮድስ ሰይፍ ይዞ - ከማይሄድበት
ልቧ በሀዘን - ከማይጎዳ
ከድካም ዓለም - ከምድር ጓዳ
ሰማይን ሆና - ሰማይ ሄዳለች
በእውነት ድንግል አርጋለች።
.
.

ሰዶም፣ ገሞራ - ከሱባማ
ሱባዮንና - አድያማ
ከእሳት ገብተው - ከነደዱበት
በኃጥአት ምክንያት - ሞትን ካዩበት
የኖህን ዘመን ሰው - በእርጥብ እሳት
ከለበለበው - የግፍ ትኩሳት
ከዚሁ ምድር - ከቅጣት ሰፈር
እንዳይገባት - ለእሷ መደመር
ሰማይን ሆና - ሰማይ ሄዳለች
በእውነት ድንግል አርጋለች።
.
.
በሰማይ ሆነው - ስለሚጣሯት
ሊያይዋት ጓግተው - ተነሽ እያሏት
በህብረ ምሳሌ - በአፈ ነቢያት
ሁሉም ሠራዊት - ሁሉም መላእክት
ድንቅ አቀባበል - እያደረጉ
እሷኑ ሆኖ - የሰማይ ጥጉ
ለአምላክ ማደሪያ - የሚሆን ማደሪያ
ማረፊያ ክፍሏ - ስሙ መጠሪያ
አንክሮ ሆኖ - ለቅዱሳኑ
ለዚህም ደስታ - እንዲፋጠኑ
ሰማይን ሆና - ሰማይ ሄዳለች
በእውነት ድንግል አርጋለች
.
.
የምድሩን ልትስብ - ወደ ከፍታ
ልትጎትተው - ወደ እርፍት ቦታ
ለድል ትንሳዔ - አብነት ሆና
ቶማስ እንዳያት - ከፍላ ደመና
የኛስ መመኪያ - በቀኝ ቆማለች
ሰማይን ሆና - ሰማይ ሄዳለች
በእውነት ድንግል አርጋለች።

(አክሊሉ ደበላ ነሐሴ 16/2009ዓ.ም)

@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gititm

#join and #share
389 views𝓜𝓮𝓷𝓽𝓮 ²⁵, 04:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 18:35:01 #ደብረ_ታቦር


መለኮት ተገለጦ ብርሃንን አበራ፣
በተቀደሰችው የታቦር ተራራ።
የአብ አባትነት የወልድ ልጅነት፣
በግልጽ ታወቀ ተነገረ በእውነት።
ዮሐንስ ጴጥሮስ ያዕቆብን ጠርቶ
ሙሴን ከመቃብር ከሙታን አሥነስቶ
ከብሔረ ሕያዋን ኤልያስን አምጥቶ
በአምላክነቱ ፍጹም አንጸባርቆ
በሕያው መለኮት በብርሃናት ደምቆ
አብም ተገለጠ በብሩህ ደመና፣
የምወደው ልጄ ክርስቶስ ነውና።
እርሱን ብቻ ስሙት እስከ ዘለዓለም፣
ሕይወትን በእርሱ እንጂ ያለርሱ አትድኑም።
ብሎ ስለልጁ በግለጽ መሰከረ፣
አምላክነቱንም በተግባር ነገረ።

"...ታቦርና አርሞንዔም በስምኽ ደስ ይላቸዋል፤ ክንድኽ ከኀይልኽ ጋራ ነው፤ እጅኽ በረታች ቀኝኽም ከፍ ከፍ አለች።" መዝ ፹፰፥፲፪




@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gititm

#join and #share
428 views𝓜𝓮𝓷𝓽𝓮 ²⁵, 15:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 06:37:22 #ደብረ_ታቦር

ከደብሮች ሁሉ ልቀሽ
እውነትን ብርሃን አጥልቀሽ
ተንቀሽ የነበርሽ ተራራ
አንቺ የሚስጥር ስፍራ
የመለኮት ብርሃን በር
የሥሉስ ቅዱስ ሚስጢር
ልቆ ያታየብሽ መንበር
ደብረ ታቦር !!!
ከአድማሳት ከፍ ከፍ ብሎ
ያስምሽ ተረፈ ውሎ
የተዘከረው በአለሙ
ምን ይሆን ወርቅ ስሙ?
ምን አገኘሽ የኔ ታቦር
እንዲያ ተከፍሎ የብርሃንሽ በር
የክብሩ ግርማ የዋጠሽ
እኮ ማነው የረገጠሽ
ጌታሽ ነው አሉ ስሰማ
ከተራራሽ አናት ማማ
የብረሃን ጉንጉን ሻማ
የጎነፀፈሽ በግርማ
ደብረ ታቦር

ከተራሮች አንቺን መርጦ
ከነ አባቱ ተገልጦ
ደጅሽን ሳይንቅ ማክበሩ
እንዴት እንዴት ይሆን ሚስጥሩ?
ይሄንንም አውቆ ዳዊት
ተናግርዋል አሉ በትንቢት
ታቦር ወአርማንኤም በሚል ቅኔ
በስሙ ተደሰቱ የኔ
እያለ ዘመረ በክብር
የዛችን ተራራ ሚስጢር
ያልብ አምላክ ዳዊት
የተናገረው ትንቢት
ለካ ይሄ ኖርዋል ግብ
ደጅሽ በብርሃን ማበቡ
ብሉ በዚያች የብረሃን እልፍኝ
የዘላለም ደስታ ልናገኝ
አስቦ በቅፅጰት እውነቱ
ገርሞትም አይደለ ከስተቱ
የብረሃን ፀዳል ድምቀቱ
እኮ እንደምን አይገርመው
ሙሴ እና ኤለያስ ቆመው
ክብሩን ሲያውጁ እያዩ
ማነዉ የሙሴን አምላክ ሙሴ ባዩ
ሲል ሙሴ ባህር ከፋዩ
የኤልያስንስ ክብር ጌታ
አውርደውት ከሰው ተርታ
ኤለያስ ባዮቹ እነማን ናቸው
ሲል ኤለያስ ገርሙዋቸው
የሥሉስ ቅዱስ ሚስጢር
የተገለጠብሽ መንበር

ደብረ ታቦር

ይሄን ሲያዩ ሃዋርያቱ
በድንጋጤ ሲመቱ
ደግሞ ወርዶ አባቱ
ልጄን ስሙት በማለቱ
በፍረሃት ማእበል ሲንገላቱ
ይሄን ሁሉ ሚስጥር በመታየቱ
በአንቺ አይደለ ታቦር
መገለጡ የሦስትነት ሚስጥር
ጥንትስ ታሪክሽ ተዘክሮ
መቼ ያልቃል ተነግሮ
እንዲያ ድንቅ
እንበል እንጂ ድንቅ!ድንቅ!
የብረሃንሽ ሰንደቅ

ከአድማሳት ልቆ ሲደምቅ
ክብር እንበልሽ ክብር!ክብር!
አንቺ እውነተኛ የሚስጥር በር
የሥሉስ ቅዱስ ነገር
የተገለጠብሽ መንደር

ደብረ ታቦር

ታቦር አንቺ ታድለሻል
የማይቻለውን ችለሻል
ለመሆኑ እንዴት ቻልሺው ታቦር!
ያን እውነተኛ ፍቅር

ከመንበሩ የተሳበ ንጉስ
ከብረሃን ሰረገላው ሲፈስ
መሰረትሽ ሳይናጋ
ባለበት ቆሞ የረጋ
ምን ይሆን ሚስጥሩ የፅናትሽ
በፊቱ ቆመሽ መታየትሽ??
ልብሱ ነጭ ሆኖ በረድ
አብም ከሰማይ ሲወርድ(ድምጽ ስልክ)
ዙርያው በክብር ደመና
ተመልቶ በብርሃን ፋና
ሙሴ ከመቃብር ተጠርቶ
ኤለያስ ከቤሄረ ሄያዋን መጥቶ
በእየሩሳሌም ስለ ሚሆነው
ሲወያዩ ላስተዋለው
ምን ይመስል ይሆን ገፁ
የብርሃን መለኮት መገለፁ
የሥሉስ ቅዱስ ሚስጢር
ልቆ ይታየብሽ መንደር

ደብረ ታቦር

ደግሞ የሃዋርያቱ
የእነዚያ የሦስቱ
ጴጥሮስ ያዕቆብ ዮሃንስ
በድንጋጤ ፈረስ
ሲጋልቡ ርደው
እንደ ቄጤማ ወርደው
ከስሩ የተነጠፈው
ምን ይሆን ምክኒያቱ?
ጴጥሮስ ተሸብሮ
ናላው በድንጋጤ ዞሮ
ለእያንዳንዳቹ በጋር
ሦስት ዳሶችን እንስራ
ያበራሽ ይበራ ስሙ ይግነን
ዛሬም ለእኛ በርሃኑ ይሁን
ገኖ የገነነ በፍቃዱ
በሪ ይሁንልን ሠንገዱ
ክብሩን ከፍ ከፍ ወደ ላይ
ከሰማይ ሰማያት በላይ
እንዲሁም በምድር በቀላይ
የ!!አምላካችን አዱናይ
ክብርሽ ዛሬም ነገም ይነገር
መሆንሽ እውነተኛ የብረሃን በር
የሥሉስ ቅዱስ ሚስጥር
የተገለጠብሽ መንበር
ደብረ ታቦር

@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gititm

#join and #share
469 views𝓜𝓮𝓷𝓽𝓮 ²⁵, 03:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 06:56:49 ብርሃን ያለበሰ እርሱ ነው፡፡ ለመላዕክት፣ ለጻድቃን ለቅዱሳን ሁሉ የጽድቅ ብርሃንን ያደለ የማይጠፋ ብርሃን እርሱ ነው፡፡

በጻድቁ አባት በገብረ መንፈስ ቅዱስ ገድል እንደምናነበው ለጻድቁ የጽድቅ ምስክር ሆኖ ለረዥም ጊዜ የቆየውን ዓይነት ብርሃን አይደለም፡፡ አባ አትናቴዎስ ስለ ንስሃውና እመቤታችንን ስለ መውደዱ ካገኘው ብርሂት እድ ጋር እንዴት እናነጻጽረዋለን? ሊቀ ነቢያት ሙሴ ከተራራው በወረደ ጊዜ የእስራኤልን ዐይን የበዘበዘ ገጸ ብርሃን ምሳሌው ሊሆን አይችልም፡፡ እርሱ ለቅዱሳን ብርሃንን የሚሰጥ የብርሃናት አምላክ፣ ሙሴን ብሩህ ያደረገ፣ ለአባ አትናቴዎስም ብርሂት እድን የሰጠ... ነው እንጂ፡፡ በቅዱሱ ተራራ ማደሪያውን ያደረገ አምላክ በዚህ ተራራ ብርሃነ መለኮቱን ገለጠ፡፡

ይህን ልዩ ምስጢር በገለጠባት ቅዱስ ተራራ ደጋግሞ የአብን ምክር ሰማን አብ በደመና "የምወደው የምወልደው ልጄ እርሱ ነው እርሱን ስሙት" ብሏልና፡፡ በከዊን /ከዊነ ቃል ከዊነ ልብ ከዊነ እስትንፋስ/ ሦስት ሲሆኑ በኩነት አንድ ናቸውና በደብረ ታቦር ልብሱ እንደ በረዶ ነጥቶ በአካለ ሥጋ ብርሃነ መለኮቱን በገለጠው ወልድ ቃልነት አብ በደመና "የምወደው የምወልድ ልጄ" በማለት መሰከረ፡፡

ሙሴ ወ ኤልያስ 

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሕያዋንም የሙታንም አምላክ ነው፡፡ ሙሴን ከመቃብር ኤልያስን ከብሔረ ሕያዋን አምጥቶ ያስመሰከረውም ይኸንኑ ነው፡፡ ወንጌልም ስለምስክርነታቸው ሲናገር "በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው ተነጋገሩ" ይላል፡፡ አስቀድመው በፊልጶስ ቂሣርያ ሙሴ፣ ኤልያስ ይሉሃል ብለውት ነበር፡፡ ሙሴ "የኔን የሙሴን አምላክ እንዴት ሙሴ ‹‹ሰው፣ ሩቅ ብእሲ፣ መዋቲ..../ ነህ ይሉሃል ? እኔ ባሕር ከፍዬ ባሻግር፣ ከዐለት ውኃ ባፈልቅ.... እስራኤልን ከዳግመኛ ሞት ላድናቸው ያልተቻለኝን፡፡ አንተ ከዘለዓለም ሞት የምትቤዥን ነህ" በማለት መስክሮለታል፡፡

ኤልያስም የእኔን የኤልያስን አምላክ እንዴት ኤልያስ /የሕያዋን ብቻ፣ የነፍስ ገዥ ብቻ/ ነህ ይሉታል? እኔ እሳት ከሰማይ ባወርድ ከሰጠኸኝ ነው፡፡ አንተ በሞትህ ዓለምን የምታድን ነህ ሲል መስክሮአል፡፡

ከዚህ ምስክርነትና መገለጥ የተነሣ አንተ ስንሞት እያስነሳኸን፣ ሕብስት እያበረከትህ እያበላኸን፣ ሙሴ መና እያወረደ ደመና እየጋረደ ከጠላት እየተጋደለ፣ ኤልያስ እሳት እያዘነመ ቤት /ዳስ/ ሠርተን በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው፡፡ የሚጠይቁን ሰዱቃውያን፣ የሚያሳድዱን ጸሐፍት ጋር ምን አጣላን በዚህ እንቆይ በማለት እስኪመኝ አደረሰው፡


ትውፊቱ

ቡሄ

ቡሄ ማለት ብራ፣ ብርሃን፣ ደማቅ ማለት ነው፡፡ ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት በዓል የሚዘከርበት እና ለበዓሉም ችቦ ስለሚበራ የብርሃን በዓል በማለት የቡሄ በዓል እንላለን፡፡

ወቅቱ የክረምት ጨለማ አልፎ የብርሃን ወቅት፤ ሰማይ ከጭጋጋማነት ወደ ብሩህነት የሚለወጥበት፤ የመሸጋገሪያ ወቅት ነው፡፡ "ቡሄ ከዋለ የለም ክረምት፤ ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት" እንዲሉ፡፡ በሌላ በኩልም "ቡኮ/ሊጥ" ተቦክቶ ዳቦ የሚጋገርበት "ሙልሙል" የሚታደልበት በዓል በመሆኑ ቡሄ ተብሏል፡፡

ጅራፍ

በደብረ ታቦር በዓል በትውፊታዊ መልኩ የሚታየው ምስጢር በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው የጌታችን ምስጢራዊ ሞቱ ነው፡፡ ጅራፍ መገመድ እና ጀራፍ ማጮኸ ሁለት ዓይነት ምስጢር ይዞ የሚከወን ትውፊታዊ ተግባር ነው፡፡ የመጀመሪያው ግርፊቱን እና ሞቱን እናስብበታለን፡፡ እንዲሁም ድምፁን ስንሰማ የባሕርይ አባቱን የአብን ምሰክርነት ቃል፣ እንደ ነጎድጓድ ድምፅ ያስታውሰናል፡፡

የጅራፍ ትውፊታዊነት /ውርስ/፣ መጽሐፋዊ ትምህርትና ምስጢር ጠብቆ ለትውልድ እንዲተላለፍ ለማድረግ ጨዋታውን በተራራማ አካባቢ፣ ከመኖሪያ ቤት ርቆና፣ በሜዳ ማድረጉ ጠቃሚ ነው፡፡ ጅራፍን በርችት መቀየር የሚያመጣውን የምስጢር ተፋልሶ ብቻ መመልከት ከማኀበራዊ ጎጂ ገጽታው በላይ እንድናስወግደው ያስገድደናል፡፡


ችቦ

ችቦ የጌታችንን ብርሃነ መለኮት መገለጥ የሚያመለክት ነው፡፡ በመሆኑም ችቦ ለኩሰን በዓሉን እናከብራለን፡፡ የዚህ ትውፊታዊ የት መጣ ግን በብርሃኑ ድምቀት የቀኑን መምሸት ያልተረዱ እረኞች በሜዳ ቀርተዋልና ወላጆች ከመንደር ችቦ ለኩሰው ልጆቻቸውን ፍለጋ ሔደዋልና ታሪኩን እያዘከርን በዓሉት እናከብራለን፡፡

የችቦው መንደድም ሌላ ትርጉም አለው፡፡ አንድ ምእመን ለሌላው ምእመን መካሪ አስተማሪ መሆኑን፣ መከራ እየተቀበለም አርአያ ምሳሌ ብርሃን መሆኑን ያሳያል፡፡ በሃይማኖትም አርአያ ምሳሌ ይሆንላቸዋል፡፡

ሙልሙል

በችቦ ብርሃን ልጆቻቸውን ፍለጋ የወጡ ወላጆች ዳቦ ጋግረው ይዘውላቸው ወጥተዋል፡፡ ስጦታው ቤተሰባዊነትን፣ ፍቅርንና መተሳሰብን መግለጫ ነው፡፡ ወደ ቤታችን "ቡሄ" እያሉ ለሚመጡ አዳጊዎችም ዘምረው እንዳበቁ የሚሰጥ "ሙልሙል" ዳቦ አለ፡፡ ለምሳሌ ሐዋርያት ምስራች ሊነግሩን፣ ወንጌል ሊሰብኩን በደጃፋችን ቆመው "ቡሄ በሉ" የሚሉንን አዳጊዎች የሚበሉትን መስጠታችን ምሳሌያዊ /መጽሐፋዊ/ ነው፡፡ ጌታችን ደቀ መዛሙርቱን ባስተማራችሁበት፣ በደረሳችሁበት ተመገቡ ብሏቸዋል፡፡ /ማቴ 10÷12/ ሕፃናቱም ሊዘምሩ ሲመጡ ዳቦ መስጠት ልማዳዊ ብቻ አይደለም፡፡ ሕፃናቱ የደቀመዛሙርት ምሳሌ ናቸው፡፡ መዝሙራቸው ደግሞ ሐዋርያት "የምስች" ይዘው የመምጣታቸው ምሳሌ ነው፡፡

ሐዋርያት በገቡበት አገር አስተምረው አጥምቀው የጸጋ ልጅነትን አሰጥተው በረከት አድለው እንደሚሔዱም፣ ልጆችም ዘምረው፣ አመስግነው፣ መርቀው "ውለዱ ክበዱ፣ ሀብት አግኙ፣ የመንግሥተ ሰማያት ወራሾች ያድርጋችሁ ...." ይላሉ፡፡

በአጠቃላይ በዓለ ደብረ ታቦር ከነዚህ ምስክር ካላቸው ትምህርቶቹ፣ ምስጢር ከሚራቀቅባቸው ትርጓሜያቱና ከትውልድ ትውልድ በቅብብል በተላለፈው ቅዱስ ትውፊት ጋር ሃይማኖታዊ ባሕል ሆኖ ሊቀጥል ይገባዋል፡፡ ይህን ማድረግ የሚቻለው ግን አዳጊዎች ሃይማኖታዊ ትውፊቱን ይዘው እንዲያድጉ ጥቆማ በመስጠት፣ ግጥም በመግጠምና ምስጢሩን በማብራራት የመጀመሪያዎቹ ባለድርሻዎች ወላጆች ናቸው፡፡ አንዳንድ ጊዜ የሚሰሙ ግጥሞች ስድብ፣ ፌዝና ሥላቅ የተቀላቀለባቸው ይሆናሉ፡፡ ሕፃናቱም ዝማሬውን ሲጀምሩ "ከሰጡን እንነሣ ከነሱን እናርዳ" ብለው ይጀምሩታል፡፡ ከሰጡን እንመርቃለን ካልሰጡን እንራገማለን በማለት፡፡ አሳሳቢው ነገር ደግሞ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን ወደ ገንዘብ ማግኛነት የቀየሩ ሁኔታዎች መታየታቸው ነው፡፡ ዳቦ /ሙልሙል/ ትምህርቱንም፣ ምስጢሩንም፣ ትውፊቱንም በአግባቡ ልንጠቀምበት ይገባል፡፡

ቤተክርስቲያን የምስጢር ግምጃ ቤት ናት የምታከናውነውን ሁሉ ከበቂ መረጃ ጋር ነው ተግባራዊ የምታደርገው፡፡ በተለይ ወጣቱ ክፍል ይህንን አውቀን ተረድተን ለቀሪው ትውልድ ማስተላለፋ እንችል ዘንድ ከክፉ ጠላት ከሰይጣን ፈተና፣ በሽታ ከመሳሰሉት ችግሮች ለመዳን ወደ ተራራዋ ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመሸሽ ከክፉ ነገሮች ሁሉ ማምለጥ ይቻላል፡፡ በቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር የሚጠለሉ ሁሉ ዕድሜያቸው ይረዝማል፡፡ አስተዋዮችም ይሆናሉ ሁሉን ማየትና የሚጠቅማቸውን መምረጥ ይችላሉ በሥነ-ምግባር የታነፁ አገርንና ወገንን የሚጠቅሙ ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያን በመጠጋት ከክፉ ሁሉ የሚያመልጡ ይሆናሉ ለዚህም የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ይርዳን፡፡
1.6K views𝓜𝓮𝓷𝓽𝓮 ²⁵, 03:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ