Get Mystery Box with random crypto!

ISLAM IS UNIVERSITY

የቴሌግራም ቻናል አርማ islamisuniverstiy_public_group — ISLAM IS UNIVERSITY I
የቴሌግራም ቻናል አርማ islamisuniverstiy_public_group — ISLAM IS UNIVERSITY
የሰርጥ አድራሻ: @islamisuniverstiy_public_group
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.00K
የሰርጥ መግለጫ

⭐️ሰው የሚገነዘብ አእምሮና የሚያፈቅር ልቦና ባለቤት ነው።እነዚህ ሁለቱ ካልተመጣጠኑ ስብእናው አደጋ ውስጥ ነው።የሚያገናዝበው አዕምሮው፣የሚያፈቅረው ልቡ፣የሚንቀሳቀሰው አካሉናወደ ሰማይ የሚወነጨፈው መንፈሱ በውህደት ካልተንቀሳቀሱ ሰውየው ላይ ችግር አለ ማለት ነው
📨የፍቅር እና የጥላቻ ስሜቱ፣የፍላጎት እናየፍርሃት መንፈሱ በአዕምሮ ብስለት ካልተገራ አስቸጋሪ ነው
አስተያየት👇
T.me/Aisuu_bot

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-03-29 12:23:32 https://www.youtube.com/live/nkLopSTEecI?feature=share
205 views09:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 19:59:01 https://www.youtube.com/live/tCV6CH0APfc?feature=share
273 views16:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 12:46:35 https://www.youtube.com/live/2qycWGGrpeo?feature=share
521 views09:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 16:12:05 https://t.me/arebgendamesjid?livestream=d5fd5d7d6719db3dfd
382 views13:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 20:48:53 https://youtube.com/live/bJhHCAXuq0I?feature=share
392 views17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 15:35:11 https://www.youtube.com/live/3S_3MNJO8RA?feature=share
581 views12:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 12:50:35 በነገራችን ላይ እንደ ወሎየ እያሰብኩም ሊሆን ይችላል....የኔ ሁለት አያቶቼ ክርስቲያን ናቸዉ ..አጎት የአጎት ልጅ ምናምን እንደ ወሎ አንድ ላይ በልተን ጠጥተን አድገናል ከዛ አንፃር እያሰብኩም ሊሆን ይችላል....ግን የኛ ሙስሊም ችግር ዲነል ኢስላምን እንኳን ለሌሎች ሀይማኖት ማዳረስ ይቅርና ለሙስሊሙ ለማስተማር ኡስታዞች ሸይሆች ከወጣት እስከ ትልቅ ሙስሊሙ በዱንያ ቢዚ ሁኗል የዚህ ችግር እንጂ
ሞክሩ እነሱን ኢስላምን በማስተማር ቀላል ነበር የኔ ቤተሰቦች 20% የሚሆኑት መልሰዉ ሰልመዋል
የኛ ችግር እነሱ ቦታ ተቀበሉ እንደዚህ አረጉ እርይ ኡኡኡኡ በቃ አለቀ የጮሀዉ ሁሉ 1% ሲሰራ አይታይም ጥጉን ይይዛል.... የሌሎችን ሀይማኖት ተከታዮችን ኢስላምን ለማስተማር እስከ ጥግ ድረስ ጥረት ሲደረግ አላየሁም...

ማወቅ ያለብን ለሌላ ሀይማኖት ኢስላምን ማስተማር ግዴታ እንዲሰልም አይደለም
ለኢስላም መጥፎ አመለካከት እንዳይኖረዉ ለማድረግ ጭምር መሆን መታሰብ አለበት ኢስላም የሚሰጠዉ አላህ ብቻ ነዉና...ከልምድ አንፃር አንድ ሰዉ ማስለም የፈለገ በጥረት የ5-7 አመት ትግል ያስፈልጋል
ሀይማኖት እኮ እንደ ስም በፍርድ ቤት ሂደህ በአንድ ወይ በሁለት ቀን የምትቀይረዉ ነገር አይደለም
ሀይማኖት መቀየር የህሊና ጦርተን ያለበት..ከቤተሰብ ከዘመድ ከወዳጅ የሚያራርቅ ከባድ ዉሳኔ ነዉ ስለሆነም የአሁን ሙስሊም በአንድ ወይ በሶስት ቀን የሚቀይሩ ስለሚመስለዉ አካሄድ አይችልም..እነሱን ከመወንጀል ከመከታተል ዉጭ እናም ይሄ መታረም አለበት በዚህ ቻናል ብዙ የማቃቸዉ የሌላ ሀይማኖት ተከታዮች ጋር ስለማቅ ስለምግባባ ጭምር ነዉ ፡፡
እናም መጀመሪያ ሁሉም ሙስሊም የኛ ጥርት ያለ ነዉ ማለት አንችልም የኑሮ ዉድነት እየመጣብን ያለዉ በተለይ በብዙ ስግብግብ ሙስሊም ነጋዴዎች መሆኑ አንዘጋ ይሄዉ ዘንድሮ ተምር 3000 ከዛም በላይ ገብቶ በካርቶን የለመድነዉ በኪሎ አፁመዉናል እኮ መታሰብ ያለበት ተምር የሚሸጡት 90% በላይ ሙስሊም ነጋዴዎች መሆኑን አንዘንጋ

እያየነዉ ባለዉ ተጨባጭ ከሌላ ሀይማኖት ሰልመዉ ወደ ኢስላም የገቡ ናቸዉ ለኢስላም እየሰሩ ያሉት...ሙስሊሙ የኢስላምን ፀጋ ስጦታ አላስተነተነዉም ግን የሰለሙ ትክክለኛ መሆኑን አረጋግጠዉ ቆርጠዉ ወደ ኢስላም ስለገቡ ቁርአን ቀርተዉ ሀዲስ ተፍሲር ቀርተዉ ሙስሊም ሁኖ የተወለደን እያስተማሩና ሌሎች ለመስለም ያልታደሉትን ወደ ኢስላም እየጠሩ እያስተማሩ እያሰለሙ እያየን ነዉ እናም አሁን ላይ በጣም ጭፍን ጥላቻ እነሱ ጋር ያለዉ አያስፈልግም ማስተማር እንጂ

እኛም ማወቅ ያለብን ነብዩ ሰዐወ አንድ ሰዉ እናንተን በባህሪ በሁሉ ነገር አይተዉ ለመስለም ጉጉት ካላደረጉ ኢማናችሁ ድክመት አለበት ብለዋል...የኛ ባህሪ ኢስላምን ይጣራል ወይ??



አሁንም በዚህ HIV+ ዙሪያ ገንቢ አስተያየት ካለ እቀበላሁ፡፡ሙሉ በሙሉ ችግሩን መቅረፍ ባንችል አንድ ወይ ሁለትም ቢሆን ትዳር ቢያገኙ ትልቅ ነዉና በተቻለን እንታገል እንረባረብ ...የነገን ማን ያቃል በጣም ከባድ ኬዝ ነዉ እናም  እስኪ HIV+ የሆኑትን ቀረብ ብላችሁ የተወሰነ ለመረዳት ሞክሩ እየሳቁ ብዙ የሚደብቁት ችግር የሙራል የሳይኮ ጉዳት ብቸኝነት ተስፋ መቁረጥ ተሸክመዉ ነዉ የሚዞሩት ወላሂ ብዙዎች ተስፋ የቆረጡ ናቸዉ

ከጎናቸዉ ልንሆን በሀሳብ ልንረዳቸዉ ይገባል ..ብዙዎች ሲወለዱ ከቤተሰብ ነዉ የሚይዛቸዉ ወደዉ ያልተቀበሉት በሽታ ነዉ እናም በሀሳብ ያለንን በመርዳት ትዳር በማፈላለግ ጭምር ከጎናቸዉ እንሁን

አስተያየት ለመስጠት
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot
652 viewsedited  09:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 12:49:49 አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካትሁ
እንዴት ናችሁ
             አሚር ሰይድ

    ከተወሰኑ ቀናቶች በፊት በተፓሰተዉ በHiv positive ያለባቸዉ ችግሮች እና እነሱ ትዳር እርስ በራሳቸዉ ለመገናኘት ከባድ ፈታኝ ችግር ስለሆነ በቻናል ላይ የጤና ባለሙያዎች እና ማንኛዉም ያነበበዉ ሙስሊም የራሱ ሀሳብ ካለዉ እና Hiv positive የሆናችሁ በአስተያየት መስጫ bot እንዲያሳዉቁኝ ሰፋ ያለ ፁሁፍ ፓስቼ ነበር
ከሞላ ጎደል ከአገሪቱ ወቅታዊ ጉዳይ አንፃር Data ስለተዘጋ በpisphon ብቻ ስለምንጠቀም በpisphon የማይጠቀምም ስላለ በተጨማሪም የተፓሰተዉ ረመዳን ሊገባ 10 ቀን ሲቀረዉ ስለሆነ በዚህ ቀናቶች ደግሞ አንዳንድ ወገኖች ረመዳንን ብቻ ሚዲያ አልጠቀምም ብለዉ የሚቶብቱ ስላሉ አላህ በዛዉ ከሚዲያ የሚጠፉ ያድርጋቸዉና እንደታሰበዉ ፁሁፉ ለብዙ ሰዉ ተደራሽ ባይሆንም ግን ከታሰበዉ እቅድ 55% ግብ ላይ ዉሏል

☞በአስተያየት ላይ ሰዉ በጣም ሰፊ ልዩነት ያለዉ እንደዉ ስለ Hiv አያቁም ወይ ያስብላል የሚሰጡት comment ደባሪ የሰጡ አሉ ምን ይባላል ጀሊሉ እዉቀትን ጨምርላቸዉ ከማለት ዉጭ.. ስድብም የሰደቡኝ ነበሩ እነሱ የማይጠቅም የማይጎዱ ስለሆኑ
ከቻናል ተጭረዋል መቀመጣቸዉ ቻናል ከማሞቅ ዉጭ ጥቅም የላቸዉም

☞ የተወሰኑ ወደ 5 comment ደግሞ Hiv ይለቃል የሚሉም አየሁ ይሄን እያዩ አንዳንድ ከተሞች ሰፈሮች የፈጣሪ ቁጣ እንጂ በሽታ አይደለም ብለዉ ራሳቸዉን ያሳመኑም አሉ ....
የለቀቀዉ ሰዉ ብሎ የነገሩኝ ግራ ገብቶኝ የጤና ባለሙያ ስጠይቅ አይለቅም ግን በሽታዉ ስለሚዳከም ስትመረመር ላያሳይ ይችላል ብለዉኛል እናም ይለቃል ብላችሁ ባይዳከሙ ባይ ነኝ፡፡ ግን አንድ አዲስ አበባ የተፈጠረ የማቃት ልጅ የነገረችኝ ገርሞኛል ግን መንገሩ ጥሩ ስለማይሆን በደንብ ማሰቡ ይሻላል

☞ በቻናል Hiv positive ራሳቸዉን ይፋ ያደረጉት ሴቶች ብቻ ሲሆኑ ..ግን ተማሪዎችም ስራ ላይ ያሉም የወለዱም አሉ ግን ፈጣሪ ይድረስላቸዉ 95% ተስፋ የቆረጡ ሁነዉ አግኝቻቸዋለሁ :: የተወሰኑትም ተስፋ ቆርጠዉ መድሀኒት እስከማቆም የደረሱ ነበሩ እነሱን በሶይኮ ማከምና እነሱን የስነልቦና ምክርን በመስጠት መድሀኒት በማስጀመርና ለወደፊት ህልም ሰንቀዉ ተማሪዎችም ተምረዉ እንደነሱ hiv+ የሆኑትን መርዳት እንዳለባቸዉ የተለያዩ ምክሮች ልምዶች በመስጠት እነሱን በፊት ካሉበት ዲፕሬሽን በማዉጣትና መድሀኒት ያቋረጡትን ደግሞ እንዲጀምሩ በማድረግ በቅርብ በመከታል 97% ተሳክቷል አልሀምዱሊላህ ለወደፊትም ከጎናቸዉ ሁኜ እከታተላቸዋለሁ

☞አንድ እንኳ ወንድ ማግኘት አልቻልንም..ይሄ ማለት
ብዙዎች ደብቀዋል ወይም ከኑሮ ዉድነት አንፃር አሁን ላይ ትዳር ለመመስረት ስለከበደ ሊሆንም ይችላል እናም ለማገናኘት የተለባለዉ ወንድ ማግኘት አልቻልንም....
የHiv+ group አለ እዛ ወደ 20 ወንዶች ነበሩ ግን ከወሬ የዘለለ ቁም ነገር የላቸዉም...እነዚህን አግቡ ማለት ስስ የሆነ የሴት ልብን መጉዳት ነዉ፡፡ ለምን ብዙ ሴቶች በዚህ ኬዝ ያሉ እዉነት ስለሚመስላቸዉ የትዳር ፕሮሰስ ተጀምሮ ቢያፈገፍጉ የሴቱ ልብ ይጎዳል ከዚህ አንፃር ለማግባት የነየተን እንጂ እኔም የዚህ ኬዝ ካላት ጋር ወሬ ብቻ የሚወራን ማገናኘቱ ለሴቶቹ ጉዳት መጨመር እንጂ ጥቅም ስላልታየ ትተነዋል

☞ አዲስ አበባ ላይ መድሀኒቱን የሚሰጠዉ የጤና ባለሙያዉን ለማማከር በየጊዜዉ ይቀያየራሉ ብለዉኛል ይሄ ትንሽ ለማማከር ይከብዳል ግን ከአዲስ አበባ ዉጭ ያሉ ከተሞች መድሀኒቱን የሚሰጠዉ  አንድ የጤና ባለሙያ የተወሰኑ ወራቶች እስከ አመታትም ስለሚቆይ ብታማክሩ አሪፍ ነዉ መፍትሄ ግብ ላይ መድረስ ግዴታ ስበብ ማድረስ ስለሚያስፈልግ፡፡ Hiv+ ስለትዳር ሲታሰብ የመጀመሪያ ዉሳኔ መሆን ያለባቸዉ የጤና ባለሙያ ማማከር መሆኑን አንዘጋ...ግን የወሰኑ ሴቶች የጤና ባለሙያ ስናማክር የምናገኘዉ እድሜዉ ከ40 በላይ የሆነ ነዉ ያሉኝ አሉ በዚህ በእድሜ የተነሳ እንዳላገቡ ነግረዉኛል፡፡ይሄ በኔ የሚወሰን አይደለም ትዳር የፍላጎት ምርጫ ስለሆነ ገብቶ ከመጨቃጨቅ ከመናናቅ የሚወዱትን መስፈርታቸዉን የሚያሟሉ  ማግባት የራሳቸዉ ምርጫ ስለሆነ በእድሜ የገፋ አግቡ ብየ ማስገደድ አልችልም....
ፈጣሪ ያሰባችሁትን ያሳካለችሁ ከማለት ዉጭ


☞ አዲስ አበባ AHF Addis clinic /kolfe clinic የሚባል ለም ሆቴል አካባቢ አለ HIV positive ለሆኑ ሰዎች ትዳር ያገናኛሉ ብለዉኛል ይሄ የኮሚሽን ግን ይቀበላሉ ብለዉኛል እንደ አማራጭ ይያዛል


☞ለታዋቂ ሰዎች ማድረስ በሚለዉ ደግሞ ለተለያዩ ፀሀፊዎች ለተለያዩ ኡስታዞች የትላልቅ ሚዲያ ባለሙያዎች በማድረስ ከአንድ በኔ ሀሳብ በምትሄደዉ የዲን እህቴ ጋር በመናበብ 80% ያሳወቀን በዚህ ዙሪያ የቻሉትን እንዲሰሩ ታገለን ነበር ያዉ የዘንድሮ ሙስሊም ከኢንሻ አላህ ዉጭ የሚሰራ የለም ኢንሻ አላህ ብለዉ ዘግተዉናል
የአሁን ብዙዉ ሙስሊም ኢንሻ አላህ ብሎ ወደ ግራ የሚሄድ ነዉ ምንም ማድረግ አልችልም በተቻለን አላህን ይዘን መታገል ብቻ ..አሁን ላይ ከዳኢዎች ከኡስታዞች ጥሩ ምላሽ መጠበቅ ከብዷል አላህ ለዚህ የዋህ ሙስሊም ኡማ ይድረስልን

☞ አንድ ብቻ ሙስሊም ወንድም የጤና ባለሙያ ሙስሊሞችን Hiv+ የሚያገናኝ አለ ግን አሁን ረመዳን ነዉ ከረመዳን ቡሀላ ብሎኛል ፡፡ ግን ከአገናኘሁ ቡሀላ እየተጣሉ እየተፋቱ ተቸግሪያለሁ ለምን ይሁን ይሁን ችግር የለም በሚል ከተጋቡ ቡሀላ ብዙዉ ሳይግባቡ ስለሚጋቡ ሲግባቡ ችግር እየመጣ በጣም ተቸግሪያለሁ አለኝ...እናም ከረመዳን ቡሀላ ብሎኛል እናም እዚህ ያላችሁ
Hiv + የሆናችሁ የቻናል ቤተሰቦች ፈርታችሁ ያልተናገራችሁ በዚህ bot አሳዉቂኝ የእሱን ስልክ ቁጥር እሰጣችሆለሁ በዚህ bot ያሳዉቁኝ

T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot

☞  የተቸገሩን ኸይር መስራት የፈለገ Hiv+ ሆነ ከዛ ዉጭ ያሉ መርዳት የሚፈልግ ካለ እኔ ችግረኞችን በስልክ ወይ በtg acount አገናኛችሆለሁ ራሳችሁ መርዳት የምችሉበትን አመቻችላችሆለሁ ...እኔ ሚዲያ ላይ የማቃቸዉ በጣም ብዙ የተቸገሩ አሉ በራሴ አቅም የቻልኩትን ባደርግም ግን ብዙ ከአንድ ሰዉ አቅም በላይ ነዉ እናም ኸይር መስራት የሚፈልግ የተቸገረዉን እኔ ላገናኛችሁ ችግሩን ሁኔታ ራሱ ያስረዳችሆል የምረዱትን ቀጥታ እነሱ ጋር ማገናኘት እችላለሁ የመርዳት ንያዉ ያለዉ በዚህ bot ያሳዉቀኝ

T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot  T.me/Aisuu_bot

☞ደግሞ በተሻለ መልኩ የክርስቲያን ሀይማኖት የሰጡት ገንቢ አስተያየት ነበር እነሱን ሳላደንቅ አላልፍም...አሁን ላይ እነሱ ይሰራሉ ለሀይማኖታቸዉ ደስ ይላሉ እኛ ግን እነሱ ሰሩ ቦታ ተቀበሉ ብሎ ጫጫታ ነዉ ለእምነታቸዉ የመስራት ፈጣሪ ብለዉ ከያዙት ግዴታ ስለተሰጣቸዉ ይሰራሉ ሰሩ ብሎ እርይ አያዋጣም ይልቅ እኛ ኢንሻ አላህ እያሉ ከመሹለክ እንደ እነሱ ተናቦ መስራት ያዋጣል፡፡ እናም ከልምድ አንፃር ለሰጣችሁኝ አስተያየት ጥቆማ ከልብ አመሰግናለሁ፡፡
628 views09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 12:48:19
ሴትነት ምንድን ነዉ?

ኡስታዝ ኑሩ ቱርኪ
1.1K views09:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-20 23:50:13

55 views20:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ