2022-08-27 15:56:13
ዩኑስ ቢን አብድ አል- ዓዕላ የተባለ የኢማሙ ሻፊዒ ተማሪ ነበር ። አንድ ቀን ኢማም ሙሀመድ ቢን ኢድሪስ አሻፊዒ መስጂድ ውስጥ እያስተማሩ እያሉ ከዩኑስ ጋር በሆነች መስአላ ( ጉዳይ) ይለያያሉ።
ከዛም ዩኑስ ተናዶ ትምህርቱን አቋርጦ ወደ ቤቱ ይመለሳል። ከመሸ በኃላ የቤቱ በር ሲንኳኳ ይሰማና
" ማን ነው ??? " ብሎ ሲጠይቅ
የሚያንኳኳውም ሰው ፦ " ሙሀመድ ቢን ኢድሪስ ነኝ " ይላል ።
በዚህ ጊዜ ዩኑስም " ከኢማሙ ሻፊኢ በስተቀር ሙሀመድ ቢን ኢድሪስ በተባለ ሰው ሁላ አሰብኩ " ይላል ። ሲቀጥልም
" ከዛም በሩን ስከፍት ባየሁት ነገር ደነገጥኩኝ ። በዚህ ጊዜ ኢማሙ አሻፊኢ እንዲህ አሉኝ " አንተ ዩኑስ ሆይ! ብዙ መስአላዎች አስማምተውን ሳለ አንዲት መስአላ ታለያየናለች"
↠ በሁሉም ልዩነቶችና ክርክሮች ላይ ማሸነፍን አትሞክር ። አንዳንድ ጊዜ አጋጣሚዎችን ከማሸነፍ ይልቅ ልቦችን ማሸነፍ ይበልጣል ።
↠ የገነባሀቸውንና ያለፍካቸውን ድልድዩች በትንሽ ምክንያት አታፍርስ ። ምን አልባትም ለመመለስ አንድ ቀን ሊያስፈልጉህ ይችላሉና።
↠ምን ጊዜም ስህተቱን እንጂ ተሳሳቹን ሰው አትጥላ ።
↠ንግግሩንም አውግዝ ነገር ግን ተናጋሪውን አክብር።
↠ በሙሉ ልብህ ወንጀሉን ልትጠላ ቢገባህም ለወንጀለኛው ግን ማዘን አለብህ ።
↠ የኛ ሀላፊነት ህመሙን እንጂ ህመምተኛውን ማስወገድ እንዳለሆነ ልናውቅ ይገባል ።
ይ ላ ሉን share
┏━ ━━━━ ━┓
@Halal_Fonqaa
┗━ ━━━━ ━┛
2.3K views Cʀᴀᴢʏ ʟᴏᴠᴇ , 12:56