2022-08-17 23:22:55
ብቸኝነቴን ...... መልሺልኝ
ክፍል ሀያ ስድስት (26)
.
.
በአንድ ሰው በሞላው መጠጥ ቤት ሰላምና ኬብሮን ቁጭ ብለው ይጨቃጨቃሉ
እሷ መጠጥ እንዲጠጣ ት ፈልጋለች እሱ እንደማይጠጣ ይነግራታል።
" አንተ ግንብ እራስ ዝም ብለህ ጠጣ አንተ እኮ አይደለህም የምትከፍለው እኔ
ነኝ እሺ " አለችው ሰላም።
" ክፈልስ ብትይኝ ከየት አምጥቼ እከፍላለው ቆዳዬ ተገሽልጦ ብር አይሆን
....ትሰሚያለሽ እኔ መጠጥ አልወድም ከጠጣው እንኳን ጤነኛ አልሆንም
እራሴንም የማረገውንም አላውቅም ስለዚህ መጠጥና እኔ አይጥና ድመት ነን
እሺ" አላት የማስንጠቀቅ አይነት ንግግር ተናግረ።
" ዝም ብለህ ጠጣ ከማን ጋር ያለህ መሰለህ እኔ እኮ ነኝ ... እኔ ሰላም ....
ሰላም ሽቡሩ እሺ " አለች በመተማመን።
" ልክ ነሽ ሰላም ሽብሩ ነሽ ... እኔ መቼ አልጋነሽ ሽብሩ ነሽ አልኩሽ ? " አላት
ፈገግ ብሎ እሷ ተናዳ።
" አ .... አ .. አልጋነሽ .. ስትል አልገባኝም?" መረር ባለ ቁጣ
" እንዴ ምን አስቆጣሽ ?..... አልጋነሽ ስም እኮ ነው " አላት
" አ አ ስም እማ ስም ነው ..... ያልገባኝ አሽሙሩ ነው ... ልትል የፈለከው የአልጋ
ላይ ሽብርተኛ ነው አይደል" አለችው ኬብሮን የሆነ ነገር እንደገማው ፈገግ አለና
።
" አሀ ሀሀሀ .... አልጋነሽ ሽብሩ አይገርምሽም እኔ ተናግሬው አንቺ ሲገባሽ እኔን
ገባኝ ..... ምን አለበት ....... አይይደል የሚባለው " አለና ከት ብሎ ሳቀ ።
" እንደውም ልክነህ ..... አልጋ ላይ ሽብርተኛ ነኝ ተስማማን አሁን ....... ትንሽ
ጠጥተህ ትሄድና ይሄ ዝናብ የመታው ፍየል ፍየል የሚሸተውን ጠረንህን
ታጥበሀው ትመጣለህ " አለች ሰላም በመጠየፍ። ኬብሮን ዝም ብሎ በፈገግታ
አየትና።
" እኔ የምልሽ ሶል ..... ፍየል ዝናብ ሲመታው መጥፎ ጠረን እንዳለው እንዴት
አወቅሽ ነው ....... አብረሻቸው አድረሻል ?" አላት ኬቡ የሰላም ፊት በንዴት
ተለዋወጠ ።
በጣም በፍጥነት እጅግ እየበረረ በትላክስ አካባቢውን እየበጠበጠ ቶማስ
እየበረረ በመምጣት የሆስፒታሉን ቅጥር ግቢ በር አቁም እየተባለ ዝም ብሎ
ገባ መኪናውን አግባብ ባለው ቦታ አላቆመውም ። ከመኪናው ዘሎ በመውረድ
ወደ ውስጥ ገባ ፊቱ እና አይኑ ቀልቷል በደንብ እንዳለቀሰ ያስታውቃል ቀጥታ
ወደ ዶክተሩ ቢሮ በመሄድ ሳያንኳኳ ገባ።
" አቤት " አሉት ዶክተሩ በእድሜ ፀና ያሉ ሽበታም ወፍራም።
" ዶክተር ከፎቅ ላይ ወድቃ የመጣችው የቃል ኪዳን ባለቤቷ ነኝ እንዴት ነች
ዶከተር " አለ ቶማስ እያለከለከ።
ዶክተሩ በትህትና እንዲቀመጥ ካደረጉት በኋላ ለደቂቃ እራሱን እንዲያረጋጋና ከዛ
በኋላ ያለውን ነገር እንደሚነግሩት አሁን ግን ስሜቱ የሚረጋጋ ከሆነ ደህና
መሆኗን ነገሩት በእርግጥም ለቶማስ ይሄ ንግግር አረጋጋው።
ወደ እራሱ እንዲመለስ ካደረጉት በኋላ አሁን ያለውን የቃል ኪዳንን ውጤት
ነገሩት። በእርግጥም ቃል ኪዳን አሁን ባለው የህክምና ውጤት ወገቧ ላይ
ዪለው እስፓይናል ኮርድ በመሰበሩ የተነሳ ከዚህ በኋላ መራመድ አይደለም
መቀመጥም የምትችል እንደማይመስላቸው ሙሉ ለሙሉ ያለውን ውጤት
ደግሞ በተጨማሪ ከሚደረግላት ምርመራ እንደሚያሳውቁ ነገሩት። ቶማስ
በየንግግራቸው መሀል እያለቀሰ እንደ አይምሮ በሽተኛ ለሀጭ ንፍጡን
መቆጣጠር ተስኖት እየተዝረከረከ ነበር የሚሰማው በመጨረሻ ከቢሮው
በፍጥነት ወጥቶ ሄደ የት እንደሚሄድ እርግጠኛ ነበር።
" እማ ያ ሳቂታ ተጨዋች የነበረው ሚኪ ለምን ሳቁ ጠፍቶ ጭምተኛ የሆነበትን
ችግር አሁን ደረስኩበት እኮ ፍቅር ፍቅር ይዞት እኮ ነው " አለች ሚጣ ከሆስፒታል
ወጥተው ሰርካለም ከረጅሙ ሶፋ ላይ ጋደም ብላ እነሱ ባለ አንድ አንድ ሶፋ ላይ
ተቀምጠው። ሚኪ ደንግጦ ።
" እረ እንደሱ አይደለም ሚጣ ምን ሆነሽ ነው" አላት እያፈረ።
" ሚኪዬ እኔ ልጅህ እኮ ቅመም እኮ ነኝ የፍቅር ቫይረስ ሲይዝ የህመሙን
ምልክት እኔ አውቀዋለው እንደ አንተ ነው የሚያረገው እሺ " ስትል በሩ ተንኳኳ
ሚጣ ለመክፈት እየሮጠች ሄደች ከፍታ ከአክስቷ ጋር ተመልሳ መጣች ሰርካለም
እንዳየቻት።
" አክስቴ ምነው ከመሸ ከየት ነው ?" አለቻት
" ሄይ አንድ boy frend ቀጥሬ ሲጋበዘኝ አምሽቶ እንደር አላለኝም አይገርምም
በአንደ ቀን 300 ብር አውጥተህ የ3000 ( የሶስት ሺህ ) ብር ስትፈልግ
አይደብርም ብዬው ትቼው መጣኋ ....... " አለችና ሚኪን ተቀምጦ ስታየው
ዳበስ እያረገቺው በፈገግታ "....ዋው ይሄ ቆንጆ እዚህ ነው እንዴ ዛሬ...... ዋው
በጣም ነው የሚያምረው" ስትል ሚጣ አይኗን በቀጥታ ወደ እናቷ ወረወረቺው
ሰርካለም መናደዷን አየች።
" በይ አክስቴ ከእሱ ጋር እንኳን አቁሚ እና ነይ ቁጭ በይ " አለች ያልተናደደች
በመምሰል ።
" እማ እንዴ ምን አናደደሽ ..ምን ችግር አለው " አለቻት ሚጣ
" እረ ተይ አንቺ ልጅ " አለች ሰርካለም በምሬት በዚህ ሰአት የሚካኤሌ ስልክ
ጮሀ ስልኩን ይዞ እንደተለመደው በዱላው እየተመራ ከቤት ሊወጣ ሲል ማክዳ
ጋር ተገናኝተው ሰላም ተባባሉ እና እሷ ስትገባ እሱ ወጣ ግን ስልኩ ተዘግቶ
ስለነበር ዳግም እስኪደወል ጠበቀ። ተደወለ ሰላም ነበረች በምሽት መደወሏ
ገርሞታል አነሳውና ወደ ጆሮው ወሰደው።
" አንተ ብርሀን አልባ ዛሬ ማን ሲያስደስተኝ እንደሚያድር ልንገርህ ኬቡ ነው ....."
አለችና ለኬብሮን ስልኩን ሰጠችው "ሀይ ወዳጄ ወንድሜ ዛሬ አዳሬ ይቅርታ
እዚህ ነው ....." አለው የሚኪ ፊት ወዲያው ተቀያየረ ።
" ያው እንዳታስብ ብዬ ነው የነገርኩሁ እሺ ከፈለክ በኋላ በፎቶ እልክልሀለው
ለማረጋገጥ " አለችው ሚኪ የምን ሳቅ እንደሆነ ያላወቀው ሳቅ ከት ብሎ ሳቀ።
.........
~~ ይቀጥላል ~
@Kooblife
@Kooblife
For any comment
@Ethio96bot
7.1K views20:22