Get Mystery Box with random crypto!

ʜᴀʟᴀʟ ꜰᴏɴǫᴀᴀ || ሀላል ፎንቃ

የቴሌግራም ቻናል አርማ halal_fonqaa — ʜᴀʟᴀʟ ꜰᴏɴǫᴀᴀ || ሀላል ፎንቃ ʜ
የቴሌግራም ቻናል አርማ halal_fonqaa — ʜᴀʟᴀʟ ꜰᴏɴǫᴀᴀ || ሀላል ፎንቃ
የሰርጥ አድራሻ: @halal_fonqaa
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.56K
የሰርጥ መግለጫ

የአላህ እዝናት ሠላም ፍቅር አንድነት በሁላችሁም ለይ ይወራድ !!
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን
ይህ Channel የናንተ Channel ነው!! ስለ ዲነቻን የምናውቅበት ቤታችን ነው።
🌺 የነቢያት ታሪክ 🌺
🌺አስገራሚ መልዕክቶች🌺
🌺ጣፋጭ እውነተኛ ታሪኮች🌺
ኢስሊምነን 💓 የመሰለ ምን አለ!
🚩 አስተማሪ እና አዝናኝ ገጠመኝ እዚ ይገኛል።
💌 @Damme_man

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 23:40:25  
ለውድ እህቴ ውድ ስጦታ
 
የ ሀ ራ ም ፍ ቅ ር
    ( ቦይ-ፍሬንድ  ገርል-ፍሬንድ )
 
ወላሂ መነበብ ያለበት በጣም አስተማሪ ፁሁፍ ነው። አልሃምዱሊላህ ለብዙዎች የመመለስ ሰበብ ሆኗል። ብዙዎችም ፁሁፍን አምበብው ጥንቃቄ እያደረጉ ነው።

ውድ እህቴ ለአላህ ብለሽ ሶስቱንም ክፍል አምብቢው።

→ ክፍል አንድ

بــســم الــلــه الــرحــمــن الــرحــيمــ
الحمد الله رب العالمين

 ውድ እህቴ የሃራም ፍቅር ግኑኝነትን በጣም በሩቁ ልትጠነቀቂው ይገባል ምክንያቱም በዚህ ሰዓት ብዙ እህቶችሽ እየተፈተኑበት የሚገኙው ከባድና አስቸጋሪ ፊትና ነው አሁን ባለንበት ዘመን የተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች ተበራክተዋል ለምሳሌ ዋሳፕ ፌስቡክ ኢሞ ቴሌግራም እና መሰል ሚዲያ አፖች አሉ በነዚህ ቴክኖሎጂዎች ከሚመጡ ፊትና እራስሽን ማራቅ ይኖርብሻል። ግን በሚያሳዝን ሁኔታ ብዙ እህቶች በነዚህ ሶሻል ሚዲያዎችና ስልክ በማውራት ከተለያዩ ወጣቶች ጋር የሃራም ፍቅር ግኑኝነት ፈጥረዋል ለምን እህቶች ተብለው ሲጠየቁ ምን ችግር አለው ለቀልድ ለመዝናናት እና ጊዜ ለማሳለፍ ብቻ ነው ብለው ይመልሳሉ።
ውድ እህቴ ይሄንንስ የሃራም የቀልድ ግኑኝነት እንድትቀርቢው ማን ነው የፈቀደልሽ  ውድ እህቴ ይሄ ሃራም ነው። አላህን ፍሪ! እንዲህ አይነቱ የሃራም ፍቅር ግኑኝነት በኢስላም በጥብቅ የተከለከለ ነው እስከዛሬም ወደፊትም በሸሪዓው አልተፈቀደም። እንደውም ከከባባድ ወንጀሎች ሊመደብ ይችላል ምክኛቱም እህቴ ያን ሚስኪን ወጣት በለስላሳው ድምፅሽና አንደበትሽ ተስፋን ሰጠሽ ፍተና ላይ ትጥይዋለሽ  በአላህ ይሁንብኝ ስንትና ስንት ወጣቶች ናቸው በሃራም ቆሻሻ ተግባራቶች ላይ የወደቁት ምክንያቱን ሲናገሩ እንደምንሰማው በእከሌ ምክንያት ተፈትኜ እከሌ ፊት ባትሰጠኝ እከሌ ባታማልለኝ ኖሮ እንዲህ አልሆንን ነበር ይላል። እና መሰል የፊትና ሰበቦች እያመጣሽባቸው ስለሆነ ነው። እና በማንኛውም ምንገድ ለወንድሞችሽ ፈተና ከመሆን ልትጠነቀቂ ይገባል።
 
ወድ እህቴ ከየትኛውም አይነት ወጣት ጋር የሶሻል ሚዲያ የሃራም ፍቅር ግኑኝነት ሚባለውን በጣም በሩቁ ልትጠነቀቂው ይገባል በጣም ተጠንቀቂ  ፍቅር አይደለም ብለሽ ልታወሪም አይገባም በፁሁፍ የምታወሪውን በስልክም ምታወሪውን ልታቆሚ ይገባል። ትዳር ፈልገሽም ከሆነ በዚህ በሃራም ምንገድ መሆን የለበትም ብዙዎች ትግስት እያጡ ወደ ሃራም ፍቅር ይገባሉ ግን መፍትሄው ይሄ አይደልም ማወቅ ያለብሽ ነገር በሃራም ፍቅር የጀመርሽው ግኑኝነት መጨረሻ ላይ ልታገቢው ብትችይ እንኳ ለትዳርሽ ጥፍጥናን አታገኝም ምክንያቱም በሁለት ጥንዶች መሃል መዋደድንና መተዛዘንን የሚያደርገው አንድ አላህ ብቻ ነው። እና አላህን አስከፍትሽ በሃራም ባመጣሽው ትዳር እንዴት ደስተኛ ህይወት ልትኖሪ ትችያለሽ።ይሄ በጭራሽ አይሆንም ካገባሽው በኋላ ባጭር ግዜ ውስጥ በትናንሽ ነገር ትዳራችሁን ይበጠብጠዋል እና ቆም ብለን አርቀን በማሰብ ከዚህ የሃራም ግኑኝነት እንራቅ አላህን በማስቆጣታችን ጉዳቱ ለኛ እንጂ ለአላህ አይደለም።
 
በዚህ የሃራም ፍቅር ውስጥ የተደበቀውን እውነታ እነግርሻለሁ በደምብ አድምጪኝ
 
→ የመጀመሪያው እውነታ፦  አንችን ሊወድሽ ይችላል ግን ካንችም ውጭ ሌሎችን ብዙ ሴቶችንም ይወዳል ያወራል ይህ ማለት አንችም ላይ ይጫወታል ካንችም ውጭ ብዙ ሴቶች ጋር ግኑኝነትን ይፈጥራል። ይህ የመጀመሪያው እውነታ ነው። ሲጀመር ለአላህ ያልታመነ እንዴት ላንቺ ሊታመን ይችላል።? ይሄ የመጀመሪያው የተረጋገጠ እውነታ ነው ንቂ እህቴ! ይሄን በተለያየ መንገድ ማረጋገጥ ትችያለሽ
 
 → ሁለተኛው እውነታ ደግሞ ምንም ጋብቻ ሚባለውን ነገር አያስበውም አላማውም ግቡም የለውም ይህ ማለት ወደ ጋብቻ አይገፋፋሽም ሀሳቡም ግቡም የለውም እንደውም ካንች ጀርባ ሁኖ ስላንች ብዙ ያወራል ከኔ ውጭ ሌላ ውንድ ጋር እያወራች ከሃዲ ናትኮ እያለ ስምሽን ያጠፈዋል ግን በተዘዋዋሪ እሱም አንችን ይከዳሻል።
 
→ ሦስተኛው እውነታ አንችን የሱ ባሪያ ወይም ምርኮኛ የሚያደርግብሽ በሁለት ከባባድ ምክንያቶች ነው።
 
 ↠ አንድኛው ያንች የተገላለጡ የራቁት ፎቶዎች ካሉት ነው። ይህ ወንድ ልጅ ይሄ ፎቶሽ ካለው አንቺን የሚያስፈራራብሽ የመጀመሪያው ከባድ ሰበብ ይሄ ነው። እሱ ያሰበው ሃራም ነገር የማትሰሪ ከሆነ ያን ፎቶ ለሌሎች አሰራጨዋለሁ ብሎ ያስፈራራሻል ይሄኔ አንች አቋምሽን እያለወጥሽ ትመጫለሽ ምክኛቱም ሌላ ነገር ለማድረግ አትደፍሪም እሱ የያዘብሽ ሚስጥራዊ ፎቶ ስላለ ትፈሪያለሽ ያኔ ያዘዘሽን ቆሻሻ ነገር ሁሉ ትሰሪያለሽ። እና እባካችሁ ተጠንቀቁ እህቶች ፎቶ መላላክ ይቅርባችሁ እባካችሁ ለማንም ፎቶ አትላኩ ሌላው ይቅርና የምትቀርቢያትና የምታምኛት ጓደኛሽ እንኳ ብትሆን ፎቶሽችን እንዳትልኪላት እስካሁን ከነበረም አስጠፊ ምክንያቱም በገዛ ፎቶሽ አሳልፋ ልትሰጥሽ ትችላለች። በያዘችብሽ በገዛ ፎቶሽ ልታስፈራራሽ  ትችላለች ወይም እሷ ሳታውቀው ከሷ ሌላ ሰው ሊወስደው ይችላል ስለዚህ ፎቶ መላላክ ጭራሽ አስፈላጊ አይደለም።
  ኖርማል ፎቶ እንኳ ቢሆን ከራቁት ፎቶ ጋር አቀናብረው ሊያስፈራሩሽ ስለሚችል ራስሽን ከማንኛውም ፎቶ አፅጂ በሚዲያ የለቀቅሻቸውም ፎቶዎች ካሉም አጥፊያቸው።
    ራስን ቁጥብ ማድረግ ለራስ ነው ሚጠቅመው!


ይ ቀ ጥ ላ ል ክፍል ሁለት

ውድ እህቴ ይሄን ፁሁፍ በውስጥ መስመር ለምታውቂያቸው ሁሉ ሼር የማድረግ ሃላፊነት አለብሽ
ምን አልባት የአንድ ሰው የመመለስ ወይም ጥንቃቄ የማድረግ ሰበብ ልትሆኚ ትችያለሽ እና ለአላህ ብልሽ ሼር አድርጊው።

Share ሼር share

ቀጣዩን ሌሎችን ለመከታተል ቻናሉን ይቀላቀሉ
Coment
@jezakellah

በዝሙት አንዘምን የቴሌግራም ቻናል
Join us on t/g channel


https://t.me/latekrebu_zina
https://t.me/latekrebu_zina
https://t.me/latekrebu_zina
የዝሙት ሌላኛው ስሙ የሃራም ፍቅር ነው!
147 views Cʀᴀᴢʏ ʟᴏᴠᴇ , 20:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 23:09:22 ከአላህ ሱብሀነሁ ወተአላ ዉጭ በሆነ ነገር የተሞላ ልብ ሁሉ ባዶ ነው !!!

{ وَأَصْبَحَ فُؤَادُ أُمِّ مُوسَىٰ فَٰرِغًا }


«የሙሳም እናት ልብ ባዶ ሆነ »

【አል ቀሰስ 10】

የሙሳ እናት ሙሳን ከማስታወስና ስለእሱ ከማሰብ ውጭ ሌላ ልቧን የሞላው ነገር አልነበረም ።

{إِن كَادَتْ لَتُبْدِى بِهِۦ لَوْلَآ أَن رَّبَطْنَا عَلَىٰ قَلْبِهَا لِتَكُونَ مِنَ ٱلْمُؤْمِنِينَ}

« ከምእምናን ትሆን ዘንድ በልቧ ላይ ባላጠነከርን ኖሮ ልትገልጸው ቀርባ ነበር፡፡»

አላህ በልቧ ላይ ያለውን ኢማን ባያፀናላት ኖሮና ባትጠናከር … ሙሳ ልጇ እንደሆነ በተናገረች ነበር … ይህም የማንኛውም ባዶ ልብ ሁኔታ ነው ። ባጋጠመመው ችግርና መከራ በፍርሀት ሊበር ይደርሳል ።

በአላህ እንደማመንና እንደመተማመን ሊያፀናውና ሊያጠነክረው የሚችል ነገር የለም።

ለእነዚያ ለተጨነቁና ግራ ለተጋቡ ልቦች ከዚህ በአንደበት ውስጥ ከሚሰርፀው ኢማን በስተቀር መረጋጋትና ስክነትን የሚያሰፍን ነገር የለም ።


ይ ላ ሉን share
┏━ ━━━━ ━┓
@Halal_Fonqaa
┗━ ━━━━ ━┛
234 views Cʀᴀᴢʏ ʟᴏᴠᴇ , 20:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 22:13:11 #ቀደምቶች_ለ_አላህ_የነበራቸው_ፍራቻ

#ክፍል_2
አንድ ሰው አንዲትን ሴት ወደዳት እሷም ወደደችው ከዚያም በሆነ ቦታ ተገናኙ
ይህችም ሴት ይህን ሰው ከ ነፍሱ አባበለችው( ፈለገችው) እሱም አጀሌ(የመሞቻ ቀኔ) በእጄ አይደለም ያንቺም አጀል በእጅሽ አይደለም ምናልባት ጊዚያችን ቀርቦ አመፀኞች ሆነን አላህን ልንገናኝ እንችላለን አላት
እሷም እውነት ብለሃል አለችው
ከዚያም ወደ አላህ በፀፀት ተመለሱ ሁኔታቸውም ያማረ ሆነላቸው በኋላ ላይም ከእሱ ጋር ትዳር መሰረተች!


(ምንጭ፦
روضة المحبين ونزهة المشتاقين
ابن القيم الجوزية
አንድን ነገር ለአላህ ብሎ የተወ አላህም ለእሱ የተሻለውን ነገር ይለግሰዋል!
ይ ላ ሉን share
┏━ ━━━━ ━┓
       @Halal_Fonqaa
┗━ ━━━━ ━┛
463 views Cʀᴀᴢʏ ʟᴏᴠᴇ , 19:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 21:44:31 ‍ ​ ዳግማዊት ራህመት
ደራሲ ኢሳቅ ሀብታሙ
ክፍል ሶስት


ኤሊያስ ፈገግ ያለሁ ለካ ከራህመቴ ደብዳቤ ተቀብሎ ነበር ለሪድዋን ስትልኝ ብላ ሰጠችው
ከፍቼ ማንበብ ጀመርኩ
ሪዱ ሆይ ያመመኝ ነው ህመሜ ምን እንደሆነ ታውቃለ? ናፍቆት ይሰኛል ሐኪሞቹ መዳኒቴ የአንተ አይን እንደሆነ ነገሩኝ ሪፈር ፅፈው ሰተውኛል ሪዱ ሳልሞትብህ አግኘኝ ከሰላምታ ጋር ያንተዋ ራህመት
ራሴን መቆጣጠር አቃተኝ በደስታ ብዛት ስካር ውስጥ ወደኩ ሳይጠጡ መስከር በጣም ደስ ይላል ትምህርት ባይኖረኝም እሷ ጋ ሄድኩ በጣም አምሮባታል ተገናኘን ጥሩ ጊዜ አብረን ካሳለፍን ቡኃላ ስልክ ቁጥሬን ሰጥቻት ተለያየን ለኔ ሲል ኢሊያስ ትምህርት ጀመረ ብዙም ሳይቆይ እኔም ሚኒስትሪ ተፈተንኩ እነ ኤሊያስ ከሁለት ሳምንት ቡኃላ ትምህርት ጨረሱ ክረምቱ ገባ ከእለታት አንድ ቀን የኤሊያስ እናት በጣም ስለታመሙ ለመጠየቅ ሄድን እዛ ስንደርስ እናቱ ወደ አኪራ ሂደዋል ኢሊያስ ከሀዘን መውጣት ተሳነው በጣም ይከብድ ነበር

ከአራት ወራት ቡኃላ ዛሬ በጣም ደስተኛ ሁኛለሁ አይስኩል ገባሁ ኤሊያስም ከነበረበት ስሜት የወጣ ነው ራህመቴ በጣም ኮርታብኛለች ሚኒስትሪ ጥሩ ውጤት በማምጣቴ ምክንያት ኤሊያስ አስጠንቅቆ ነው የላከኝ ፍቅሬን እንድገልፅላት እኔም እሱ ያለኝን ላደርግ ወደ ክፍላቸው ሳቀና ከጓደኞቿ ጋር ሀይለኛ ወሬ ይዛ ነበር አረብሻትም ብዬ ትቼ ወጣሁ ከክፍላቸው ስለ አይስኩሉ ትንሽ ልበላቹ የተሰራው 2006 costa foundation በተባለ የግል ተቋም ነው ጊቢው በጣም ውብ ነው አንድ ነገር ይጎላቸዋል እንጂ ምን መሰላቹ ራህመትን የመሰለች ቆንጆ ሴት እሷን ከፍለዉ ነበር ማስገባት የነበረባቸው ግን ነገ የመጣው ይምጣ ፍቅሬን ከመግለፅ ወደኋላ አልልም ብዬ ለራሴ ቃል የማይደርስ ነገር የለምና ቀኑ ከብዙ ደቂቃዎች እና ረዢም ከሚመስሉ ሰዓታት ቡኃላ ወደነ ራህመት ክፍል ሊሄድ ስል የትምህርት ቤቱ ጊቢ ዝግ ነበር ያለኝ አማራጭ በአጥር መሽሎክ ነበረ አደረኩት ግን ምን ያደርጋል ተያዝኩ መጨረሻ ለይ ወላጅ እንዳመጣ ተወሰነብኝ ምንም እንኳን ብባረርም ራህመቴ ጋር መሄዴ ስለነበረብኝ ቀጥታ ሄድኩ ያየውትን ማመን ተሳነኝ

የኔዋ ራህመቴ ከሆነ ልጅ ጋር ስትሳሳም አየሁ ምን አለ በህልሜ ቢሆን እያለቀስኩ ወደ ቤት ገባሁ ካሁን ቡኃላ ማድረግ ያለብኝ ትምህርቴ ለይ ማተኮር ብቻ ነው ሀሰኔ ተጫውቶብኛል እስኪ ምን አድርጌው ነው እንዲህ የሚጫወትብኝ? ደግሞ የኔስ ነገር አይገርምም አምኜው ጊዜዬን መፍጀቴ እሷ ጋር ለማሳለፍ ስል ስንት ክፍለ ጊዜ ፎረፍኩ ይበለኝ የራሴ ጥፋት ነው የሚገርመው እኮ የኤሊያስ ነገር ነው ተሳስተህ ነው እንጂ እሷ እንዲህ አታደርግም ማለቱ ከአይኔ በላይ ማንንም አላምንም እርግጠኛ ነኝ ራሷ ናት ዱዓ ማድረግ ጀመርኩ ከጥቂት ጊዜያት ቡኃላ ራህመት አይኗን በጨው አጥባ መነጋገር አለብን አለችኝ
የጨረስን መስሎኝ
እባክህ ምን ተፈጥሮ ነው አታስጨንቀኝ
እኔ ልጠይቅሽ እንጂ ካልሰገድክ ካልቀራህ እንዳታናግረኝ ያልሽበት ኢማን ነው አጅ ነቢ ወንድ ጋር ያሳሳመሽ? እኔን አጅ ነቢ ወንድ አልጨብጥም ብለሽ መሳሳሙን እንዴት ደፈርሽ ባክሽ?
ስለምንድ ነው የምታወራው
ከልቤ አፍቅሬሽ ነበር እንኳን ደስ አለሽ ተጎድቻለሁ
እኔም እኮ አፈቅርሃለሁ
እረ ባክሽ ታዲያ ሌላ ወንድ ጋር ምን አሳሳመሽ የኔ ፍቅር ነው?
ብዬ ሳልጨርስ በጥፊ ብላኝ ሄደች ከትንሽ ቆይታወች ቡኃላ ራህመቴ ሁለት ሰዎችን ይዛ መጣች የሆነ ቦታ የማቃቸው መሰለኝ አንዷ ራህመቴን ቁርጥ ይበልጥ ግራ ተጋባሁ ለምን ይዛቸው መጣች እነማን ናቸው? ራህመቴ እያለቀሰች ነው ለምንድ ነው የምታለቅሰው? እንባዋን እና ጎሮሮዋን እየጠረገች
አሚና ትባላለች እሱ ደግሞ ጣሂር ፍቅረኛዋ ነው በስንት ልመና ነው ወደ ዚህ ያመጣዋቸው
አሀ ትዝ አለኝ ገና አንቺ ጋር ተመሳስላብኝ ነው እሱን ነበር ያየሁት
መንታ ነን እኔም ጠርጥሬ ነበር የተፈጠረውን ስነግራት እንዳየችህ እና ያለቀስክ እንደሄድክ ነገረችኝ አሁንስ እውነታው ገባህ
በጣም ይቅርታ ልረዳሽ ስላልሞከርኩ ሽልማቱ ይገባኝ ነበር
የቱ ሽልማት
ጥፊዋ ናታ
በጣም ይቅርታ ማድረግ አልነበረብኝም ግን አትዘንብኝ የማደርገውን ሳጣ ነው
ኧረ ችግር የለውም
እኔ ምልህ ስሄድ ለምን አላስቆምከኝም
ልብሽ እኔ ጋር ስለሆነ ትመለሻለሽ ብዬ ነው

በቃ እንዴት ልንገራቹ በጣም ደስ ብሎኛል አሁን ራሱ ቤት ውስጥ ብቻዬን ስስቅ ያበድኩ መስሎት ኤሎ የተገረመ ነው ሁሉም ነገር ለከይር ነው በራህመት ማዘኔ መጣላቴ መጨረሻ ለይ የዘወትር ምኞቴ የነበረው ቃል ከአንደበቷ ሰማው ሰሞኑን ጥሩ ጊዜ አብረን ያሳለፍን ነው ዛሬ የሆነ የምነግርህ ነገር አለ ብላኝ ወደ ሷ የሄድኩ ነው

ክፍል አራት ይቀጥላል

ይ ላ ሉን share
┏━ ━━━━ ━┓
@Halal_Fonqaa
┗━ ━━━━ ━┛
614 views Cʀᴀᴢʏ ʟᴏᴠᴇ , 18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 21:42:59 •°•☞የማላቀው ባሌ☜•°• {በነኢማ ኸድር} ክፍል ➌ እኔም የሁቢ አባትም ዱብዳ የሆነብን ያ አስቀያሚው አሁን ግን ውብ የሆነልንን ቀን አሻግሬ ማሰብ ጀመርኩ ድንገት ሁቢ ከሀሳብ በሀር አስወጣችኝ እንጂማ ብዙ እርቄ ሄጄ ነበር ሁላችንም ተነስተን የፈጅርን(የንጋትን)ሰላት ከሰገድን ብሀላ ሁቢና አባቷ ወደ መኝታ ክፍል ገብተው እንቅልፋቸውን ቀጠሉ ሴት ስትሆን ብዙ ሀላፊነት አለብህ እናም የቤት እመቤትነትና…
601 views Cʀᴀᴢʏ ʟᴏᴠᴇ , 18:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 17:30:34 ዘላለም አትኖርም /አትኖሪም
         ሞት አለ ወዳጄ    
    
.....አንዳንዴ ጉዳይ አለኝ ብለህ እየተጣደፍክ ምትሄድበት ቦታ ላይ የሞት ቀጠሮህ እዛ ልሆን ይችላል ።
《عن أبي عزة يسار بن عبد الله الهذلي، عن النبي ﷺ  قال: إن الله إذا أراد قبض عبد بأرض، جعل له بها، أو فيها حاجة》
የአላህ መልእክተኛ ሰላትና ሰላም በሳቸው ላይ ይሁንና እንዲህ አሉ ፦
{አላህ ሱብሀነሁወተአላ ለአንድ ባሪያ የሆነ ቦታ ላይ ሩሁ እንዲወጣ ሲፈልግ እዛ ቦታ ወይም በዛ ቦታ ውስጥ የሆነ ጉዳይ ያደርግለታል።}}
أخرجه أحمد، والترمذي، وابن حبان

ሀቂቃ እውነታው በጣም ይገርማል
ስንቱ ነው እዛ ቦታ ላይ ጉዳዬን ፈፅሜ መጣሁ ብሎ በሰላም ይወጣል ከትንሽ ሰአት በኋላ የሞት መርዶው ይሰማል

ስንቱ ነው ሀጃውን ፈፅሞ ልክ እቤቱ ጫፍ ሲደርስ ባላሰበው አደጋ ህይወቱ የሚቀጨው

ስንቱ ነው ተውቦ ተጊጦ ለጉዳዩ ሲጣደፍ ቀጠሮው ደርሶ ባላሰበው አደጋ በደም ተነክሮ ሚመለሰው!

.... ይህም የሆነበት ምክንያት ማንኛውም ሰው የሚሞትበት ቦታና ሰአት ስለማያውቅ ነው። አላህ እንዳናውቀው ከሩቅ ሚስጥር ካደረጋቸው ጉዳዮች ውስጥ አንዱ ስለሆነ ነው። ለምን ከተባለ፦
ገና ወጣት ነኝ አሁን አልሞትም
ሙሉ ጤነኛ ነኝ ሞት አያገኘኝም ሳንል በሁሉም ሰአትና ቦታ ሆነን ሞት በድንገት ባላሰብነው ሰአትና ሁኔታ ሊመጣ ስለሚችል በዝግጅት ላይ ሆነን እንድንጠብቀው ነው።
ስንቱ ወጣት ነው ገና በለጋ እድሜው ዱንያን የተሰናበተው
ስንቱ ጀግና ነኝ ማን አለብኝ ሲል የነበረው ሁሉ ሳያስበው በድንገት ቀብር የገባው
ስንቱ ተመራቂ በምረቃው ቀን፣ ስንቱ ወጣት በሚሞሸርበት ቀን፣ ስንቱ ተስፈኛ ተስፋው በሚሳካበት ቀን ሳያስቡት አፈር ስር የገቡት
አስተውል ሌላው ቢቀር ወይ እናት፣ ወይ አባት፣ ወይ አጎት፣ ወይ ልጅ፣ ወይ እህት፣ ወይ አያት ሳትቀብር አትቀርምና በነሱ ትምህርት ውሰድ
እነሱም እንዳንተው ገና አግብተው ወልደው፣ ሀብታም ሆነው፣ ከብረው ተከብረው፣ ወግ ማእረግ አይተው፣ ደና ቤት መኪና ገዝተው የመኖር ህልም ነበራቸው። ኑሮን አሸንፈው ስኬታማ መሆን ይፈልጉ ነበር። ነገር ግን አልሆነም ቀጠሮው ደርሶ ወደ ማይቀረው አለም ሄዱ። ነገ ያንተም ተራ እንደሚደርስ አትዘንጋ።
ግን በጣም ሚገርመው እነሱ ጥለውት በሄዱት በዚህ ዱንያ ተታለን ሞትን መርሳታችን ነው። ለዱንያ ብለው ከፊሉን ከፊሉን መግደሉንና መጨካከናችን ነው። የሸይጧንና የነፍስያችን ባሪያ መሆናችንን ነው። በወንጀል ባህር ሰምጠን ያለ እስቲግፋርና ያለፀፀት በዚሁ አመፅ ላይ ህይወታችን መግፋታችን ነው። ሀቂቃ የብዙዎቻችን ሁኔታ ሲታይ ሞት የለም ዘላለም ነው ምትኖረው የተባልን ወይም አብሽር ጀነት ላይ ቦታ ተይዞልሀልና ዘና በል የተባልን ነው ሚመስለው

ወዳጄ
የቀብር ጨለማ እንዳያገኝህ፣ የሲራጥ ሜንጦ እንዳይቧጥጥህ፣ ኪታብ በቀኝ እጅ እንዲሰጥህ፣ ጀነት በሰላም ግባ አትጨነቅ አትፍራ ትባል ዘንድ በመልካም ስራ በመበርታትና ከመጥፎ ስራ በመቶበት ወደፊት ቀጥል


ይ ላ ሉን share
┏━ ━━━━ ━┓
@Halal_Fonqaa
┗━ ━━━━ ━┛
859 views Cʀᴀᴢʏ ʟᴏᴠᴇ , 14:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 08:30:13
Islamic quotes

ፍቅር ያሸንፋል
ባንቱ አይተናል ነቢ !!

ይ ላ ሉን share
┏━ ━━━━ ━┓
@Halal_Fonqaa
┗━ ━━━━ ━┛
1.2K views Cʀᴀᴢʏ ʟᴏᴠᴇ , 05:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 08:18:27 •°•☞የማላቀው ባሌ☜•°•
{በነኢማ ኸድር}
ክፍል ➌
እኔም የሁቢ አባትም ዱብዳ የሆነብን ያ አስቀያሚው አሁን ግን ውብ የሆነልንን ቀን አሻግሬ ማሰብ ጀመርኩ ድንገት ሁቢ ከሀሳብ በሀር አስወጣችኝ እንጂማ ብዙ እርቄ ሄጄ ነበር ሁላችንም ተነስተን የፈጅርን(የንጋትን)ሰላት ከሰገድን ብሀላ ሁቢና አባቷ ወደ መኝታ ክፍል ገብተው እንቅልፋቸውን ቀጠሉ ሴት ስትሆን ብዙ ሀላፊነት አለብህ እናም የቤት እመቤትነትና እናትነት ሲጨመር ደሞ ከ 11 ሰአት በኀላ መተኛት አይታሰቤ ነው ሁሉም ጓዳውን ለመሙላትና ባለቤቱን ለማስደሰት መአድቤት መፍጨርጨር የተለመደ ነው ዛሬ እሁድ ነው በኛ ቤት ህግ እሁድ ለት ቤተሰቡ ሁሉ አብሮ ይውላል የሁቢ አባት በጠዋት ከእንቅልፉ ተነስቶ ወቷል ወዴት እንደሄደ ግን እንጃ ከ ሁለት ሰአታት ቆይታ ብሀላ ተመልሶ መጣ እሁድ እሁድ ሁሌ በዚ ሰአት ወቶ ይመለሳል እስከዛሬ ግን የት እንደሚሄድ ሳይነግረኝ ነው ሚወጣው ለወትሮ እንደዚ አይነት አመል ፈፅሞ የለበትምም ልጠይቀው አልጠይቀው እያልኩ ሁሌ አቅማማለው ዛሬ ግን የት እንደሚሄድ ማወቅ ጉጉት አድሮብኝ "ማሬ"አልኩት እየተርበተበትኩ "ወዬ የሁቢ እናት"አለ ይቺ ቃል ሁሌም ስሰማት ልቤ በሀሴት ትሞላለች "የት ሄደክ ነው ቆየህ እኮ" አልኩት የሞት ሞቴን ላወጣጣው መሆኑ ነው "እእእ አይ እዚ.. "ብሎ ሳይጨርስ ሁቢ መፀዳጃ ቤት ገብታ ነበር "ማሚ ጨርሻለው ነይ"አለች ሳይጨርስልኝ ሁቢ ጋር ሄድኩኝ ግን ሁሉ ሀሳቤ የሁቢ አባት ጋር ነበር ለኔ ሳይናገር የሚሄድበት ቦታ የት ነው ወይስ ከኔ ሚደብቀው ነገር አለ ብዬ አሰብኩ ቀኑን ተጣጥበን ሁላችንም ወጣን ዛሬ የሁቢ ተራ ስለሆነ ሁቢን ሊያዝናናት የሚችል ቦታ መርጠን ወደዛ ለመሄድ ከሰፈር ወጣን ቀኑን ሙሉ ሁቢን አስደስተር ወደ አስር ሰአት ላይ የአስር ሰአት ሰላትን ሰግደን ወደቤት ተመለስን ድንገት የ እማማ ሰኢዳ ቤት ስንደርስ ሀቢ"አባቢ የእማማ ሰኢዳ ቤት አባቢ በናትህ እንግባና ትንሽ እናጫውታቸው ይደብራቸዋል እኮ"አለችው ከኀላ ከተቀመጠችበት እየተነሳች " የሁቢ አባት መኪናውን አቁሞ" ሁቢ አንቺና ማሚ ግቡ እኔ ደክሞኛል"አለና እንደምንም አሳምኖን እኛ ገባን እሱ ወደቤት ሄደ እማማ ሰኢዳ እንደወትሮ አልነበሩም አዲስ ልብስ ለብሰዋል ብታቸውም ቡዙ ነገሩ ተቀያይሯል በ አንድ ቀን ለውጥ ተገረምኩኝ ባለፈው የነገሩኝ ልጅ እንደሆነ ገብቶኛል እማማ ሰኢዳ እንደወትሮዋቸው "ማነው" አሉ በደከመና ባረጀ አንደበት "ሁቢና እናቷ ነን እማማ ሰኢዳ"አለች ሁቢ ፈጠን ብላ በዛ በሚኮላተፍ አንደበቷ ንግግሯ አስገርሞኝ እጅን አፌ ላይ ጭኜ ተመለከትኳት "የልጅ ቅመም እስኪ ነይ ልሳምሽ"አሏት እጃቸውን ዘረጉላት ሁቢ እየሮጠች ሄደች እማማ ሰኡዳ ደብሯቸዋል ብና ላፍላ ብላቸውም እንቢ አሉኝ ትንሽ ጊዜ ከሁቢ ጋር አጫወተናቸው እኛ ወደቤት ተመለስን ነገ ሰኞ ስለሆነ ለሁቢ የምትይዘውን ምሳ ለኛም እራት እንዲሆነን ምግብ ሰራሁኝ ውሎ'ችንም ምሽታችንም እንዳማረ ወደ መኝታ ቤት ገባን እና እስከ ንጋት 12 ሰአት ለሽሽ ብለን ተኛን እንደ ድንገት የመኪና ክላክስ ከ እንቅልፌ አነቃኝ ከኛ ቤት አጠገብ ያሉት ተከራዮች ሁሌ ከቤት ሲወጡ በር እንዲከፈት የሚያሰሙት ድምፅ ነበር ደንግጬ ተነሳሁ ሁቢ አጠገቤ የለችም ግራ ገባኝ የሁቢ አባት(ሀፊዝ) አጠገቤ ነው ግራ ተጋባው ከአልጋው ብድግ ብዬ "ሁቢ" ብዬ ወደሳሎን ሮጥኩኝ ሁቢ መልስ አልሰጠችኝም...

ክፍል ➍ ይቀጥላል ..

ይ ላ ሉን share
┏━ ━━━━ ━┓
@Halal_Fonqaa
┗━ ━━━━ ━┛
1.1K views Cʀᴀᴢʏ ʟᴏᴠᴇ , 05:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 07:59:04 ‍ ኢክራም
ፀሀፊ ሂራ
ክፍል አንድ

የሰው ልጅ በህይወት ለመኖር ምግብ፣ውሀና መጠለያ እንደሚያስፈልገው ሁሉ ፍቅርም ለመኖር ያስፈልገዋል።ፍቅርን ሲያጣ በሰው ተከቦ ብቸኝነት ይሰማዋል መኖር ያስጠላዋል በአንድ ግለሰብ ፍቅር ካጣ ከሌላ ግለሰብ ዳግም የሚያገኝ አይመስለውም።ሁሉም ሰው አንድ ይመስለዋል።እኔ የደረሰኝ እጣ ፈንታ ይሄው ነው።

ሰው የመጥላት ምክንያቶቼ ዘመዶቼ ናቸው።በነሱ ምክንያት ሀሉም ሰው መጥፎ ይመስለኛል።በተለይ ሀብታሞችማ ከሰው የተፈጠሩ አይመስለኝም።

ስሜ ኢክራም ይባላል የተወለድኩት አዲስ አበባ ነው።በድህነት ተወልጄ በድህነት ነው ያደግኩት።አሁን ላይ ግን ደና ኑሮ ነው የምኖረው።እናትም አባትም የለኝም።እህትና ወንድምም እንዲሁ።በቃ በአጭሩ ብቸኛ ነኝ።መጀመርያ ጥላኝ ወደ አኼራ የሄደችው እናቴ ናት ከዛን አባቴ።ግን በመሀላቸው የረዥም አመት ልዩነት አለ።እናቴን አላስታውሳትም በህፃንነቴ ነበር የተለየችኝ።አባቴ ደግሞ በሃያ አመቴ ነው ጥሎኝ የነጎደው።
አባቴ በጣም ሲበዛ ደግ ሰው ነው።በጣም የመገርመኝ ከሚያገኘው አነስተኛ ገቢ እራሱ ከኔ የባሱ ተንቀሳቅሰው መስራት የማይችሉ ስለሚኖሩ እያለ ለተቸገረ የሚሰጠው ነገር ነበር።መስጠት የማይሰለቸው ሰውን የማይንቅ ለትንሹም ለትልቁም ክብር ያለው አባት ነበረኝ።እናቴ ከሞተች ቡሀላ እንደናትም እንደ አባትም ሁኖ አሳደገኝ።እኔን ለማሳደግ ያየው ስቃይ የበረታ ነበር።ግን ያንን ስቃይ ሲያይ ምን ልርዳህ ያለው ሰው አልነበረም።
እራሴን አስክችል ድረስ ጠዋት ት/ቤት እያደረሰኝ ከሰአት ከትምህርት ቤት አውጥቶ ስራ የሚሰራበት ቦታ እየወሰደኝ ማታ አብረን ወደ ቤት አንገባለን።ራሴን በደንብ ካወቅኩ ቡሀላ ግን እኔ ተማሪና የቤት እመቤት አባቴ ደግሞ የቤት አባወራ ሁነን መኖር ጀመርን።
አባቴ ለትምህርቴ ትልቅ ቦታ ስለሚሰጥ እንድቀልድ አይፈልግም።እኔም ተምሬ የሱን ህልም ለማሳካት እጥራለው።ያው ለወጉ የቤት እመቤት ነኝ አልኳችሁ እንጂ የኔ ስራ ቤት ማፅዳት ብቻ ነው ሌላውን አባቴ ነው የሚሰራው።

የምንተዳደረው አባቴ ድንጋይ ተሸክሞ በሚያመጣው ገንዘብ ነው።እሱን ስራ እራሱ የማያገኝበት ግዜ ይኖራል።ምግብ ከቤታችን ማይኖርባቸው ግዜያቶችም በርካታ ነበሩ።እኔ በጣም ጌታዬን አማርር ነበር አባቴ ግን ᐸᐸሁሉም ነገር ለኸይር ነው ጨለማው የፈለገውን ያክል ድቅድቅ ቢሆንም መንጋቱ ግን አይቀርም ይሄ የተፈጥሮ ህግ ነው።ጌታሽን ማማረር የለብሽም እሱ አንቺን ሲፈጥርሽ በምክንያት ነው።ደግሞ በድሎት ዱንያ ላይ እንድትኖሪ ሳይሆን እሱን እንድትገዢው ነው የፈጠረሽ።አንቺ እሱን በብቸኝነት ተገዝተሽ የጎደለሽን ለምኝው።እሱ ደግሞ ላንቺ የመረጠልሽን ይሰጥሻል >>ይለኛል ለኔ መንገር ብቻ ሳይሆን ለራሱም የሚያደርገው ነገር ነው።
በዚህ መልኩ እየኖርን ህይወት መልኳን መቀየር ጀመረች።አባቴ ብር ማግኘት ጀመረ።መጀመርያም የምንኖረው በራሳችን ቤት ነበር።በምን ገዛችሁት ድሀ አልነበራችሁ ትሉ ይሆናል።የአባቴ እናት ለአባቴ ያወረሱት ቤት ነው።አባቴ የተወለደው እዚሁ አዲስ አበባ ነው።እናም የቤት ኪራይ የለብንም።እኔም የምማረው አከባቢያችን በሚገኘው የመንግስት ት/ቤት ስለሆነ ምንም አይነት ወጪ አላስወጣም።እናም በዚህ ምክንያት አባቴ የተወሰነ ብር ማጠራቀም ቻለ።ብሩ በደንብ ሲጠራቀም የወንዶች ቡቲክ ነበር የከፈተው።በስራውም ውጤታማ ሆነ።ይህ ስራ ከብዙ ሰዎች ጋር አገናኘው።እና ስራውን ለማሳደግ ወደ ዱባይ እየሄደ የወንድም የሴትም ልብሶችን ማምጣት ጀመረ።እንዲህ እንዲህ እያለ ዱንያ ቤታችንን አንኳኳች።አባቴ በሩን ቢከፍትላትም ግን እስከነ ሸሯ እንድትገባ አልፈቀደላትም።ሸሯን ወደ ውጪ አሽቀንጥራ ጥሩ ነገሯን ይዛ እንድትገባ አደረጋት።ቤታችን ከጭቃ ቤት ወደ ዘመናዊ ቪላ ቤት ተቀየረች።እኔ ከመንግስት ትምህርት ቤት ወደ ግል ት/ቤት ተሸጋገርኩ።አባቴ ከባስ ወደ ቤት መኪና ተሸጋገረ።ግን አሁንም የተቸገረን መርዳቱን አልዘነጋውም።ረዥሙን የእረፍት ሰአቱን የቲሞችንና ሚስኪኖችን በመዘየር ነው የሚያሳልፈው።አላህ በነሱ ሰበብ ይህንን ሀብት እንደሰጠው ያምናል።ግቢያችን ውስጥ ተጨማሪ ሰርቪሶች አሉ።አባቴ እንደ መጋዘን ነው የሚጠቀምባቸው።
አባቴ ኸይር ስራው በዚህ አያበቃም።በየመስጂዱ እየዞረ ምንጣፍ የሚያስፈልገው ከሆነ ሲገዛ።ሽንት ቤት ከሌለው ሲያሰራ መታደስ የሚያስፈልገው ከሆነ ሲያሳድስ ይህንን ሲያደርግ ሀብቱም ይጨምር ነበር።በዚህ ግዜ አይንህን ላፈር ያሉት ዘመዶቹ ወደሱ ይጎርፉ ጀመር።አይ ሰው ይሄ ሁሉ አመት ይሙት ይኑር የማያውቁ ሰዎች ዛሬ ህይወቱ ሲያምር ሊያሽቃብጡ ይመጣሉ።አባቴም ምንም ሳይል የወንድምነት የዘመድነት ቦታቸውን ሳይነግፍቸው በፍቅር ተቀበላቸው።ቅርበታቸውን እያበዙት ሲመጡ እንዲህ ይሉት ጀመር።
ᐸᐸአንተ እኮ በዚህ ግዜ ማግባት ይኖርብሀል።ምክንያቱም ከስራ ደክመህ ስትመጣ ቤቱን አሟሙቃ የምትጠብቅህ ለልጅህም እናት የምትሆን ሴት ታስፈልግሃለች።እንዲሁም ይሄንን ሀብት የሚጠብቅ ወንድ ልጅ ያስፈልግሃል>>
ሲሉት አባቴ እንዲህ በማለት ያከሽፍባቸው ነበር።

"""""ክፍል ሁለት ይቀጥላል"""""
«ቶሎ እንዲቀጥል ጫን አርጓት»

ይቀላቀሉን ይቀላቀሉን

@Halal_Fonqaa @Halal_Fonqaa
1.1K views Cʀᴀᴢʏ ʟᴏᴠᴇ , 04:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 07:56:48 ‍ ​ ዳግማዊት ራህመት
ደራሲ ኢሳቅ ሀብታሙ
ክፍል ሁለት


እስክሰማሁ የጨነቀኝ የሀሰኔ ንግግር ጀመር ምን መሰለህ ሪዱ ራህመት ታፈቅርሀለች እንዳትነግርህ ፈራች በቃ የነገርኩህን በሚስጥር ያዘው አለኝ እንዴት እንደተደሰትኩ ወዲያው ነበር ለኤሊያስ የሰማሁትን የነገርኩት ኤሊያስ ማለት አብሮ አደግ ጓደኛዬ የማማክረው ወንድሜ ብዬ ብጠራው ይሻለኛል ኤሎ ብዬ ነው የምጠራው የነ ራህመቴ ክፍል ነው ሌቱ እጅግ ረዢም ነበር ቢሆንም ቀስ በቀስ ነጋልኝ ጉዞ ወደ ት/ቤት ራህመቴን እስከማያት ጨነቀኝ ከብዙ እንግልት ቡኃላ አይኔ እሷ ለይ አረፈ ልቤን ስራውን ጀመር የቀረብኳት ስመጣ የበለጠ ልቤ መምታት ጀመረ እስኪ ምላሴ ምን አለበት ከልቤ ብትማር ስራውን እንዴት አቀላጥፎ እንደሚሰራ ተመልከት ምላስም ተሳስሮ በነበረበት ሰዓት የራህመቴ ስራውን በመጀመሩ
አሰላሙ አለይኩም የሚል ለዛ ያለው ድምፅ ለመስማት በቃ
እኔም የተንቀጠቀጥኩ ወአለይኩመ ሰላም እንዴት ነሽ
ደህና አልሃምዱሊላህ አንተስ
ካንቺ ባይበልጥም አልሃምዱሊላህ ደና ነኝ
ደግሞ ጀመረህ ይሄ ነገርህ
የትኛው?
እሱን ተወውና ሰላት እንደማትሰግድ ሰማው ቁርሃንም መቅራት አቁመሃል ለምንድነው?
ያ ኤሊያስ ነው አይደል የነገረሽ?
ጥያቄዬን በጥያቄ አትመልስ እንደሁም ተወው ካሁን ቡኃላ አታናግረኝ
እረ ራሙ ይደብራል
ምኑ ነው የሚደብረው?ትስማኛለህ የማትሰግድ ከሆነ እንዳታናግረኝ ብላ ጥላኝ ሄደች አይ ያ አላህ የማታውን ደስታ ሳላጣጥም ወደ ሀዘን ይሁኑ የሱ ቀደር ነው እውነት ሰላት መጀመር አለብኝ አንደኛ ወደ ጌታዬ ያቃርበኛል ሁለተኛ ደግሞ ከራህመቴ ጋር እታረቃለሁ በዛው ቀን ሰላት ጀመርኩ ከሳምንት ቡኃላ ራህመቴ እኔ ጋር በመምጣት ሰላትና ቁርሃን መጀመርህን ሰማሁ ደስ ብሎኛል
ምክር በመቀበል አልታማም
ኢድ ጉረኛ
ለስድቡ አመሰግናለው
ስምኝማ የሆነ ነገር ልነገርሽ ነበር
ሪዱ በቃ ሌላ ጊዜ ትነግረኛለህ አሁን ጓደኞቼ የጠበቁኝ ነው ብላ ጥላኝ ሄደች እኔም ሆንኩ እሷ ልብ ያልልነው ነገር ለአራት ወራት እንደማንገናኝ ነበር ምክንያቱም ከነገ ጀምሮ የኛ ሞዴል ስለሆነ አሁን እንዴት ብዬ አራት ወር አይኗን የማላየው?ሌላ ከባድ ፈተና ቆይ አሁን ምን ላድርግ? ሰሞኑን ደግሞ ኤሊያስ ጥሩ ሁኔታ ለይ አይደለም እኔም ያፅናናውት ነው በምችለው መጠን ምን መሰላቹ የኤሊያስ እናት በጠና ታመሙ ዘመዶቻቸው ካፊር ነበሩና ፀበል አምጥተው ረጭዋቸው የአላህ ቀደር ሆነና መቆም ጀመሩ በዚያው ቅፅበት ክርስቲያን ሆኑ ሁለት ሴት ልጆቻቸውም ክርስትናን ተቀበሉ ኤሊያስና ታላቅ ወንድሙ ክርስትናን አንቀበልም ብለው ከቤት ወጡ አሁን ኤሊያስ እኛ ቤት ነው የሚኖረው የኤሊያስ እናት አሁን የበለጠ ታመዋሉ ኤሊያስ በየቀኑ ይዘይራቸዋል በሚችለውም አቅም ወደ እስልምና የተጣራ ነው አልሰማም አሉት እንጂ ኤሊያስ እኛ ከተፈተን ቡኃላ ነው ትምህራታቸው መከታተል ጀመረ ውስጡ ቢደማም ቢከብደውም በስተመጨረሻም ኤሊያስ ትምህርት ለማቆም ወሰነ ለሆነ ልጅ ብር አበድሮ ስለነበርና ብሩን ለመቀበል ትምህርት ቤት ሄደ ግን እኔ ከኤሊያስ ቤተሰብ የተረዳውት ነገር ቢኖር ልጆቻችንን የቤት ውስጥ ስራ ለይ ጊዜያቸውን የፈጀን ስለ ዲናቸው እንዳያውቁ ማድረጋችን ለዲናችን ትልቅ አደጋን ይዞ እንዲመጣ ያደርጋል አስቡት ኤሊያስ እና ታላቅ ወንድሙ ሳይከፍሩ እህቶቹ ጠቅላላ ሲከፍሩ አሁን ኤሊያስ በፈገግታ ታጅቦ ወደኔ መጣ ምን አገኝቶ ይሆን?

ክፍል ሶስት ይቀጥላል

ይ ላ ሉን share
┏━ ━━━━ ━┓
@Halal_Fonqaa
┗━ ━━━━ ━┛
1.1K views Cʀᴀᴢʏ ʟᴏᴠᴇ , 04:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ