Get Mystery Box with random crypto!

አሚነ ፅድቅ✨

የቴሌግራም ቻናል አርማ lesanegeez — አሚነ ፅድቅ✨
የቴሌግራም ቻናል አርማ lesanegeez — አሚነ ፅድቅ✨
የሰርጥ አድራሻ: @lesanegeez
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 138
የሰርጥ መግለጫ

የእውነት እምነት ። group :- @lesanegeez2

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-04-19 13:54:38
ሰሙነ ሕማማት

@Eftah_bemaleda
38 views10:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-05 16:52:25
መጋቢት ፳፯ በዚህች ዕለት የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዓለም ድኅነት በሥጋ ተሰቀለ! "ሊቃነ መላዕክት በመፍራትና በመንቀጥቀጥ ከፊቱ የሚቆሙለትን በአደባባይ አቆሙት፤ ኃጢአትን ይቅር የሚለውን ኃጥእ አሉት፤በመኳንንት በሚፈርደው በርሱ ፈረዱበት!"

Join - @Eftah_bemaleda
41 views13:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-03 16:09:51 ማን ያምናል አሁን የእኛን መዳን
በአለም እርኩሰት ለሚያውቀን
እንዲሁ ነጻ ናችሁ ያልከን
ተባረክ ፈቅደህ የባረከን
ኑሮአችን ነበር የጨለማ
ምንቀኝ የአልምን ዜማ
ሳንጠፋ ሳንገባ ከጥልቁ
ተማርን ታይቶልን ሰንደቁ

Join - @Eftah_bemaleda
28 views13:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-19 19:19:51 “…እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ እናንተ ታለቅሳላችሁ ሙሾም ታወጣላችሁ፥ ዓለም ግን ደስ ይለዋል፤ እናንተም ታዝናላችሁ፥ ነገር ግን ኀዘናችሁ ወደ ደስታ ይለወጣል። ሴት በምትወልድበት ጊዜ ወራትዋ ስለ ደረሰ ታዝናለች፤ ነገር ግን ሕፃን ከወለደች በኋላ፥ ሰው በዓለም ተወልዶአልና ስለ ደስታዋ መከራዋን ኋላ አታስበውም። እንግዲህ እናንተ ደግሞ አሁን ታዝናላችሁ፤ ነገር ግን እንደ ገና አያችኋለሁ ልባችሁም ደስ ይለዋል፥ ደስታችሁንም የሚወስድባችሁ የለም።”
ዮሐ 16፥ 20-23

@Eftah_bemaleda
33 views16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-19 11:17:10 "አባታችን ሆይ እንዴት ትላለህ?"

→እንደ ልጅ ካልኖርህ እንዴት "አባት" ትለዋለህ?

→ሌላውን ጠልተህ ራስ ወዳድ ከሆንክ እንዴት አባት "አችን" ብለህ በአንድነት ትጠራዋለህ?

→ምድራዊ ነገር ብቻ እያሰብህ እንዴት "በሰማያት የምትኖር" ትለዋለህ?

→ልብህ ከእርሱ ርቆ በአንደበትህ ብቻ እየጠራኸው "ስምህ ይቀደስ" እንዴት ትለዋለህ?

→ሥጋዊና መንፈሳዊውን እየቀላቀልህ "መንግሥትህ ትምጣ" ለምን ትለዋለህ?

→መከራን በጸጋ የማትቀበል ከሆነ "ፈቃድህ ይሁን" ለምን ትላለህ?

→ለራስህ ሆድ እንጂ ለተራቡት ግድ የማይሰጥህ ከሆነ ለምን "እንጀራችንን ሥጠን" ትላለህ?

→በወንድምህ ላይ ቂም ይዘህ "እኛም የበደሉልን ይቅር እንደምንል" እንዴት ትላለህ?

→የኃጢአትን አጋጣሚዎች ሳትሸሽ "ወደ ፈተና አታግባን" እንዴት ትላለህ?

→ክፉን ለመቃወም አንዳች ሳታደርግ "ከክፉ አድነን" እንዴት ትላለህ?

→ጸሎቱን ከልብህ ሳትሰማውስ እንዴት አሜን ትላለህ?

( የኤፍራጥስ ወንዝ-ገጽ ፹፮)
44 views08:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-08 15:22:12
«ጾም እስከ ስንት ሰዓት ነው?»

የቅድስቲቱ ቤተክርስቲያን ሥርዓቱ በልኬት እና በምክንያት የታጀበ ነው። ጾምን ስንመለከት አብዛኞቻችን በተለምዶ ሰዓት ሳንጠብቅ (እስከ 3፣ 6፣ 7፣ 9፣ 11 ሰዓታት እያልን) እንጾማለን እንጂ የአዋጅ አጽዋማት የተወሰነ የተገደበ ሰዓት አላቸው።

ፍትሐ ነገሥታችን “ሕማማት እስከ 12 ሰዓት ይጹሟቸው፥ ሌሎቹን አጽዋማት በዓለ ልደት እና ጥምቀት ረቡዕ እና ዐርብ የሚውሉባቸው ካልሆኑ በቀር እስከ 9 ሰዓት ይጹሙ” (ፍት.ነገ አን 15፥565-566) ብሏል።

የአጽዋማትን ዝርዝር ካስቀመጠ በኋላም በዚሁ አንቀጽ ቁጥር 572 ላይ ደግሞ “በእነዚህ በታዘዙት ጾሞች ከቀኑ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ ይጹሙ፣ ... ከዚህ አብልጦ የጾመ ግን ዋጋው ይበዛለታል፣ ከጥሉላት ምግቦች መታቀብ ካልሆነ በቀር እሑድና ቅዳሜ ግን አይጹሙ” ብሎ ወስኗል።

ዐቢይ ጾም ሁዳዴ፣ ጾመ ዐርብዓ ግን ይለያል። “በዐቢይ ጾም መጀመሪያ ሱባኤ ፀሐይ እስኪገባ ይጹሙ፣ ሌሎቹን ሳምንታት እስከ 11 ሰዓት ይጹሙ፥ በሰሙነ ሕማማት ግን ኮከብ እስኪወጣ ይጹሙ” ብለዋል። (ፍት.ነገ.አን 15፥595)።

ፍትሐ ነገሥት ቁጥር 578 ላይ ደግሞ “(የሰሙነ ሕማማትን) ዓርብንና ቅዳሜን ግን ሁለቱንም በአንድነት ይጹሟቸው፣ የሚችል እስከ ሌሊት ዶሮ ጩኸት ድረስ ምንም ምን አይቅመስባቸው፣ ሁለቱን በአንድነት መጾም የማይቻለው ግን ቅዳሜን ይጹም” ተብሎ ህግ ተሠርቷል።

https://t.me/yeemariyaam21
41 views12:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-06 19:18:54 ✞ መነኮሳት ስለ ጾም( ዐቢይ ጾም)✞
---------------------------------------
"መስቀል በራሱ ያለ እውነታ መገለጫ ነበር፣ ጌታችን አስቀድሞ አለም ሳይሰቅለው ራሱን ስለ ዓለም ሰቅሎ ነበር፡፡...በአብይ ጾም ራሳችንን ለምሴተ ሐሙስ(ጌታ እራት) እናዘጋጃለን፡፡ ለሁለት ተመሳሳይ ነገሮች ራሳችንን እናዘጋጃለን፡፡ ራሳቸውን መስዋዕት የማያደርጉ እንዴት ራሱን መስዋዕት ላደረገው የተገባ ይሆናሉ? የተሰዋውን የጌታ ስጋ እየበላን ነገር ግን ራሳችንን መስዋዕት የማናደርግ ከሆነ እንዴት ከጌታ ጋር ተዋሃድን ማለት እንችላለን? ምስጢራዊው ምሴተ ሐሙስ የመስዋዕትነትን ሕይወት በፈቃድ የመቀበል እና መከራዎችን እስከሞት ድረስ በግልጽ መቀበያ ነው፡፡"

____ አባ ማታ ምስኪኑ(Fr. Matta the Poor)

@Efath_bemaleda
31 views16:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-04 17:20:47
በፊት ስማቸው አባ ዘሊባኖስ ፈንታ የሚባሉት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ፣ በጎንደር ክፍለ ሀገር በደብረ ታቦር አውራጃ በአለታ ወረዳ አረጊት ኪዳነ ምሕረት በተባለችው ገዳም ሰበካ፣ ልዩ ስሙ ማር ምድር በ1930 ዓ.ም.፣ ከብላታ ፈንታ ተሰማና ከወ/ሮ ለምለም ገሰሰ ተወለዱ፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ፣ 4ኛ ፓትርያርክ ኾነው የተሾሙት፣ ነሐሴ 29 ቀን 1980 ዓ.ም. ሲኾን፣ በፖሊቲካዊ ግፊትና ጫና መንበራቸውን ለቀው ከሀገር ከመውጣታቸው በፊት እስከ ነሐሴ 28 ቀን 1983 ዓ.ም. ድረስ ለቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ አመራር ሲሰጡ ቆይተዋል፡፡ ከ26 ዓመታት ስደት በኋላ፣ ሐምሌ 25 ቀን 2010 ዓ.ም.፣ በስሙ በተሠየሙበት በሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ ክብረ በዓል ወደ ቅድስት ሀገራቸው ኢትዮጵያ መመለሳቸውን፣ ይታወቃል፡፡ ብፁዕ አቡነ መርቆሬዎስ፣ የበላዮቻቸውን መካሪ፣ የበታቾቻቸውን አክባሪ፣ በሥራ ታታሪ፣ መንፈሳዊ አባትነታቸውና ትሑት ሰብእናቸው አርኣያነት ያለው ቁጥብ አባት ናቸው፡፡ ምንጭ https://bit.ly/3pBMbKC
40 views14:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-04 17:20:17
አሳዛኝ ዜና

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከዚህ ዓለም ድካም ዐረፉ።

ሃሌ ሉያ ግሩማን መላእክት ሱራፌል ወኪሩቤል እለ አክናፊሆሙ ነበልባል ወረዱ ዮም ይተቀበሉከ በብሒል አማን መርቆሬዮስ

#በዕለተ_መርቆሬዎስ_መርቆሬዎስ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከዚህ ዓለም ድካም ዐረፉ።

አቡነ መርቆርዮስ ከብፁዓን ጳጳሳት ጋር ከሀያ ስድስት ዓመት ስደት በኃላ ሐምሌ 25/2010 ዓ.ም አስራ ዘጠኝ ሊቃነ ጳጳሳት እና አገልጋይ ካህናት ጋር ወደ ሀገር ቤት ተመልሰዋል።

#ከስደት_ወደ_ሃገራቸው_የተመለሱትም_ያረፉትም_በዕለተ_መርቆሬዎስ_ነው

በረከታቸው አትለየን።


•✥• @Z_TEWODROS •✥•
29 views14:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-02 08:52:09
“እንግዲህ ሊመጣ ካለው ከዚህ ሁሉ ለማምለጥ፥ በሰው ልጅም ፊት ለመቆም እንድትችሉ ስትጸልዩ ሁል ጊዜ ትጉ።”
— ሉቃስ 21፥36

@Eftah_bemaleda
34 views05:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ