2022-05-20 21:45:47
ፅናት
ክፍል 36
ደራሲ ቤዛዊት ፋንታዬ (የሸዋ ልጅ)
.
.
.፨ ሶስናም "ሰውየው የያቤፅ አባት እንደሞተ ነበር የነገረኝ። ከያቤፅ አባት ይልቅ
ይበልጥ እሳቸው ስለሚቀረቡኝ በመሞታቸው በጣም አዝኜ ነበር። የያቤፅ
አባትም በጣም በጣም አዝኖ ነበር። ለቅሷውን በሙሉ የያቤፅ ሴት አያቱ እኛ
ቤት አሳለፉ ከዛ ግን የያቤፅ አያትን የገደሏቸው የገዛ ባለቤታቸው እንደሆነ
ስለተደረሰበት እሳቸው ታሰሩ። በዛ ትልቅ ቤት ውስጥ እኔ፣
የያቤፅአባት፣ሰራተኞቹን እና ያቤፅ መኖር ጀመረን። ልጄ እያደገ ሲመጣ ከሰው
የተለየ ፀባይ እየያዘ መጣ። በእኔ በኩል የልጄ ፀባይ እና ነፃነቱ ችግር ያለው
መስሎ አልታየኝም ነገር ግን አባቱ እና የሚያውቁት ሰዎች ልጅሽ አብዶል
ይሉኛል።
፨ ያው እንደነገረኩሽ ልጄ በጣም ግልፅ ነው። አንድ ቀን የያቤፅ አባትን እኔ ስራ
በጣም እየበዛብኝ እንደሆነ እና እንዲያግዘኝ ጠየኩት። የያቤፅ አባት ግን
"ስታስቢው እኔ ብማር ዝም ብዬ እቀመጣለሁ?" አለኝ። ያኔ ነበር እንዳሰተማረ
የገባኝ። ምንም አላልኩትም በነጋታው ስራ እየሰራው ፀሀፊዬ አንድ ፖሰታ
አመጣችልኝ ግራ ተጋብቼ ከፈትኩት። የያቤፅ አያት ፊርማ ነበረበት።
ወረቀቱ ላይ እኔ በጣም ጎበዝ ሰራተኛ እና የልጅ ልጃቸው እናት በመሆኔ
የድርጅቱን ግማሽ እንደሰጡኝ የሚገልፅ ነበር። ንብረት እና ሀብት ላይ ሳይሆን
ክብር እና መሪነት ላይ ልቤ ስላለ ስለ ሰጡኝ ንብረት ሳይሆን ክብር እጅግ
በጣም ደስ አለኝ። ያው ስራዬን በሞራል መስራቴን ቀጠልኩ። ልጄም ስኬታማ
ተማሪ ስለነበር በጣም ደስተኛ ነበርኩኝ ምክንያቱም ልጄ እኔን ይሰማኛል እና
ደሞ በትምህርቱም በእኔ ነው የወጣው የያቤፅ አባት እኔን ማውራት አቆመ
ምክንያቱን ግን አላውቅም ነበር።
፨ በእዚህ መልኩ ልጃችን አደገ እና የ12ተኛ ክፍልን በድል አጠናቆ ዩንቨርስቲ
ሊገባልኝ ነው ብዬ ደስ ሲለኝ ልጄ ጥሎኝ ሄደ። የያቤፅ አባትም ስራተኞችን
አባረራቸው በዛ ቤት ውስጥ እኔ እና የያቤፅ አባት መኖር ጀመረን። አንድም ቃል
ግን እሱም እኔም አንድም ቃል አውጥተን ተነጋግረን አናውቅም። ለመጨረሻ ጊዜ
ያወራኝ ያቤፅ 4 አመቱ እያለ ነው። እኔ እና ልጄ የእኔን እና የልጄን ልደት መኝታ
ቤታችን እናከብር ነበር።የቤቱ ሰራተኞችም እንዲገኙ አልፈልግም ነበር። ለምን
እንዳትሉኝ ምክንያቱም መልስ የለኝም። እና ልጄ ሲሄድ ቤት ከስራ ስመለስ እሱን
ማጣቱ ጎዳኝ። ስራ መስራትም አልቻልኩም ልጄን ፈለኩት ግን ላገኘው
አልቻልኩም የያቤፅ አባት ግን ልጅሽን አመጣልሻለው ብሎ አታለለኝ ይቅርታም
ጠየቀኝ።
፨ በጣም ገረሞኛል ለውጡ ምግብም እሱ ይሰጠኝ ነበር፤ በጣም
ይንከባከበኝም ነበር። ለካ በሚሰጠኝ ምግብ እና መጠጥ ላይ አይምሮን
የሚያዛባ መዳኒት እየጨመረ ነበር የሚሰጠኝ እየቆየ ለእራሴ እየታወቀኝ መጣ
ወደ ማበዱ ሄድኩኝ። የያቤፅ አባትም ፈገግ ብሎ ወደ ጆሮዩ እየተጠጋ አንቺ እና
ልጅሽ አበዳቹ አደል ይለኛል። የሚሰጠኝ መድሀኒት ወደ ሰውነቴ ተሰራጭቶ
ከተላመድኩት በኋላ ያለ መዳኒቱ መቆየት አቃተኝ።መዳኒቱን ካልዋጥኩኝ
ልገልፀው እማልችው አሰቃቄ ህመም ይስማኝ ነበር። ይህንን የያቤፅ አባት ነው
የነገረኝ። የሆነ ቀን አንድ ወረቀት አምጥቶ እዚህ ጋር ካልፈረምሽ መዳኒቱን
አልሰጥሽም አለ። አልፈረምም ምን ልታረግ ነው ደረሻዬን ልትወስድ ድርሻዬ
የልጄ ነው ስለው" አለችና እሪሪሪሪ አለች። ያቤፅ ምንም አልተነፈሰም ፅናትም
እንደዛው
ሶስና ለቅሶዋን ስጨረስ እራስዋን አረጋግተታ ወሬዋን ቀጠለች "እሱ ዝም
ብለሽ ካልፈረምሽ መዳኒቱንም አልሰጥሽም ልጅሽንም እገድለዋለሁ አለኝ።
ልጅሽ አትበል ያንተም ልጅ እኮ ነው አልኩት እሱ ግን ጥሩ ብሎ ሄደ።በጩኸት
ተጣርቼ እሺ አልኩት እና ፈረምኩኝ አይኔ ብዥታ ላይ ስለነበር በጭራሽ ሊነበበኝ
አልቻለም። የፊርማ ቦታውን እጄን አስይዞ ነበር ያሳየኝ።
፨ በነጋታው ደሞ ከቤቱ አስወጥቶ አንድ ትንሽ ሱቅ ውስጥ አስገባኝ። ከዛ
የምወስደውን መዳኒት እየመጣ ይሰጠኛል ሙሉውን አይሰጠኝም አንድ አንድ
ፍሬ ነበር የሚሰጠኝ ምክንያቱም ወደ ልጄ እንዳልጠጋ ማስፈራሪያው አረጎ
መዳኒቱን ስለሚሰጠኝ በዛ መልኩ ነበር እኔ የትንሽዬ ሱቅ ባለቤት የያቤፅ አባት
ደሞ የዛ ትልቅ ድርጅት ባለቤት ሆኖ ያገኘውት። ወደ ድርጅቱ ሄጄ ነበር ግን ደሞ
ድርጅቱ ውስጥ እንዴት እንደሆነ ባለቅም የያቤፅን አባት አስተዳዳሪ እና ዋና ሆኖ
አገኘውት። ቢሮዬ ወንበር ላይ ቁጭ ብሎ የልጄን ፎቶ እና የኔን አውርዶ እማይረባ
ስእል ለጥፎበታል
ምንም ቃል አላወጣም ትልቅ ዶክሜንት ስጠኝ። አገላብጭኤ በቁሜ አየውት
የሙሉ ንብረቱ ባለቤት እንደሆነ የሚገልፁ ነገሮች ነበሩ ያነበብኩት።እኔም ቃል
ሳላወጣ ከእዛ ድርጅት ወጣው። በምን ጭንቅላቱ ያንን ድርጅት እንደሚመራው
ግን አላውቅም እኔም ሁሉን ትቼ ሱቅ ውስጥ መሸጥ ጀመረኩኝ።
፨የሆነ ቀን አንድ ሰው ሱቄ ፊት ለፊት ተኝቷል ሮጬ ከሱቄ ወጣውና ልክ
የተኛው ሰው ጋር ልደረስ ስል የያቤፅ አባት ከየት እንደመጣ እኔ ባላውቅም
መጥቶ ጎትቶ ወደ መኪናው አስገባኝና የተኛው ያበደው ልጅሽ ነው ነገር ግን ወደ
እሱ ደግመሽ ብትጠጊ አንቺንም ልጅሽንም እገድላቸዋለሁ መዳኒትሽንም
አልሰጥሽም ከዛ ትሞቻለሽ ያኔ ለልጅሽ እነግረዋለሁ እና እሱም ይሞታል አለኝ።
ምክንያትክ ምንድነው አልኩት እሱም ምክንያቱም ከተገናኛቹ ተባብራቹ
ስለምታጠፉኝ ልበልሽ ለማንኛውም እምልሽን ካልሰማሽ ያልኩን እንደማረግ
አትጠራጠሪ ልጄን እኔ እንከባከባዋለሁ ብሎኝ ከመኪናው አስወረደኝ ከዛ በቃ
ልጄን መጠጋት የከለከለኝ ሰው ህይወቱ እንዳበቃለት ሳቅ ወደ ልጄ ለመቅረብ
ፈልጌ መጣው እሱ ግን ያኔ ባይቀበለኝም አሁን ተቀብሎኛል ያውም ከእሱ
ለመራቄ ምክንያት ሳይጠይቅ። ተመስገን ከእዚህ በኋላ ማንም አይለየንም"
አለች።
፨ፅናትም "እሺ ከዛስ" አለቻት። ሶስናም "ከዛማ የኔ ቆንጆ የያቤፅ አባት ከሞተ
በኋላ አንድ ሰው መጥቶ ልጅሽ እብድ አደለም የልጅሽ አባትም ላንቺ የሚሰጥሽ
መዳኒት እንደነገረሽ አይነት አደለም። ለ3ቀን መዳኒቱን ካልወሰድሽ ስቃይ
ቢኖረም ትድኛለሽ ግን ከባድ ነው"አለኝ። እኔም ልጄን እያሰብኩ ህመሙን
እወጣዋለው ለልጄ ስል አረገዋለው አልኩት። ስውየው ከሄደ በኋላ ሱቄን ለአንዴ
እና ለመጨረሻ ጊዜ ዘጋውት መዳኒቱን እምወስድበት ሰአት ደረሰ እንደጉድ
ጭንቅላቴ መብላላት ጀመረ። በጣም ጥቋቁር ሰዎች የሚደበድብኝ መሰለኝ
እራሴንም ማጥፍት በጣም አማረኝ። እራብ እራብ አለኝ። የሱቁን ብስኩቶች
በጉልበት እየከፈትኩ መብላት ጀመረኩ።
፨ይህ ነው ብላቹ እማይገባቹ ህመም ለ3 ቀናት በስቃይ አሳለፈኩ ሰውነቴን ሁሉ
ነካክሼ ቁስል በቁስል ሆንኩኝ። ከ3ቀን በኋላ እልም ያለ እንቅልፍ ወሰደኝ። እና
ከእንቅልፌ ስነቃ እራሴን የያቤፅ አባት ቤት የድሮ መኝታ ቤቴ የድሮ የግል
ዶክተራችን እያከመኝ አገኘውት። ደነገጠኩ ማነው እዚህ ይዞኝ የመጣው
አልኩኝ። ዶክተሩም ምንም አላውቅም ፈጣሪ ምህረቱን ይላክልሽ ብሎኝ ወጣ።
ዶክተሩ እንደወጣ የያቤፅ አባት ጠባቂ መጣ። ምን እየተፈጠረ እንደሆነ ጠየኩት
494 views18:45