2022-07-04 21:44:07
የሰው ልጅ፣የሰውን ልጅ በዘሩ ምክንያት መንቅፍም ሆነ መደገፍ ከጀመረ፣ ከእዚያ ሰው እውነትንና ፍትህን ለማግኘት አትሞክር!
"ሃይማኖት አለኝ"፣እያለ የፈጣሪውን ስም ቢጠራ አትስማው! ምክንያቱም በፈጣሪው ፈጣሪነት ከልብ የሚያምን ቢሆን በዘሩ የወደደውም ሆነ የጠላው ሰው የተፈጠረው በፈጣሪው ፍቃድ ነውና ፣ያንን አይቃወምም ነበር።
ተምሬያለሁ ቢልም፣ጭንቅላቱን ደፍኖ ጆሮው ላይ ባይንጠለጠል ሰው በዘሩና በቋንቋው ፣ሳይሆን፣በአካባቢው፣በመልክዐምድሩ፣በባህሉና በትምህርት ደረጃው እንደሚለያይ ማሰብ አይገደውም ነበር። ለዚህ ነው ማርቲን ሉተር ኪንግ "The call for intellegence is call for openmindedeness,sound judgement,,and love truth."ያለው።
ከምክንያት ይልቅ፣ለዘር ቡድን፣ከትክክለኛ ፍርድ ይልቅ ለደባ እየተገዛን፣እውነትን ባፍጢሟ እየደፋን ለዕውቀትና ለእውነት ወዳጅና ዘመድ ልንሆን አንችልም፣ሕሊናችንም በእውነት ቁጣ ተዠልጦ ባለመስማት የሞተና የደነዘዘ ነው።
ሌባውን አጎትህን ትተህ፣ጨዋውን ባዕድ የምትከስስ ከሆነ ያንተ ትምህርት የገሀነም ፍም ነው።ሌሎችን ብቻ ሳይሆን አንተን ያቃጥላል።
ሰው እንዲታረድ መመሪያ እየሰጡ ክርስቶስ ያድናል ብሎ መናገር፣ስለታቦታት መደስኮር ፣ስለቁርዐን መተረክ ዐይን አውጣነት ነው።
ወይ ሃይማኖቱን አሊያም ዘረኝነትን መተው ነው።
እንደ መጽሐፍ ቅዱሱ ሰው ኢያሱ " እኔና ቤቴ እግዚአብሔርን እናመልካለን፣እናንተ የምታመልኩት ምረጡ!" የሚል ቄስ፣ዲያቆን፣ፓስተር፣ሼክ እንዴት በሀገር ይጠፋል?
ገዳይነት የሰይጣን አሽከርነት ነው፣ዘረኝነት ከእግዚአብሔር ጋር ጥል ነው።ታዲያ በአንድ ጊዜ የሰይጣን አሽከርና የእግዚአብሔር አገልጋይ መሆን ይቻላል እንዴ??
እውነትም ፕሮፌሰር መስፍን እንዳሉት ከሽፈናል።ሺህ ጊዜ ከሽፈናል!!
*
ደረጀ በላይነህ
2.0K views18:44