Get Mystery Box with random crypto!

✞ ፍኖተ ጽድቅ ✞

የቴሌግራም ቻናል አርማ finote_tsidk — ✞ ፍኖተ ጽድቅ ✞
የቴሌግራም ቻናል አርማ finote_tsidk — ✞ ፍኖተ ጽድቅ ✞
የሰርጥ አድራሻ: @finote_tsidk
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.39K
የሰርጥ መግለጫ

👉ፍኖተ ጽድቅ
(የሕይወት መንገድ የጽድቅ ጎዳና)
በዚህ channel ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን የጠበቁ ትምህርቶች እና መዝሙሮች እንዲሁም ቅዱሳንን እንዘክራለን ስለቅዱሳን እንማማራለን ዕለታዊ ዜና ቤተ-ክርስቲያ ስንክሳር ግጻዌ ጥያቄና መልስ እንዲሁም በየእለቱ አጥንትን የሚያጠነክሩ መንፈስን የሚያለመልሙ ጽሁፎችን ወደ እናንተ እናደርሳለን፡፡
ቻናሉን ይቀላቀሉ
@finote_tsidk
ሼር ያርጉ!!

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-07 08:50:23 #ሰኔ_30

ዝ ክ ረ - ቅ ዱ ሳ ን


እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የልደት በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!!



የአምስት ዓመቱ ህጻን ባህታዊ ቅዱስ ዮሐንስ!
...........................................................................................................................
የዓለም ሁሉ ደስታ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ተወለደ
...........................................................................................................................
ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ለወላጆቹ የዘገየ የሚመስል ግን ወደር የማይገኝለት ታላቅ ስጦታ ነው።

ወላጆቹ ቅዱስ ዛካርያስና ቅድስት ኤልሳቤጥም በጸሎት የሚተጉ ዘወትር ከቤተ መቅደሱ የማይጠፉ ደጋግ ቅዱሳን ናቸው። ነገር ግን ልጅ ለምን አልተሰጠንም፣ ጥያቂችንም ለምን በፍጥነት መልስ አላገኝም ባንተ የማያምኑ በቤተ መቅደስህም ለጸሎት የማይቆሙ፣ እልፎች ልጅ ታቅፈው እኛን ለምን ከለከልከን ? ጸሎታችንንስ ለምን አልሰማህም ብለው በእግዚአብሔር ላይ አላጉረመረሙም።

እንዲያውም ቅዱስ ሉቃስ እንደሚነግረን የዘጠና ዓመቷ ኤልሳቤጥና የመቶ ዓመቱ ካህኑ ዘካሪያስ
"በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: ሉቃ 1÷6

እኛ ጠዋት ለምነን ማታ ካልሆነልን ብለን ስንት ዘመን አጉረምርመን ይሆን ?

ሁለቱ ቅዱሳን ግን ቢዘገይም የሚቀድመው የሌለ አምላካቸውን ሙሉ ዘመናቸው ሲያመሰግኑ ኖሩ።

እግዚአብሔርን ጠይቀነው፣ለምነነው ዝም ካለን እጅግ የተሻለ ውድ ነገር ሊሰጠን ነውና በትእግስት እንጠብቅ።

እስኪ አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ ቅዱስ ዮሐንስ የመሰለ ድንቅ ልጅ ለዓለም ሁሉ ደስታ የሚሆን ድንቅ ስጦታ ለመቀበል ዕድሜ ሰጥቶን 1000 ዓመትስ ብንጠብቅ ስ ? በደስታ እንጂ።

እስኪ ተመልከቱ ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ በስተ እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ ድንቅ ልጅ ሰጣቸው።

ያውም አስቀድሞ በነቢያት ትንቢት የተነገረለት ኢሳ 40:3 ሚል 3:1ዐ በቅዱስ ገብርኤል ከመወለዱ አስቀድሞ የተመሰከረለት ሉቃ 1÷14 በሗላም ጌታ ክርስቶስ " እውነት እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም " ማቴ 11:11 ብሎ የመሰከረለት ታላቅ ነቢይ ልጅ ተሰጣቸው።

ቅዱስ ዮሐንስ ገና በማህጸን ሳለ የአምላክ እናቱ የእመ ብርሃንን ድምጽ "ሰላምታ" በሰማ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ እናቱ ኤልሳቤጥ በምስጋና እርሱ ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘሏል (ሰግዷል)።

በቤተልሔም ህጻናት ላይ የሞት አዋጅ ሲታወጅ ቅዱስ ዮሐንስ 2 ዓመት ከ6 ወሩ ነበር።

" የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው ?" ብለው ሰብአ ሰገል በመምጣታቸው በእሥራኤል ምድር የሚገኙ ሕጻናትን
ክፉው ሄሮድስ አስገደለ። እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ...
" ከዚህ በኋላ ሄሮድስ ሰብአ ሰገል እንደ ተሣለቁበት ባየ ጊዜ እጅግ ተቆጣና ልኮ ከሰብአ ሰገል እንደ ተረዳው ዘመን በቤተ ልሔምና በአውራጃዋ የነበሩትን ሁለት ዓመት የሆናቸውን ከዚያም የሚያንሱትን ሕፃናት ሁሉ አስገደለ።" ማቴ 2:16 ።

ነገር ግን ትንሽ ቆይተው ክፉዎች አይሁድ ለሔሮድስ ስለ ቅዱሱ ሕጻን ስለ ዮሐንስ ነገሩት:: እንዲህ በማለት "ሲጸነስ የአባቱን አንደበት የዘጋ ሲወለድ ደግሞ የከፈተ 'ዮሐንስ' የሚባል ሕጻን አለና እሱንም ግደል" ብለው።

ይህንንም ዜና በእድሜዋ ማብቂያ ውድ ስጦታ የተሰጣት እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ሰማች። ወዲያውም ይዛው ሸሸች።

ቅዱስ ዘካርያስ ግን ካህን ነውና በቤተ መቅደስ መካከል አግኝተው ገድለውታል።

ወንድሞቼ ሆይ መላ ዘመንን ለእግዚአብሔርና ለቤተ መቅደሱ ታማኝ አገልጋይ ሆኖ እስከ ሞት ድረስ መታመን እንደምን መታደል ነው ?

ጌታ ሆይ እኔ ኃጢያተኛውን ልጅህን ለቤተ መቅደስህ ታማኝ አገልጋይ ሆኜ እኖር ዘንድ ፈቃድህ ትሁን ።

ቅድስት ኤልሳቤጥም በበረሃ ገዳመ ዚፋታ በተባለ ስፍራ ሕጻኑን እያሳደገች ለ5 ዓመታት አብራው ቆየች።
ነገር ግን ቅዱስ ዮሐንስ 5 ዓመት ሲሞላው እዚያው በበርሃ እናቱ ዐረፈች።ሰው የማኖርበት የሰውም ድምጽ በማይሰማበት አራዊት በሰለጠኑበት ዱር የቀኑ ሙቀት የሌሊቱ ግርማ በሚያስፈራበት በዚያ በስተርጅና የተሰጣትን ውድ ስጦታ ከሞት ለማትረፍ በዛለ ሰውነቷ በደከመ ጉልበቷ ተከራታ ከሰው ተለይታ በበረሃ የከተመችው እናቱ ገና በለጋነቱ እድሜ ህጻኑ ዮሐንስን እንደ ታቀፈች የሞት እንቅልፍ አሸለበች።

ይህ የአምስት ዓመት ህጻን በበረሃ ይሰማ የነበረው ድምጽ የእናቱ ብቻ ነበረ። አሁን ግን እርሱም የለም

በዚህ ጊዜ ሕጻኑ ዮሐንስ በበረሃ ውስጥ ምርር ብሎ አለቀሰ። የሚያስደንቀው ነገር እልም ባለው በረሃ በሀገረ እስራኤል በገዳመ ዚፋታ የተሰማው ለቅሶ...

አንድ ልጇን ሄሮድስ እንዳይገልባት የግብጽን በረሃ አቆራርጣ የአሸዋውን ግለት፣ የውሃውን ጥማት ችላ ግብጽ የወረደች እመ ብርሃን ቅድስት ድንግል ማርያም ስንት አገር አልፋ የህጻኑን ለቅሶ ሰማችው።

ያዘኑትን የምታረጋጊ የእኛ የልጆችሽ ለቅሶ ፈጥነሽ የምትሰሚ እመቤቴ ሆይ ዛሬም የኢትዮጵያ እናቶችን ለቅሶ ሰምተሽ መከራውን በቃ በይን።

ከዚያም እርሷም አንድ ልጇን ታቅፋ ስደት ላይ ነበረችና ከልጇ ከወዳጇ ጋር በደመና ፈጥና ከዮሐንስ ዘንድ ደረሰች።

አቅፋም አጽናናችው፣ ከዓይኖቹ የሚወርደውን እንባም አበሰችለት።

ልጇንም ከእኛ ጋር ይሆን ዘንድ "እንውሰደው ይሆን?" አለችው። ጌታችንም እናቴ ሆይ "ለአገልግሎት እስክጠራው እዚህ ይቆይ" አላት።
እመብርሃንም አጽናንታው፣ባርካው ተለያዩ።

ተመልከቱ ይህ አስደናቂ የአምስት ዓመት ህጻን ገና በህጻንነቱ የብህትውናን ህይወት ጀመረ።

የመጀመሪያው የአምስት ዓመት ህጻን ባህታዊ ሆነ

መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በዚያው በበረሃ የግመል ጠጉር ለብሶ፤ ጠፍር ታጥቆ ተባሕትዎውን ለ25 ዓመታት በዚያው ቀጠለ።

የብህትውናን ሕይወት በህጻንነት ዕድሜው በበረሃ የጀመረው ቅዱሱ የእግዚአብሔር ሰው በቆይታው በንጽሕና በቅድስና ሲኖር ከምድር አራዊትና ከሰማይ መላእክት በቀር ማንንም አላየም። ምን ይደንቅ ምን ይረቅ።

30 ዓመት ሆኖት እግዚአብሔር ከሰማይ ተናግሮ "ሒድ! የልጄን ጐዳና ጥረግ" እስካለበት ድረስ በዚያ ኖረ።

የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ በረከቱ ይደርብን !

ሼር በማድረግ ለሌሎች አዳርሱ!!
@finote_tsidk
@finote_tsidk
67 viewsedited  05:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 08:46:30
60 views05:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 15:50:06 "ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ሁሉ የክርስቶስንም ፀጋና ክብር ሳይፈተኑ ማግኘት አይቻልም የዚህ ዓለም ፈተናና እሳት ቶሎ ያልፋል ይጠፋል ኃጢያተኞች የሚገቡበት የገሀነም እሳት ግን ለዘላለም እንደ ነደደ ይኖራል።"
#ቅዱስ_ሚናስ
103 views12:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 15:50:06 "ዛሬን ለሰይጣን ነገን ደግሞ ለእግዚአብሔር አትስጡ!"
ታላቁ ቅዱስ ጎሮጎርዮስ
104 views12:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 16:20:56
160 views13:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 16:45:51 ዘ መ ነ - ክ ረ ም ት
----------------------------------
በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ወቅቶች በአራት ይከፈላሉ። በቅዱስ ያሬድ የዜማ መጻሕፍት፣ እንደዚሁም በመጽሐፈ ግጻዌ እንደ ተገለጸው እነዚህም፡- ዘመነ መጸው (መከር)፣ ዘመነ ሐጋይ (በጋ)፣ ዘመነ ጸደይ (በልግ) እና ዘመነ ክረምት ይባላሉ፡፡

ከአራቱ ወቅቶች መካከል ከሰኔ ፳፭ እስከ መስከረም ፳፭ ቀን ድረስ ያለው ጊዜ (አሁን የምንገኝበት ወቅት) ዘመነ ክረምት ተብሎ ይጠራል፡፡

በአተ ክረምት (የክረምት መግብያ)
በዘመነ ክረምት መጀመርያ (መግብያ) ሳምንት በቤተ ክርስቲያናችን የሚቀርበው የቅዱስ ያሬድ መዝሙር የሚከተለው ነው፤
‹‹ደምፀ እገሪሁ ለዝናም ሶበ ይዘንም ዝናም ይጸግቡ ርኁባን ደምፀ እገሪሁ ለዝናም ሶበ ይዘንም ዝናም ይትፌሥሑ ነዳያን ደምፀ እገሪሁ ለዝናም ወሠርዐ ሰንበተ ለሰብእ ዕረፍተ ደምፀ እገሪሁ ለዝናም ደምፀ እገሪሁ ለዝናም››
የመዝሙሩ ቀጥተኛ ትርጕም፡-
‹‹የዝናም ኮቴው ተሰማ፡፡ ዝናም በሚዘንም ጊዜ የተራቡ ይጠግባሉ፡፡ የዝናም ኮቴው ተሰማ፡፡ ዝናም በሚዘንም ጊዜ ድሆች ይደሰታሉ፡፡ የዝናም ኮቴው ተሰማ፡፡ አምላካችን ለሰው ልጅ ዕረፍት ሰንበትን ፈጠረ፡፡ የዝናም ኮቴው ተሰማ፡፡ የዝናም ኮቴው ተሰማ፡፡››

ይህ መዝሙር ከሰኔ ፳፮ ጀምሮ ያለው ወቅት ክረምቱ የሚገባበት እና ዝናም በብዛት የሚጥልበት ጊዜ መኾኑን የሚያበሥር ሲኾን፣ በተጨማሪም ዝናም በሚዘንብበት ጊዜ የሚበቅለውን እኽልና የምንጮችን መብዛት ተስፋ በማድረግ የተራቡ እንደሚጠግቡ፤ የተጠሙም እንደሚረኩ የሚያትት ምሥጢር ይዟል፡፡ እንደዚሁም ጊዜ ለበጋ፣ ጊዜ ለክረምት የሚሰጥ አምላክ ለሰው ልጅ ማረፊያ ትኾን ዘንድ ዕለተ ሰንበትን መፍጠሩንም ያስረዳል፡፡

‹‹ዘይገለብቦ ለሰማይ በደመና ወያስተዴሉ ክረምተ ለምድር ዘያበቍል ሣዕረ ውስተ አድባር፡፡››መዝ ፻፵፮፥፰
ትርጕም፡- ‹‹ሰማዩን በደመና የሚሸፍን፣ ለምድርም ዝናምን የሚያዘጋጅ፣ ሣርን በተራሮች ላይ የሚያበቅል እርሱ ነው፡፡››

እግዚአብሔር ሰማዩን በደመና የሚሸፍን፤ ዝናምንም (ክረምትን) ለምድር (ለሰው ልጅ) የሚያዘጋጅ፤ እንደዚሁም በተራሮች ላይ ሣርን (ዕፀዋትን) የሚያበቅል አምላክ መኾኑን ያስገነዝባል።

ሼር በማድረግ ለሌሎች ያካፍሉ!!
@finote_tsidk
@finote_tsidk
211 viewsedited  13:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 13:18:07 ❖ አንድ " ግዩር " እንዲህ ይመክራል ❖

ሥለ እግዚአብሔር ብለን ሰውን እንውደድ እንጅ ስለ ሰው ብለን እግዚአብሔርን መውደድ አይገባንም። በእግዚአብሔር ፊት ሰውን መውደድህን ይገለጥልህ እንጅ በሰው ፊት የእግዚአብሔር ወዳጅ ለመምሰል ብለህ የምትኖር አትሁን። ለሰዎች ብለህ እንደወደድከው ለሰዎች ብለህ ልትጠላው ትችላለህ እና።
----------------------------------------------------------------
የእግዚአብሔር ሰው መሆን ማለት እግዚአብሔርን መመገብ እንጅ እግዚአብሔርን ማወቅ አይደለም። ለመዳን ብለህ እወቅ እንጅ በእውቀትህ የምትድን አይምሰልህ። የማታውቀውን የምታውቀው ልትኖረው እንጅ እውቀቱ በክርስቶስ ቀኝ ሊያቆምህ አይምሰልህ። በጎ ነገርን ያወቅሃት ዕለት ብቻ ደስ አይበልህ፥ የሠራሃት ዕለት እንጅ፥ በመሥራትህም አትመካ አልፈጸምካትምና። ከእግዚአብሔር ያወቅሃትን መልካም ነገር ወዲያው ሥራት፥ እየሠራሃት ያለችህን መልካም ነገር አትልቀቃት። እየኖርክ ተማር እንጅ እየተማርክ ብቻ ዘመንህን እንዳትፈጽም ተጠንንቀቅ። ያለ ዕውቀት ብትኖር ከፍርድ የምታመልጥ አይደለምና መቼም ቢሆን ከቤተክርስቲያን ጉባዔያት አትታጣ፥ በማወቅህ ፍርድ አይቀርልህምና ያወቅኸውን ፈጥነህ ሥራ።

ብቻየን ለፋሁበት ብለህ ገንዘብህን ብቻህን አትጨርሰው። ከምታገኘው ሁሉ ለመድኀኔዓለም ድርሻ አስቀምጥ። የለመነህን ሰው አትመርምረው ቢቻልህ ስጠው ባይቻልህ እዘንለት እንጅ። ለስንፍናህ ሁሉ ምክንያት አታብጅለት። መልካሙን ነገርም ዛሬ ሥራው፥ ክፉውን ነገርም ዛሬ ተናዘዘው። #እያንዳንዱ_የጊዜ_ሽርፍራፊ_የገነት_የሲዖል_ሰው_ለመሆንህ_ዋጋ_እንዳለው_እወቅ።


#ይቆየን
መልካም የሆነ እግዚአብሔር ለመልካም የሚሳብ መልካምን የሚያደርግ በመልካሞ የሚጸና በጎ ሕሊና ይስጠን!!!

✞ መልካም እለተ ሰንበት ✞

ሼር በማድረግ ለሌሎች ያካፍሉ!!
@finote_tsidk
@finote_tsidk
236 viewsedited  10:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 15:07:20 + አይዞህ አልነካህም +

ይህ የብዙዎቻችን የልጅነት ታሪክ ነው::

ጥፋት አጥፍተሃል:: ወላጆችህን በጣም የሚያስቆጣ ጥፋት ነው:: ወይ ውድ ዕቃ ሰብረሃል:: ወይ አንዳች በጣም የሚጠሉትን ነገር ሠርተሃል:: አለዚያም አድርግ ተብለህ ሳታደርገው የቀረኸው ነገር አለ::

ወላጆችህ ያጠፋኸውን ቢያውቁ ምን ሊያደርጉህ እንደሚችሉ እያሰብህ ተጨንቀሃል::
"አባዬ ዛሬ ገደለኝ"
"እማዬ በጥርስዋ ነው የምትዘለዝለኝ"
"ዛሬ መሞቴ ነው" እያልህ በፍርሃት ውስጥ ነህ::
ስለዚህ ተደብቀሃል::

መደበቅህን ሲያውቁ ወላጆችህ የሆነ ነገር ጠረጠሩ::

"ምን ሆነህ ነው አንተ?"
"ምንም"
"ታዲያ ምን ያርበተብትሃል"
"ምንም"
"ተናገር እንጂ"
ራስህን ወዘወዝህ እንጂ አልተናገርክም::

አባት ቀረብ ይልና
"አይዞህ የኔ ልጅ ምንም አልልህም አልገርፍህም ንገረኝ" እያለ ማባበል ይጀምራል:: ይሄን ጊዜ ለመናገር እያመነታህ ትቁለጨለጫለህ::

አባትም ነገሩ ይገባውና :-
"እኔ እኮ እውነት እንድትነግረኝ ብቻ ነው የምፈልገው:: ሐቁን ከነገርከኝ አልነካህም:: እኔ የማልወደው ውሸት ብቻ ነው" ይልሃል::

ይሄን ጊዜ እየተቅለሰለስክ በሹክሹክታ ጥፋትህን ትናዘዛለህ::

"አያትህ የሠጡህን የሸክላ ጌጥ እኮ ሰበርኩት"

"ለትምህርት ቤት ክፈል ብለህ የሠጠኸኝን ብር ጣልኩት" ወዘተ ብለህ ትዘረግፈዋለህ::

ተናግረህ ስትጨርስና ፊትህ ላይ የመብረቅ ድምፅ ስትሰማ እኩል ይሆናል:: የአባትህ ጥፊ ነው::

"ሥራህን አውቀህ ነዋ የተደበቅከው!? ኸከከከከ"

ሌላ ቀን ከተገረፍከው የላቀ ግርፊያ ይወርድብሃል:: "አይዞህ ያጠፋኸውን ንገረኝ አልነካህም" የሚል ቃል ዋጋ እንደሌለው ትረዳለህ::

ያጠፋኸውን ንገረኝ ብሎ ስትናዘዝ የሚምርህ አባት እግዚአብሔር ብቻ ነው::

"በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው" 1 ዮሐ. 1:9

#ዲያቆን_ሄኖክ_ኃይሌ

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን አጥብቃችሁ ስለ እኔ ጸልዩልኝ!
በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)

ሼር በማድረግ ለሌሎች ያካፍሉ!!
@finote_tsidk
@finote_tsidk
194 views12:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 16:57:45 #ሰኔ_24


ዝ ክ ረ - ቅ ዱ ሳ ን


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
አሐዱ አምላክ አሜን!!!


እ ን ኳ ን - አ ደ ረ ሳ ች ሁ!



✞ ኢትዮጵያዊው ቅዱስ አባ ሙሴ ጸሊም ✞


ሰኔ ሃያ አራት በዚች ቀን አባ ሙሴ ጸሊም በሰማዕትነት ሞተ። ሰዎች ከገድሉ የተነሣ ይህን ቅዱስ ያደንቁታል እርሱ አስቀድሞ መንግሥተ ሰማያትን ገፍቷት ነበረና እርሱ በሥጋው ጠንካራ በሥራውም ኃይለኛ ነበር ይበላና ይጠጣ ይቀማና ያመነዝር ነበር ይገድልም ነበር ማንም ሊቋቋመው አይችልም ነበር።

አንድ በግ በአንድ ጊዜ ጨርሶ እንደሚበላና አንድ ፊቀን ወይን ጠጅ እንደሚጠጣ ስለ እርሱ ተነግሮአል። እርሱም ፀሐይን ለሚያመልኩ ሰዎች አገልጋይ ነበረ ብዙ ጊዜም ወደ ፀሐይ እያንጋጠጠ ፀሐይ ሆይ አንተ አምላክ ከሆንክ አነጋግረኝ ይል ነበር ደግሞም በልቡ የማላውቅህ ሆይ ራስህን አሳውቀኝ ይል ነበር።

ከዚህም በኋላ በአስቄጥስ ገዳም ያሉ መነኰሳት እግዚአብሔርን ያውቁታል ያዩታልም እያሉ ሲነጋገሩ ሰዎችን ሰማቸው። ያን ጊዜም ተነሣ ሰይፉንም ታጥቆ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔደ በደረሰም ጊዜ አባ ኤስድሮስን አገኘው። አባ ኤስድሮስም ፈራው ሙሴ ጸሊምም እውነተኛውን አምላክ ታሳውቁኝና ታስረዱኝ ዘንድ ወደ እናንተ መጣሁ አለው። አባ ኤስድሮስም ወደ አባ መቃርስ ወስዶ አገናኘው።

እርሱም ተቀብሎ ሃይማኖትን አስተማረው እንዲህም አለው ታግሠህ የማስተምርህን ከጠበቅህ እግዚአብሔርን ታየዋለህ። ከዚህም በኋላ የክርስትና ጥምቀትን አጥምቆ አመነኰሰው ከብዙዎች ገድለኞች ቅዱሳን ይልቅ ብዙና ጽኑዕ ገድልን መጋደል ጀመረ።

ሰይጣንም ቀድሞ ሲሠራው በነበረ በመብሉና በመጠጡ በዝሙቱም ይዋጋው ነበረ እርሱም በራሱ ላይ የሚደርስበትን ሁሉ ለአባ ኤስድሮስ ይነግረው ነበር እርሱም አጽናንቶ ሊሠራው የሚገባውን ያስተምረው ነበር።

ከገድሉ ብዛትም የተነሣ አረጋውያን መነኰሳት በሚተኙ ጊዜ ቤቶቻቸውን በመዞር ውኃ መቅጃዎችን ወስዶ ውኃ መልቶ በየቤታቸው ደጃፍ ያኖር ነበር። ውኃው ከእነርሱ ሩቅ ነበረና እንዲህም እያደረገ በመጋደል ለብዙ ዘመናት ኖረ።

ሰይጣንም በእርሱ ቀንቶ በእግሩ ውስጥ አስጨናቂ የሆነ አመታትን መታው ተኝቶም እየተጨነቀ ብዙ ቀን ታመመ። ከዚህም በኋላ የመታውና የሚፈታተነው ሰይጣን እንደሆነ ዐውቆ ሥጋው በእሳት ተለብልቦ እንደ ደረቀ ዕንጨት እስቲሆን ድረስ ተጋድሎውንና አገልግሎቱን አበዛ። እግዚአብሔርም ትዕግስቱን አይቶ ከደዌው ፈወሰው የሰይጣንንም ጦር ከእርሱ አራቀለት የመንፈስ ቅዱስም ጸጋ አደረበት ወደርሱም አምስት መቶ ወንድሞች መነኰሳት ተሰበሰቡ በእነርሱም ላይ አበ ምኔት ሆነ።

ከዚህ በኋላ ቅስና ሊሾሙት መረጡት በቤተ መቅደስም በሊቀ ጳጳሳቱ ዘንድ በአቆሙት ጊዜ ሊቀ ጳጳሳቱም አልፈቀደም ነበር አረጋውያኑንም ይህን ጠቋራ ለምን አመጣችሁት ከዚህ አውጡት አላቸው እርሱም መልክህ የከፋ ጠቋራ ሆይ መልካም አደረጉብህ በማለት ራሱን እየገሠጸ ወጣ ከዚህ በኋላ ዳግመኛ ሊቀ ጳጳሳቱ ጠራውና እጁን በላዩ ጭኖ ቅስና ሾመው እንዲህም አለው ሙሴ ሆይ እነሆ በውስጥም በውጭም ሁለመናህ ነጭ ሆነ።

በአንዲትም ዕለት ቅዱሳን አረጋውያን ወደርሱ መጡ በእርሱም ዘንድ ውኃ አልነበረም እርሱም ከበዓቱ ብዙ ጊዜ ወጣ ገባ ይል ነበር ከዚህ በኋላም ብዙ ዝናም ዘንሞ ጕድጓዶችን ሁሉ ሞላ። አረጋውያንም ለምን ብዙ ጊዜ ወጣ ገባ ትል ነበር ብለው ጠየቁት እርሱም እግዚአብሔርን ውኃ ካልሰጠኸኝ ቅዱሳን አገልጋዮችህን ምን አጠጣቸዋለሁ እለው ነበር በቸርነቱም ዝናምን ልኮልን ውኃን አገኘን አላቸው።

በአንዲትም ዕለት አባ ሙሴ ከአረጋውያን ጋራ ወደ አባ መቃርስ ሔደ አባ መቃርስም የሰማዕትነት አክሊል ያለው ከእናንተ ውስጥ አንዱን እነሆ አያለሁ አላቸው አባ ሙሴም አባቴ ሆይ ምናልባት እኔ እሆናለሁ በሰይፍ የገደለ በሰይፍ ይገደል ዘንድ አለው የሚል ጽሑፍ አለና ብሎ መለሰ።

ከዚህም በኋላ የበርበር ሰዎች መጡ አባ ሙሴም ከእርሱ ጋራ ያሉትን መነኰሳት እነሆ የበርበር ሰዎች ደረሱ መሸሽ የሚፈልግ ይሽሽ አላቸው እነርሱም አባታችን አንተስ አትሸሽምን አሉት እርሱም በሰይፍ የገደለ በሰይፍ ይገደላል ስለሚለው የእግዚአብሔር ቃል እነሆ ያቺን ቀን ለብዙ ዘመናት ስጠብቃት ኖሬአለሁ አላቸው።

ወዲያውኑም የበርበር ሰዎች ገብተው በሰይፍ ገደሉት መሸሽ ስለ አልፈለጉ ከእርሱ ጋራ ሰባት መነኰሳትም ተገደሉ አንዱ ግን ከምንጣፍ ውስጥ ተሠወረ የእግዚአብሔርንም መልአክ አየ በእጁም አክሊል ነበር እርሱም ቆሞ ይጠብቅ ነበር። ይህንንም በአየ ጊዜ ከተሠወረበት ወጣ የበርበር ሰዎችም ገደሉት የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበለ።

ወንድሞች ሆይ ከሀዲና ነፍሰ ገዳይ ቀማኛና ዘማዊ የነበረውን ለውጣ ደግ አባት መምህርና የሚያጽናና ለመነኰሳትም ሥርዓትን የሠራ ካህን እንዳደረገችው በሁሉም አብያተ ክርስቲያን ስሙ እንዲጠራ እንዳደረገችው የንስሐን ኃይሏን ተመልከቱ። ሥጋውም በአስቄጥስ ገዳም ደርምስ በተባለ ቦታ ለዘላለም ይኖራል ከእርሱም ብዙዎች ድንቆችና ተአምራት ይታያሉ።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

-------------------------------------------------------------
መቶ በግ ያለው ከእነርሱም አንዱ ቢጠፋ፥ ዘጠና ዘጠኙን በበረሃ ትቶ የጠፋውን እስኪያገኘው ድረስ ሊፈልገው የማይሄድ ከእናንተ ማን ነው?
ባገኘውም ጊዜ ደስ ብሎት በጫንቃው ይሸከመዋል፤
ወደ ቤትም በመጣ ጊዜ ወዳጆቹንና ጐረቤቶቹን በአንድነት ጠርቶ። የጠፋውን በጌን አግኝቼዋለሁና ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ ይላቸዋል።
እላችኋለሁ፥ እንዲሁ ንስሐ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል።
(ሉቃ 15፥ 4-7)


#ስንክሳር_ዘወርኀ_ሰኔ

✟ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✟

ሼር በማድረግ ለሌሎች ያካፍሉ!!
@finote_tsidk
@finote_tsidk
189 viewsedited  13:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 13:45:45 "የበኩር ልጅዋን እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም " ለምን አለ ? ማቴ 1:25

አላወቃትም ማለቱ አዳም ከገነት ከወጡ በሁዋላ ሄዋንን እንዳወቃት አወቃት ማለት ሳይሆን እመቤታችን አምላክ በማህፀንዋ ሳለ የእመቤታች መልኳ ይለዋወጥ ስለነበር በውስጧ ይህ ነው የማይባል ህብር እና ቀለሙ የማይነገርለት እሳተ መለኮት ክርስቶስ እርሱ መልኩን በለወጠ ቁጥር እርሷንም ይለውጥ ነበርና ነው ፤ ለምሳሌ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን በደብረ ታቦር ሲገለጥ ፊቱም ልብሱም አጣቢ ከሚያነፃው በላይ ነጭ ሆነ ። ይህንንም በማህፀንዋ ሊያደርገው ቻለ ምክንያቱም ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና ። ስለዚህ የእመቤታችን ፊትዋ ብርሃን ሲሆንበት ዮሴፍ ይህች ማናት ብሎ ግራ ይገባው ነበር

ስለዚህ እስክትወልድ ድረስ የፊትዋን ብርሃን በማየት አላወቃትም ስትወልድ ግን በማህፀኗ ሆኖ ፊትዋን የሚለውጠው ጌታ ተወልዷልና አወቃት

#1ኛ. በኦሪ.ዘፀ 34:35 - 39 እንደ ተፃፈው ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር ተነጋግሮ ሲመለስ ፊቱ እንደ ጸሀይ ያበራ ስለነበር አሮንና ህዝቡ ስለፈሩ ፊቱን ይሸፈን እንደ ነበር እናነባለን እንዲሁም ጸጋንና ኃይልን ተመልቶ ሳይፈራ በአይሁድ ሸንጎ ፊት ስለጌታ የመሰከረው ቅዱስ እስጢፋኖስ "በሸንጎም የተቀመጡት ሁሉ ትኩር ብለው ሲመለከቱት እንደ መልአክ ፊት ሆኖ ፊቱን አዩት " ተብሎ ተነግሮለታል የሐዋ 6:15 ስለዚህ ሙሴ በእግዚአብሔር ፊት በመቆሙ ፊቱ ካንፀባረቀ ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስም ፊቱ የመልአክን ፊት ከመሰለ ፤ ሁሉን የፈጠረ እግዚአብሔር ወልድን በማህፀኗ የተሸከመች እመቤታችን ከወትሮው ሁኔታ የመልኳ መለወጥ የገጿ መንጸባረቅ ይህም ለዮሴፍ እንግዳ መሆኑ የተገባ ነው ስለዚህ እስክትወልድ ድረስ እርሷ ወላዲተ አምላክ ልጇም አምላክ ወልደ አምላክ መሆኑን አላወቀም ነበር

#2ኛ.ጌታ ሲወለድ የተደረገውን ተአምራት ተመልክቶ ማለትም፦
#ሀ.ሰብአ ሰገል እጅ መንሻ ወርቅ ፣ ዕጣን ፣ ከርቤ ይዘው በመምጣት ሰግደው መገበራቸውን
#ለ.የኮከቡ ሰብአ ሰገልን መርቶ ማምጣት
#ሐ.የእግዚአብሔር ክብር በቤተልሔም ዙሪያ ማብራት
#መ.የቅዱሳን መላእክት ዝማሬና የቤተልሔም አካባቢ በአእላፍ መላዕክት መሞላት
#ሠ.የእረኞች መጎብኘትና ምስክርነት ማቴ2:1-12 ሉቃ
2:5-14
ስለዚህ እስክትወልድና ይሄን እስኪያይ ድረስ እርሷ ወላዲተ አምላክ ልጇም አምላክ ወልደ አምላክ መሆኑን አላወቀም ነበር

#3ኛ.እንደ መናፍቃኑ አተረጓጎም #አላወቃትም የሚለውን ቃል በቀጥታ እንኳን ብንመለከተው " እስክትወልድ ድረስ " ማለቱ ከወለደች በሁዋላ አወቃት ብሎ ለመደምደም አይቻልም ። ምክንያቱም በዕብራይክጡ #እስከ ወሰን ድንበር የሌለው ፈጽሞ ከቶ ማለት ይሆናልና ። ለዚህም ማስረጃ እንይ ፦
#ሀ."የሳኦል ልጅ ሜልኮል እስከሞተችበት ቀን ድረስ ልጅ አልወለደችም " 2ኛሳሙ 5:23 ይላል ። ታዲያ ይህ ሜልኮል ፈፅሞ አልወለደችም ማለት እንጂ ከሞተች ቡሃላ በመቃብር ወለደች ማለት አይደለም
#ለ.ቅዱሳን ሐዋርያትን "እኔ እስከ ዓለም ፍፃሜ ድረስ ከእናንተ ጋር ነኝ " ማቴ 23:19 ብሏቸዋል ይህ ማለት ከዚያ ቡሃላ ይለያቸዋል ማለት አይደለምና እመቤታችንም "የበኩር ልጅዋን #እስከምትወልድ ድረስ አላወቃትም " ማለት ፈፅሞ በእደ ዮሴፍ አልተዳሰሰችም ለዘለዓለም ድንግል ናት እርሷም ወንድ ሳላውቅ እንዴት ይሆንልኛል እንዳለች ወንድ አታውቅም ማለት ነው

ሼር በማርግ ለሌሎች ያጋሩ!
@finote_tsidk
@finote_tsidk
192 views10:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ