Get Mystery Box with random crypto!

'አባታችን ሆይ እንዴት ትላለህ?' →እንደ ልጅ ካልኖርህ እንዴት 'አባት' ትለዋለህ? →ሌላውን | አሚነ ፅድቅ✨

"አባታችን ሆይ እንዴት ትላለህ?"

→እንደ ልጅ ካልኖርህ እንዴት "አባት" ትለዋለህ?

→ሌላውን ጠልተህ ራስ ወዳድ ከሆንክ እንዴት አባት "አችን" ብለህ በአንድነት ትጠራዋለህ?

→ምድራዊ ነገር ብቻ እያሰብህ እንዴት "በሰማያት የምትኖር" ትለዋለህ?

→ልብህ ከእርሱ ርቆ በአንደበትህ ብቻ እየጠራኸው "ስምህ ይቀደስ" እንዴት ትለዋለህ?

→ሥጋዊና መንፈሳዊውን እየቀላቀልህ "መንግሥትህ ትምጣ" ለምን ትለዋለህ?

→መከራን በጸጋ የማትቀበል ከሆነ "ፈቃድህ ይሁን" ለምን ትላለህ?

→ለራስህ ሆድ እንጂ ለተራቡት ግድ የማይሰጥህ ከሆነ ለምን "እንጀራችንን ሥጠን" ትላለህ?

→በወንድምህ ላይ ቂም ይዘህ "እኛም የበደሉልን ይቅር እንደምንል" እንዴት ትላለህ?

→የኃጢአትን አጋጣሚዎች ሳትሸሽ "ወደ ፈተና አታግባን" እንዴት ትላለህ?

→ክፉን ለመቃወም አንዳች ሳታደርግ "ከክፉ አድነን" እንዴት ትላለህ?

→ጸሎቱን ከልብህ ሳትሰማውስ እንዴት አሜን ትላለህ?

( የኤፍራጥስ ወንዝ-ገጽ ፹፮)