Get Mystery Box with random crypto!

ማኅቶት

የቴሌግራም ቻናል አርማ mahetotorto — ማኅቶት
የቴሌግራም ቻናል አርማ mahetotorto — ማኅቶት
የሰርጥ አድራሻ: @mahetotorto
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.11K
የሰርጥ መግለጫ

ለኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች!
ልትጠቀሙበት የሚገባ ምርጥ ቻናል!
✔ማህቶት ብርሃን ነዉ!❤
✔መንፈሳዊ እዉቀትን እያገኙ❤
✔ስለሐይማኖቶ ማወቅ የፈለጉትን እየጠየቁ ❤
✔ጊዜዎን በፍሬ የሚቀይሩበት❤
✞ይቀላቀሉን✞
✋ሐሳብ አስታየት ማንኛዉም መንፈሳዊ ጥይቄ ካልዎት ታች በላዉ link ያድርሱን🙏
@Mahetotbot
Mahetot

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-01-30 15:35:46 ​#ቀሳ
(#የፀበል_ስንብት_ምልከታ_ክፍል_1)

"አንተ ኖሮህ ሌሎች የሚጠይቁት ምንአልባት በመለኮታዊ ሐይል ብቻ የሚቻል ነዉ ፤ ሌሎች ኖሯቸዉ አንተ የምትጠይቀዉ ግን የጎጆህን በሮች ከፍቶ ዙሪያህን የመቃኘት ያህል ጥረት ብታደርግ በቀላሉ የሚመለሱ ሊሆኑ ይችላሉ ። "

አዉቃለሁ ጊዜ የለህም፤ የሳምንቱን ቀናት በስራ ነዉ የምታሳልፈው ፤ buys ነህ ፤ የኑሮ ዉጣ ዉረድ ሰቅዞ ይዞሐል...!

ቢሆንም ሮጥ ብለህ እስኪ በየፀበሉ ከአራቱም ማዕዘናት ዕልፍ የስጋና የነፍስ ጥያቄያቸዉን አንዥርግገዉ የሚተሙ ወገኖችህን ተመልከታቸዉ...!

ግማሹ እግሩ ታስሮ መራመድ ተስኖት በራስ መተማመን መንፈሱን የስጋ ደዌ ስልቦት በሌሎች ዕርዳታ ከቦታ ቦታ ይንቀሳቀሳ ... አንተ ግን አትንኩኝ ባይ ነህ ፤ተሳስቶ የነካህም ይቅርታ ጠይቆህ ነዉ የሚያልፈዉ

ገሚሱ የሰዉነት ክፍሎቹ መስራት አቁመዉ አንተ ሮጥ ብለህ አንድ አፍታ የምታደርጋቸዉን ቀላል ነገሮች ማድረግ ቅንጦት (ጭራሽ የማይታሰብ ) ሆኖበት ታገኘዋለህ

ከፊሉ በመንፈስ መታወክ ከሰዎች ተገልሎ በሰንሰለት ታስሯል። አንተ ግን ዛሬም በናፍቆት የምትገናኛቸዉ ወዳጆች አሉህ ፤የማይረሱ ጊዚያትን ከቤተሰብህ ጋር እያሳለፍክ ነዉ ፤ ከትላንት ትማራለህ ፤ ዛሬን ትኖረዋለህ ፤ ለነጌህ ታቅዳለህ...

እነዚህን ስትመለከታቸዉ የራስህን ጥያቄዎች ትዘነጋቸዉና "ጌታ ሆይ እባክህ ፈዉስን ላክላቸዉ ምህረት አድርግላቸዉ መድኃኒትነትህን ግለጥ ".... እያልክ መለመን ትጀምራለህ (ሂድና ሞክረዉ)

በየሆስፒታሉና የየሰዉ ቤት የሸፈነዉም ገመና ከዚህ የተለየ አይደለም!

"አንተ ኖሮህ ሌሎች የሚጠይቁት ምን አልባት በመለኮታዊ ሐይል ብቻ የሚቻል ነዉ። ሌሎች ኖሯቸዉ አንተ የምትጠይቀዉ ግን የጎጆህን በሮች ከፍተህ ዙሪያህን የመቃኘት ያህል ጥረት ብታደርግ በቀላሉ የሚመለሱ ሊሆኑ ይችላሉ"

#ለዚህ_ብቻ_ተመስገን

@mahetotorto
@mahetotorto
@mahetotorto
@mahetotorto
1.8K viewsedited  12:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-03 11:40:19 ​#ለባለ_ልደቱ_ምን_አዘጋጀን?

ምንም እንኳ
እንደ ሰብአ-ሰገል
ንፁህ ነህ እያልኩኝ - ወርቅ ባ'ላመጣም ለፈዋሽነትህ - ከርቤ በ'ላቀርብም
ሊቀ ካህን ስልህ - ዕጣን ባልገብርም
ለልደት ስጦታህ
ዙፋን እንዲሆንህ
ልቤን አልሰስትም

እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት ዋዜማ በሰላም አደረሳችሁ

ይህን ፅሁፍ በልደቱ ዋዜማ የለጠፍኩት ለባለ ልደቱ የልደት ስጦታ የማዘጋጃ ጊዜ እንዲሆነን በማሰብ ነዉ!

አንድ ጥያቄ አለኝ

ወዳጃችሁ ልደቱን ታከብሩለት ዘንድ ቤቱ ጋበዛችሁ እንበል ...እናንተም ያስደስተዋል ብላችሁ የገመታችሁትን ስጦታ ይዛችሁ ወዳጃችሁ ቤት ተገኛችሁ ከዚያም የስጦታዉ ስዓት ሲደርስ ዋናዉ ልደት አክባሪዉ እያለ የተወለደው ተቀምጦ ቤቱ ድረስ የጋበዛችሁን አስቀምጣችሁ ሁላችሁም ያመጣችሁትን ስጦታ እርስ በእርስ ብትሰጣጡ ባለ ልደቱ ልደት አክባሪዉ ምን የሚሰማዉ ይመስላቸዋል?

ወዳጅ ብዬ የጠራዋችሁ ጤነኞች አይደሉም እንዴ እኔን አስቀምጠዉ ለራሳቸዉ ስጦታ የሚሰጣጡ ?...

የተወለደዉን ክርስቶስን አስቀምጦ የኛ እርስ በእርስ ስጦታ መሰጣጠት ምን ይሉታል ?

በእርግጥ ስጦታ የፍቅር ምለሰክት ነዉ ተስፋ ይገለፅበታል መዉደድ ነፍስ ይዘራበታል...ለገና ስጦታ መሰጣጠት በራሱ የከፋ አይደለም መልካም ነዉ ...ግን ዋናዉን ባለ ልደት ክርስቶስን ረስተነዉ ለእርሱ አንድም ስጦታ ሳናዘጋጅለት ከሆነ ችግሩ እዛ ላይ ነዉ

ታዲያ ምን እንስጠዉ?

#በንስሐ
_አንፅተን_ልባችንን_እንስጠዉ!

#እኛዉ_እንድንባረክበት_ዘመናችንን_ለእርሱ_መባ_አድርገን_ለልደቱ_እንለግሰዉ
በተቻለን_መጠን_የማይጠቅመንን_የስጋ_ፍላጎታችንን_አሳልፈን_እንስጠዉ
.
.
.
#በድጋሚ_መልካም_የልደት_በዓል_አልኳችሁ

በዚያም የመልካም ምኞት መግለጫ share ይደረግ
@Mahetotbot
@Mahetotbot
@Mahetotbot
1.5K viewsedited  08:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-03 09:10:54 ​#የገና_ቀን_አርብ_ዉሏል_ፆም_ነዉ?


የ በዓለ ልደት ዓርብ ቀን መዋል ይበላል ወይስ አይብላም የሚል ጥያቄ ዘንድሮም በርክቷል።

የጌና (በዓለ ልደት) እና ጥምቀት ረቡዕ ወይም ዓርብ ቀን ቢውል ምን እናድርግ ለሚለው ጥያቄ መጽሐፈ ስንክሳር በስንክሳር ዘወርኃ ጥር 10 ይህን ይላል።

"በዚች ዕለት ምእመናን እስከ ምሽት እንደመጾሙን ያዘዙበት ምክንያቱ ይህ ነው የልደትና የጥምቀት በዓል በዓል በረቡዕ ወይም በዓርብ ቀን ቢሆን በበዓለ ኃምሳ የሚበላውን የጥሉላት መብል በጥዋት በመብላት ምእመናን ሁሉ በዓሉን እንዲአከብሩ የከበሩ አባቶቻችን ሐዋርያት አዝዘዋል እሊህ ሁለቱ የእግዚአብሔር ታላላቅ በዓላቶቹ ናቸውና።" (ስንክሳር ዘወርኀ ጥር 10)

አርብ ቀን ፆም አይደለም ሐሙስ እስከ ምሽት አንድ ሰዓት ተፁሞ አርብ የበዓሉ ለት ይበላል...

ይህም የሆነበት የጌታ የልደቱ ቀን በፍፁም ደስታ መከበር ስላለበት አባቶች የሰሩት ስርዓት ነዉ!

#share #ለሁሉም_ይድረስ
@Mahetotbot
@Mahetotbot
@Mahetotbot
1.1K viewsedited  06:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-30 17:20:05 ​#ቅዱስ_ዮሐንስ_ወንጌላዊ
(ክፍል ሶስት )

አባ ጀሮም ስለ ወንጌላዊው ሲገልጥ ዮሐንስ የመጨረሻውን በምድር የኖረበትን የዕድሜ ዘመን በኤፌሶን ከተማ እንዳሳለፈው ጽፏል፡፡ በዚህ ወቅትም እጅግ ከማርጀቱ የተነሣ “እርስ በራሳችሁ ተዋደዱ ይህ የጌታችን ትእዛዝ ነውና ይህን ከጠበቃችሁ ይበቃችኋል” የምትለዋን ቃል ብቻ ለደቀ መዛሙርቱ ይነግራቸው ነበር፡፡ ይህ የዮሐንስ የዘወትር ትምህርቱ ነው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም “አባታችን ለምን ኹል ጊዜ አንድ ዓይነት ትምህርት ታስተምረናለህ” ሲሉትም “ልጆቼ ይህ የጌታ ትእዛዝ ነው” በማለት ይመልስላቸው ነበር፡፡

ሐዋርያዊትና ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን የወንጌላዊው በዓል በየዓመቱ ጥር ፬ እና በየወሩ በ፬ እርሱ የደረሰው የቁርባን ምስጋና እንዲቀደስ ታዛለች፡፡

ቅዱስ ዮሐንስና የጌታ ሥዕል

ለጌታችን ሥዕል ምንጭ ከኾኑት አንዱ ወንጌላዊ ዮሐንስ ነው፡፡ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተሰቀለበት ዘመን የነበረው የሮማ ቄሣርጢባርዮስ ቄሣር ይባላል፡፡ የቄሣሩ ልጅም ታማሚ ነበር፡፡ ቄሣሩምየጌታን የማዳን ሥራ እየሰማና እነ ጲላጦስንም የጻፉለትን ደብዳቤእየተመለከተ “ከዚያ ደግ ሰው መቃብር ወስዶ ልጄን ማንባሳለመልኝ?” እያለ ይመኝ ነበር፡፡ በመጨረሻም ልጁን ወስደውበጌታ መቃብር ላይ ሲያኖሩት ከሕመሙ ስለተፈወሰለት ፍቅሩንለመግለጥ የጌታን ሥዕል የሚሥልለት ሰው ያፈላልግ ጀመር፡፡ከዚያ በኋላም ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ተገኘና ልክ በዕለተ ዓርብእንዳየው አድርጐ ሥሎ ሰጠው፡፡

ቅዱስ ዮሐንስና አስቸጋሪው የሽፍቶች አለቃ

አንድ ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ ከኤፌሶን ከተማ ተነሥቶ ክርስቲያኖችንለማስተማር ሲዘዋወር ወደ አንድ ትልቅ ከተማ ገባ፡፡ በዚያች ከተማየሚገኙ ምእመናንም ጊልስ ስለሚባልና በዐሥራዎቹ ዕድሜ ክልልስላለ አንድ ወጣት ታሪክ አጫወቱት፡፡ ወጣቱን በጣም ይወዱትስለነበርና እናትና አባቱ ስለሞቱ “የሚንከባከበውና የሚያስተምረውካጣ ሊበላሽ ይችላል” ብለው ለቅዱስ ዮሐንስ ነገሩት፡፡

ቅዱስ ዮሐንስም ይኽንን ሲሰማ ወጣቱ ጊልስን ወደ ከተማይቱ ጳጳስወሰደውና “እንደ ልጅህ ተንከባከበው፤ እውነተኛ ክርስቲያንምአድርገው” ብሎ ሰጠው፡፡ የከተማዋ ጳጳስም ደግ ስለነበረ ጊልስንበደስታ ተቀበለው፡፡ ዘወትርም ያስተምረውና ይንከባከበው ነበር፡፡በመጨረሻም የአከባቢው ምእመናን በተሰበሰቡበት ጊልስተጠመቀ፡፡

ከዚህ በኋላ ግን ነገሮች መቀያየር ጀመሩ፡፡ እኒያ አባት ሥራ በጣምሰለበዛባቸው ጊልስን “መቼም ተጠምቋል” ብለው እንደ በፊቱመቆጣጠርና ማስተማሩን ተዉት፡፡ ጊልስም የለመደው የአባትነትፍቅር ሲያጣ ወደ ከተማ ወጣ ብሎ ከእኩዮቹ ጋር መቀራረብጀመረ፡፡ ጓደኞቹ ግን መልካም አልነበሩም፡፡ ጠጭዎች፣ቁማርተኞችና ተደባዳቢዎች ነበሩ፡፡

አንድ ቀን ማታ በአንድ መጠጥ ቤት ውስጥ ጊልስና ጓደኞቹ ሲጠጡአመሹ፡፡ኹሉም ሰክረው በያሉበት ሲወደቁ ጊልስ ብቻውን ቀረ፡፡በመጨረሻም የኹሉንም የመጠጥ ሒሳብ ከፍሎ ያለውን ገንዘብጨረሰ፡፡ በነጋታው ጊልስ ለጓደኞቹ “ለእናንተ ስል ገንዘቤን ኹሉአባከንኹ፤ አሁን ባዶ ኪስ ሆኛለኹ” ብሎ ነገራቸው፡፡ ኹሉምሳቁበትና “ጅሉ ጊልስ! እኛ ገንዘብ ከየት የምናመጣ ይመስልኻል?ይልቅ የምታገኘውን አጋጣሚ ተጠቅመኽ ስረቅ” አሉት፡፡

በዚህ መሠረት ጊልስና ኹለቱ ጓደኞቹ የአንድ ሰው ቤት ሰብረውገቡና ገንዘቡንና ጌጣጌጡን ዘረፉ፡፡ በዚህም የተነሣ ጊልስ “መስረቅማለት በጣም ቀላል ሥራ ነው” ብሎ አመነ፡፡ ከዚያ በኋላ ጊልስናጓደኞቹ የታወቁ ዘራፊዎች ኾኑ፡፡ እነርሱ ባሉበት መንገድ ማንምበጤና ማለፍ አይችልም ነበር፡፡ አንድ ቀን ሰው ሲደበድቡ ነፍሱበእጃቸው ስለ ጠፋች ጊልስና ጓደኞቹ ከተማዋን ጥለው ጠፉ፡፡ከጥቂት ጊዜ በኋላም የጊልስ ስም በአከባቢው እየገነነ ስለ መጣ ሰውኹሉ ይፈራው ጀመር፡፡ እርሱና ጓደኞቹ አላፊ አግዳሚውንአላስቀምጥ አሉ፡፡ መንገደኞች ኹሉ በሰላም መጓዝ፣ ነጋዴዎችምበጤና መነገድ አልቻሉም፡፡ ጊልስ አለቃቸው ነበር፡፡ መግደልናመዝረፍም የዘወትር ሥራቸው ኾነ፡፡
ከጥቂት ዓመታት በኋላ ግን ቅዱስ ዮሐንስ ወደዚያች ከተማ መጣ፡፡እኒያን ጳጳስም ስለ ወጣቱ ጊልስ ጠየቃቸው፡፡ እርሳቸውም በጣምአፍረውና አዝነው፡- “ያልከኝን አልሰማኹም፤ ያዘዝኸኝንምአልፈጸምኩም፡፡ ጊልስ ዛሬ ሰው ኹሉ የሚፈራው ወንበዴ ኾኗል፡፡ዛሬ አላፊ አግዳሚውን አያስቀምጥም፡፡ ይህ ኹሉ ግን የእኔ ስሕተትነው” በማለት በፊቱ አለቀሱ፡፡

ቅዱስ ዮሐንስም ይህንን ሲሰማ በእጅጉ አዘነ፡፡ ወዲያውም ጊልስያለበትን ጠየቀና በፈረስ እየጋለበ ተጓዘ፡፡ የአከባቢው ምእመናን“ጨካኝ ናቸውና ይገድሉኻል” ቢሉትም አልተመለሰም፡፡

በተባለው ቦታ ሲደርስም ኹለቱ ሽፍቶቹ አገኙት....

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በወንጌላዊዊ ዮሐንስ ጸሎት ይማረን


(የመጨረሻዉ ክፍል ይቀጥላል...)
#share
@Mahetotbot
@Mahetotbot
@Mahetotbot
963 viewsedited  14:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-30 09:30:23#ቅዱስ_ዮሐንስ_ወንጌላዊ
(ክፍል ሁለት)

ቅዱስ ዮሐንስ በመጀመርያ የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዛሙር ነበር/ዮሐ.፩፡፴፭-፵/፡፡ በኋላ ግን ከታላቅ ወንድሙ ከያዕቆብ ጋር ሰዎችንእንደ ዓሣ በወንጌል መረብ ከዚሁ ዓለም ባሕር ለማጥመድ ጌታችንኢየሱስ ክርስቶስ የስብከት ሥራውን እንደ ጀመረ በቅፍርናሆምከተማ በገሊላ አጠገብ ሲመላለስ ሳለ ጠራው /ማቴ.፬፡፳፩/፡፡ እርሱምወዲያው ከወንድሙ ጋር ታንኳይቱንና አባቱን ትቶ ተከተለው፡፡ጌታችን ሲጠራው የ፳፭ ዓመት ወጣት እንደ ነበረም ሄሬኔዎስ የተባለደቀ መዝሙሩ ጽፏል፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ ከደቀ መዛሙርቱ ኹሉ የተለየ ፍቅር ስለነበረውጌታችንን እስከ እግረ መስቀሉ ድረስ ተከትሎታል፡፡ ለዚኽምመላው የሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖችን ወክሎ የእመቤታችንንእናትነት ከጌታ ተቀብሏል፡፡ በዚያች የመከራና የኑዛዜ ሰዓት የተገኘየቁርጥ ቀን ወዳጅ በመኾኑ በአደራ መልክ “እነኋት እናትኽ”ተብሏል፡፡ እርሱም ለእመቤታችን ልዩ አክብሮትና ፍቅር ስለነበረውበእናትነት ተቀብሎ ወደ ቤቱ ወስዷታል፡፡ አደራውን አክብሮበመጠበቅና በማጽናናትም ፲፮ ዓመት ሲታዘዛት ኖሯል /ዮሐ.፲፱፡፳፭-፳፯/፡፡

ሐምሌ ፭ የሚነበበው መጽሐፈ ስንክሳር እንደሚገልጠው ቅዱስዮሐንስ የስብከቱን ሥራዉን በኢየሩሳሌምና በአከባቢው የጀመረውወደ አንጾክያ ሄዶም ያስተማረው ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር ነው፡፡ከኢየሩሳሌም እስከ አንጾክያ በፈረስ ፳ ቀን ያስኬዳል፡፡ ቅዱስዮሐንስና ቅዱስ ጴጥሮስ ግን በእግዚአብሔር ርዳታ በአንዲት ሌሊትደረሱ፡፡ ዮሐንስም ወደ ከተማይቱ ቀደም ብሎ ገባና ስለ ሀገሩ ጥናትሲያደርግ የሀገሩ ሰዎች እጅግ ክፉዎች እንደኾኑ ተረዳ፡፡ ምንምእንኳ በክፋታቸው ቢያዝንም ቅዱስ ጴጥሮስ አጽናንቶ አደፋፈረውናወደ ከተማይቱ ገብተው በክርስቶስ ስም ወንጌልን ሰበኩ፡፡ ጣዖትንከሚያመልኩ ሰዎች ብዙ መከራ ቢደርስባቸውም በአንጾክያ ውስጥተአምራትን እያደረጉና በስብከት በክርስቶስ ወንጌል ብዙ ሰዎችንአሳመኑ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ከዚህ ሌላ ያስተማረባት ሀገር ሎዶቅያእንደምትባል ስንክሳሩ ይገልጣል፡፡ በከተማ አጠገብ ያለ ቄድሮስየሚባል ወንዝ ሞልቶ የሀገሪቱን ብዙ ንብረት በወደመ ጊዜ ቅዱስዮሐንስ ከቅዱስ ጴጥሮስ ዘንድ ሄደና በተአምራት የውኃውን ሙላትአቆመላቸው፡፡ ወደ ከተማዋም ገብቶ ብዙ ተአምራትን እያደረገወንጌልን ሰበከ፡፡ ካዩት ተአምራትና ከሰሙት ትምህርት የተነሣምብዙዎች አመኑ፡፡

ጥር ፬ በሚነበበው ስንክሳር እንደምናነበው ደግሞ ቅዱስ ዮሐንስ በሕይወቱ መጨረሻ አከባቢ ያስተማረው በእስያ ሀገር ሲኾን ዋናመንበሩም ኤፌሶን ነበረች፡፡ ዮሐንስ ወደዚህች ከተማ የመጣውከደቀ መዝሙሩ ከአብሮኮሮስ ጋር ነው፡፡ የስብከት ሥራቸውንበቀጥታ መጀመር ስላልቻሉም ሮምና የምትባል አንዲት ሞግዚትቤት ውስጥ ባሮች ኾነው ገቡ፡፡ እርሷም ዮሐንስን እንጨት ፈላጭ፣አብሮኮሮስን ደግሞ ውኃ ቀጅ አደረገቻቸው፡፡ አንድ ቀንከምታሳድጋቸው ልጆች አንዱን ይዛ ወደ ቤተ ጣዖት ስትገባዮሐንስና አብሮኮሮስ አብረዋት ገቡ፡፡ ያን ጊዜ በቤተ ጣዖቱ ያደረውሰይጣን እነ ቅዱስ ዮሐንስን ሲያይ የቤቱን ዕቃ አደናብሮ ወጣ፡፡አስከትላው የነበረው ልጅም በድንጋጤ ሞተ፡፡ ያን ጊዜ “የእናንተመምጣት ነው ለዚህ ኹሉ ያበቃኝ” ብላ ደበደበቻቸው፡፡ ቅዱስዮሐንስም “አስነሡልኝ አትዪምን?” ብሎ መለሰላት፡፡ “ያሁኑ ይባስ!ከመቼ ወዲህ ነው ደግሞ የሞተ ሰው የሚነሣው?” ብላ የበለጠተቆጣች፡፡ ይህን ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስና አብሮኮሮስ ጸሎት አቅርበውአስነሡላት፡፡ በዚህ ተአምር አምና ተጠምቃለች፡፡ በቤቷምየምእመናን ጉባዔ ተመሠረተ፡፡ እርሷም ለዚያ እመምኔት አድርገውሾሟት፡፡ ከዚያም በኤፌሶንና በአከባቢዋ ወንጌልን ለመስበክ ሰፊ በርተከፈተለት፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ በኤፌሶን በሚያስተምርበት ጊዜ ከኔሮን ቄሣር ቀጥሎበሮም የነገሠው ድምጥያኖስ (፹፮-፺፮ ዓ.ም) የራሱን ምስል አሠርቶእንዲሰገድለት ወደ ኤፌሶን ላከ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ግን ከምእመናንጋር ኾኖ ይህን ድርጊት ተቃወመ፡፡ ከዚያም ወደ ሮም ተወሰደናበፍል ውኃ ተሰቃይቶ በመንግሥት ላይ ያመፁ ኹሉወደሚታሠሩባት በደሴተ ፍጥሞ እንዲታሰር ተፈረደበት፡፡ ራዕዩንያየውና የጻፈውም በዚያ ቦታ ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ድምጥያኖስከተገደለ በኋላ ከግዞቱ ተመልሶ ሦስቱን መልእክታቱና ወንጌሉንእንደ ጻፈ ይነገራል፡፡

ስለ ቅዱስ ዮሐንስ የመጨረሻ ሕይወት ኹለት የተለያዩአመለካከቶች አሉ፡፡ አንደኛው በዮሐ.፳፡፳-፳፫ ላይ የተጻፈውንመነሻ በማድረግ “ዮሐንስ ሞትን አልቀመሰም” የሚል ሲኾንኹለተኛው ደግሞ በማር.፲፡፴፰-፴፱ የተጻፈውን ቃል በመጥቀስ“የጌታን የሞት ጽዋ ጠጥቷል፤ የሞትን ጥምቀት ተጠምቋል፤በግልጽ አነጋገር ሞቷል” የሚል ነው፡፡

(ክፍል ሶስት ይቀጥላል...)

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በወንጌላዊዊ ጸሎት ይማረን

share
@Mahetotbot
@Mahetotbot
@Mahetotbot
766 viewsedited  06:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-29 13:31:21 ​#ወንጌላዊ_ቅዱስ_ዮሐንስ
(ክፍል አንድ)

ቅዱሱ ሐዋርያ ከዘብዴዎስና ከማርያም ባውፍልያ ተወልዶ: በገሊላ አካባቢ አድጐ: ገና በወጣትነቱ መድኃኔ ዓለምን ተከትሎታል:: ቅዱስ ዮሐንስ ከሐዋርያት ቀድሞ ጌታን ከመከተሉ ባሻገር በምንም ምክንያት ከጐኑ አይጠፋም ነበር:: ስለ ንጽሕናውና በጐ የፍቅር ሕሊናው ሕጻን ሳለ በወንድሞቹ ሐዋርያት ዘንድ ሞገሱ ከፍ ያለ ነው:: ይህ አባት መስከረም አራት ቀን በዚች ዕለት እንደተወለደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታስተምራለች፡፡

ዮሐንስ የሚለው ስም ዮሐናን ከሚለው ቃል የተገኘ ሲኾንትርጓሜውም “ከያሕዌ (ከእግዚአብሔር) የተሰጠ” ማለትእንደኾነ ብዙ ሊቃውንት ይስማማሉ፡፡ ትርጓሜ ወንጌል ግን“ዮሐንስ ማለት ፍስሐ ወሐሴት ማለት ነው” ይላል፡፡ ቅዱስዮሐንስ ብዙ ቅጽል ስሞች አሉት፡፡ ከእነዚኽም መካከል፡-

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት በመግለጡናለጌታችን ባለው ቅንዓት ባሳየውም የኃይል ሥራ “ቦኤኔርጌስ-ወልደ ነጐድጓድ” /ማር.፫፡፲፯/፣

የእግዚአብሔርን አንድነትና ሦስትነት ስለሚናገር “ታዖሎጐስ-ነባቤ መለኰት”፣

ኃላፍያትንና መጻእያትን ስለሚናገር “አቡቀለምሲስ-ረአየኅቡአት- ባለ ራዕይ”፣

እንዲሁም የጌታን ጸዋትወ መከራ አይቶ ፊቱ በኃዘን ተቋጥሮይኖር ስለ ነበር “ቁጹረ ገጽ- ፊቱ በሐዘን የተቋጠረ” ይባላል፡፡

ጌታችን ግርማ-መንግሥቱን ሲገልጥ /ማቴ.፲፯፡፩/፣ የኢያኢሮስንልጅ ሲያነሣ /ማር.፭፡፴፯/፣ በጌቴሴማኒ የአታክልት ቦታ ሲጸልይ/ማቴ.፳፮፡፴፯/፣ ስለ ኢየሩሳሌም መጥፋት ትንቢት ሲናገር/ማር.13፡3/ ዮሐንስ አብሮ ስለ ነበር “የምሥጢር ልጅ”ምይባላል፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ አዕማደ ቤተ ክርስቲያን ብሎ ከሚጠራቸው ሐዋርያት አንዱ ዮሐንስ ነው /ገላ.፪፡፱/፡፡

ከሌሎቹ ደቀ መዛሙርት በተለየ አኳኋንም ጌታን ይወደው ስለነበር ሁሌ ከእቅፍ አይለይም ነበር፡፡ በዚህም “የጌታ ወዳጅ-ፍቁረ እግዚእ” ተብሏል /ዮሐ.፲፫፡፳፫/፡፡

ከነዚህ በተጨማሪ ወንጌላዊው፣ ሐዋርያው፣ ድንግል፣ ዘንሥር፣ዘረፈቀ ውስተ ህፅኑ ለኢየሱስ፣ ካልእ ረድእ፣ ባሕረ ጥበባት፣አበ ልሳናት… እየተባለም ይጠራል፡፡

የቅዱስ ዮሐንስ አባቱ ዘብዴዎስ የሚባል የሲዶና ሀገር ገሊላዊ ሲሆን ዓሣ አጥማጅ ነበር፡፡ እናቱም ማርያም ባውፍልያ እንደምትባልና ከ፴፮ቱ ቅዱሳት አንስት አንዷ መኾኗን የቤተ ክርስቲያናችንትውፊት ያስረዳል /ማቴ.፳፰፡፩/፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በወንጌላዊዊ ዮሐንስ ፀሎት ይማረን

(ክፍል ሁለት ይቀጥላል...)

share
@Mahetotbot
@Mahetotbot
@Mahetotbot
695 viewsedited  10:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-29 13:21:33 ስለ ወንጌላዊዊወና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ማንነት ይምታታባችኃል!...

በሚገባ ስለ ሁለቱም ቅዱሳን ማንነት በክፍል እናቀርብላችኋለን ጠብቁን
608 viewsedited  10:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-27 18:19:36 ​​እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዓል በሠላም አደረሳችሁ!

ታህሳስ 19 ቀን በዚህ ቀን ሰለስቱ ደቂቅ "የምናመልከው አምላካችን ከሚነደው ከእሳቱ እቶኑ ሊያድነን ይችላል" ያሉበት ዕለትና ቅዱስ ገብርኤል ከእሣት ያዳቸው ዕለት መታሰቢያ በዓል ነው።

ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን አባቶቻችን እንዳስተማሩን ነገሩ እንዲህ ነው። ዘመኑ ጣኦት የሚመለክበት ንጉስ ናቡከደነፆር የእግዚአብሔር ሰዎች የቅዱስ ገብርኤል ወዳጆች የነበሩት ወጣቶች ሥም አይጣላልናንያ (ሲድራቅ) ፤ አዛርያ (ሚሣቅ) ፤ ሚሣኤል (አብድናጎ) ነበሩ። ት/ዳንኤል 3፡1-30 ታሪኩ እንደሚግረን ንጉስ የጣኦት ምስል አሰራ በገሊላ አውራጃ ያለውን ሕዝብ ጠርቶ ለጣኦቴ ያልሰገደ ወደ እሣት ውስጥ ብሎ አወጀ።

በዚህ መካከል ሰልስቱ ደቂቅ ነበሩ። የንጉስ ትህዛዝ ነውና ሕዝቡ ሁሉ ለጣኦቱ ሲንበረከክ እነርሱ ግን ቆመው ያዩ ነበር። የእግዚአብሔር የሆነ ሰው ምንም ነገር አያስፈራውምና ናቡከደነፆር እርሱ ላስቆመው ጣኦት አለመስገዳቸውን ሲሰማ ተናደደ ፤ ተበሳጨም እሳቱን 7 እጥፍ እንዲነድ አስደረገ ሦስቱንም አስሮ እሣቱን እያሳየ "ከመቃጠል ወይስ ለእኔ ጣኦት መስገድ የቱ ይሻል?" ባላቸው ጊዜ የምናመልከው አምላካችን ከሚነደው ከእሳቱ እቶን ሊያድነን ይችላል ባያድነንም እንኳን አንተ ለመታመልከው ጣኦት አንሰግድም አሉት።

በዚህ ጊዜ ጉልበት ያላቸው ሠዎች ተፈልገው ሦስቱን ወጣቶች አስረው ወደ እሣት ቶን ውስጥ ጣሏቸው አስረው የጣሉቸው ወታደሮች የእሣቱ ወላፈን አቃጠላቸው ሠልስቱ ደቂቅን ግን መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ እሳቱን አበረደላቸው አጠፋላቸው።

በዚህም ጊዜ ንጉስ ናቡከደነፆር እንዲህ በማለት መሰከረ "እኛ አስረን የጣልናቸው ሦስት ነበሩ አሁን ግን አራተኛው ሰው በእሳቱ ሲመላለስ ይታየኛል እንዲያውም የአማልክትን ልጆች ይመስላል " አለ። የእግዚአብሔር የማዳኑ ስራ ሲገለጥ ቅዱስ ገብርኤል ሲታይ አዋጁ ሁሉ ተሻረ ጉልበት ሁሉ ለጣኦት ተብሎ የነበረው "ጉልበት ሁሉ ለሰልስቱ ደቂቅ አምላክ ይስገድ ይንበርከክ" ተባለ ይህን ሁሉ ታህሳስ 19 ቀን ሆነ በዚህም ምክንያት በታላቅ ደስታ እናከብረዋለን!

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የመላዕክት የቅዱስ ገብርኤል ጥበቃው ረድኤት በረከቱ አይለየን አሜን!
677 views15:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-24 23:15:05 "ነገ ለአንተ የተሸለ ነው"

ያለህበት ዛሬ ለአንተ እጅግ አሰልቺ ከሆነ ለነገህ ኑር። በዚህ ነገህ ዉስጥ አንተን ለማረጋጋት የእግዚአብሔር እጅ ወደ አንተ መዘርጋቱን ተመልከት፡፡ ይህንን ካደረግህ በዚህ ነገህ ዉስጥ ለችግሮችህ ብዙ መፍትሔዎችን መመልከት ትችላለህ። የአንተ ዛሬ ጨለማ ከሆነ ነገህ በፊትህ የብርሃን መስኮቶችን ይከፈትልሀል ፡፡

ቅዱሳን ነገ ለሚያገኙት የዘለዓለም ህይወት ስለ ኖሩ ተስፋቸዉን ሁሉ በዚህ ነገ ላይ ጥለዉት ነበር። ሳዖል ባሳደደዉ ጊዜ ነብዩ ዳዊት የኖረዉ ለነገዉ ነዉ። ነብዩ ዮናስ በዓሣ አንበሪ ሆድ ዉስጥ ሳለ የኖረዉም ለነገዉ ነዉ። ቅዱስ ዮሴፍ በወኅኒ ሳለ አባቱ ቅዱስ ያዕቆብ ደግሞ በወንድሙ በዔሳዉ በተሳደደ ጊዜ የኖሩት ለነጋቸዉ ነበር፤ ያዕቆብም ከመሰደድ ዮሴፍም ከግዞት ህይወት እንደሚወጡ በእግዚአብሔር ታምነዋልና።

ነገሮች ለአንተ አስቸጋሪ ከሆኑ ለራስህ ነገ መፍትሔ ይገኝላቸዋል ብለህ ንገረዉ። ከዚህም በኋላ ለዚህ ነገህ በፈገግታና በደስታ ኑር!!

(ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሽኖዳ)

@Mahetotbot
@Mahetotbot
@Mahetotbot
653 views20:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-24 13:22:10 "አሁን እየጾምክ ነው? እስቲ ጾምህን በተግባር አሳየኝ? የቱን ሰራህ? ድሃውን ባየህ ጊዜ ምህረትን አሳየው። ጠላትህን ስታየው ታረቀው። ስኬታማ የሆነ ወንድምህን ስታየው አትቅናበት በመንገድ የምትሔድ ሴትን ስታይ ዝም በለህ እለፋት። በአጠቃላይ አፍህ ብቻ አይጹም ነገር ግን ዓይንህ፣ እግርህ፣ እጅህ ሁሉም አካልህ ይጹም። እጅህ ከመስረቅና ከስስት ይጹም፣ እግሮችህ ወደ ኃጢአት ከመጓዝ ይከልከሉ፣ አይኖችህም በሌሎች ሰዎች ውበት ላይ ተተክለው ከመዋል ይጹሙ።

አሁን ስጋ እየበላህ አይደለም አይደል? በዓይንህም መጥፎ ነገር አትመልከት፤ መስማትንም ጹም። የፈውስ ጾም ክፉን አለመስማት የሌሎችንም ስም አለማጥፋት ነው። አንደበትም ከክፉና ከአጸያፊ ንግግር ይጹም። የዶሮና የአሳ ስጋ ከመብላት እንከለከላለን ነገር ግን የወንድማችንን ስጋ ስናኝክና ስንበላ እንውላለን። የወንድሙን ስጋ የሚበላ ደግሞ የተረገመና አሳች ነው። ቅዱስ ጳውሎስ “ነገር ግን እርስ በርሳችሁ ብትነካከሱና ብትበላሉ እርስ በርሳችሁ እንዳትጠፋፉ ተጠንቀቁ” እንዳለን። ገላ.5:15

ሆዳችንን ከምግብ ብቻ ባዶ ማድረግ አይደለም። ነገር ግን ሁለንተና ሕይወታችንን ራሳችንንም የምንቆጣጠር እኛ ወደ መንፈሳዊ ነገሮች የምንመራ መሆን አለብን።"

(የቅዱስ ዮሐንስ በረከቱ ይደርብን ውርስ ትርጉም #መምህር_ንዋይ_ካሳሁን) 
          #ሼር
╭══•:|★✧ ✧★|: ══╮
    @Mahetotbot
@Mahetotbot

╰══•:|★✧ ✧★|:  ══╯
680 views10:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ