Get Mystery Box with random crypto!

📚📚ቤተ__መፅሀፍት📖📗🧾📜

የቴሌግራም ቻናል አርማ fetaenbeel — 📚📚ቤተ__መፅሀፍት📖📗🧾📜 ቤ
የቴሌግራም ቻናል አርማ fetaenbeel — 📚📚ቤተ__መፅሀፍት📖📗🧾📜
የሰርጥ አድራሻ: @fetaenbeel
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.00K
የሰርጥ መግለጫ

📚📚እንኳን በደህና መጡ📖📗🧾
➥ እዚህ ቻናል ላይ የተለያዩ የ አማርኛ እና English መፅሀፍትን በ 📙 Pdf እና ትረካዎችን እና ሌሎችም ጠቃሚ ነገሮችን ያገኛሉ።
📖 ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል‼️
B-) :-መረዳዳት ቢኖር ሁሉም ቢተባበር
100K ይደርስ ነበር ።
For any comment @Meki3

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-28 20:27:34
For any comment @Meki3

Share eyadaragachu


Yha book kalachu ba pdf lakulgn tababarun
180 views17:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 20:17:52 ​​. ​ ◉●◦ አለሜ ነሽ ◦◉

ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ

▣ አንብበው ሲጨርሱ ሼር ያርጉ ▣

#ክፍል_4


ደራሲ:-ቤዛዊት ፋንታዬ የሽዋ ልጅ


... አዳም ዶክተሩ ጋር ከመሄዱ በፊት ሄዋን ስትነቃ አበባ መስሎ እሷ
ፊት ለመቅርብ በማስብ እንዳልተጨፈጨፈ ደን የተጠቀጠቀውን
ፂሙን ሊስተካከለው ፀጉሩንም በወጉ ለማድርግ በማስብ ሄዋንን
አይቶ ባይጠግባትም ብዙ ደቂቃ አይቷት ወደ ፀጉር ቤት ከነፈ
በደስታ በሳቂታ ፊት እየተራመደ ከሆስፒታሉ ትንሽ እራቅ ብሎ
ወደሚገኘው ፀጉር ቤት ገባ እና ቁጭ አለ ወረፋው እስኪደርስ
የእሱን እና የሄዋንን
ፎቶዎች እያየ ውስጡ በሀሴት ሞላ ፀጉር ቤት የተከፈተው ሬዲዮ
ላይ አንድ ታዋቂ ዘፋኝ ቃለ ምልልስ እየተደርገለት ነው ስልኩን
በኪሱ ከቶ ቃለ ምልልሱን መስማት ጀመር ጠያቂው ለታዋቂው
ዘፋኝ የሚጠላው ነገርን ጠየቀው ያው ሁሉም የሚለው ግን
የሆነውን ውሽት እንደሚጠላ መለስለት በስተመጨሻ ማስተላለፍ
የምትፍልገው ነገር ካለክ እና አንድ ዘፈን ለአድማጮቻችን
ብታስማልን የማስተላልፈው ነገር እንኳን የለም ዘፈን ደሞ ከእኔ
ሳይሆን ከሌላ ሰው ዘፈን ላንጎራጉር
ታመሽ ታምሜያለው
ስደኝም እንደዛው
ስትሞች ግን አልሞትም
እኔ ምን በወጣኝ
ብሎ እንጉርጉሮውን ገታ። አዳም በጣምም ተናደደ ብሽቅ አለ በገነ... ምክንያቱ ግልፅ ነው የመጀመሪያው ሰው እንዴት
የሚያስተላልፈው መልክት አይኖርም በሚለው ሲሆን ሌላው እና
ዋነኛው ደሞ ለእሱ አይነት አፍቃሪ ልብ ለሚያፈቅራት ሴት
ላበደው ለአዳም
ታመሽ ታምሜያለው
ስድኝም እንደዛው
ስትሞች ግን አልሞትም
እኔ ምን በወጣኝ
የሚለውን ቃል መስማት ያማል አይምሮን አልፎ ውስጥ ድረስ
ልብ ድረስ ገብቶ ያደማል። ፕሮግራም አቅራቢዋም ለመስናበቻ
የሚሆን ዘፈን ብላ
አሜን አሜን አሜንንንን
ልበል እስቲ አሜንንን
የሚለውን የኑዋይ ደበበን ዘፈን የፕሮግራሙ መዝጊያ አረገችው
ቢያንስ ጋባዥዋ በጋበዘችው ዘፍን ንዴቱ ጠፋ ወደ ኋላ ከሄዋን ጋር
ወዳሳለፈው የፍቅር ጊዜ ማስብ ጀመር ከ አመት በፊት ዩንቨርሲቲ
እያሉ ልደቷን ስታከብር ይህንን ዘፈን በማራኪ ድምፁ በ ዩንቨርስቲ
የሙዚቃ ባንድ አጋዥነት በምርጥ እና ጊቢውን ባነጋገረ እና
ባስደመመ መልኩ ዘፍኖ ሰርፕራይዝ አርጓት ነበር
ከዛም ልደቷን ግቢ አክብረው ወጣ ብለው ሲዝናኑ በድንገት
ተንበርክኮ በደስታ የታገቢኛለሽ ጥያቄ አቅርቦላት እሷም ተንበርክካ ተያይዘው
ተላቅስው ጥያቄውን የተቀበለችበትን ጊዜ ከዛ ደሞ እሷም
በተራዋ
አንነጋገርም ጨዋታው ይቅርብኝ
ቁጭ በል ከጎኔ ያይን እራብ አለብኝ
የሚለውን የኩኩ ሰብስቤ ዘፈን ከዘፈኑ ጋር አብራ እየዘፈነች
በፍቅር አይን እንዴት ታየው እንደነበር አስታወስ እና ፍገግም ሳቅ
ሳቅ እያለ ከዋዠቀበት ሀሳብ ነቃ ያነቃው የፀጉር ቆራጩ ድምፅ
ነበር አዳም ደነገጠ ብዙ ጊዜ ጠርቶት እንዳልስማው ተርዳ
እንደማፈር ብሎ ቀና ሲል ና ወርፋክ ደርሷል ብሎ ፀጉር
መታጠቢያ መቀመጫው ላይ እንዲቁመጥ ጋበዘው አዳምም
ቀልጠፍ ብሎ ተቀመጠ ለ2 ወራት ውሀ ያልነካውን ፀጉሩን
አጠበው ለእሱ ፊት የሚሆን ቁርጥ አስመርጦ ተቆርጦ ለ ፁጉር
ቆራጩ ከምስጋና ጋር ክፍያውን እስከ ጉርሻው ሞላ አድርጎ ሰጠብ
ፀጉር ቆራጩም ጎንበስ ቀና ብሎ አመስግኖ አዳምም
በአቆራርጡ ቆራጩም በጉርሻው ተደስተው ተመሰጋግነው ተለያዩ
አዳም
በጣም ሽበላ ሆኖል ያው ከ አንገቱ በላይ ቢሆንም ። አንድ ነገር
እንደሚቀርው አሰበ ልብስ እና ጫማ ልግዛ ወይስ ሄዋኔ
የምትወዳቸውን ልብስ እና ጫማ ላድርግ ብሎ ከራሱ ጋር ትንሽ
ግብግብ ከፈጠር በኋላ በስተመጨርሻ ሄዋኑ የእሱ ውድ
የምትወዳቸውን ለማድርግ ወሰነ ይህን እያስበ ሆስቲታል ደርሰ
ዶክተሩ
ና ያሉበት ስአት ስለደርስ ወደ ዶክተሩ ቢሮ አመራ ሲደርስ አንኳኳ
ኳኳኳኳኳኳኳኳ
ዶክተር "ማነው? ይግብ" አለ "እኔ ነኝ" አለ አዳም ዳክተሩም "ኦኦኦኦኦኦ አዳም ና
ግባ እባክህ
ቁጭ በል አዳም በጣም አምሮብካል ደሞ ዛሬ አሉ አዳምም ያው
ለእሷ ብዬ ነው አለ አዳም ልብ እንደ ከበሮ ለጉድ መምታት ጀመር
አዳም ጉሮሮውን ጠራርጎ
ለምን ነበር የፈለጉኝ ዶክተሩ ርዥምምምም ትንፋሽ ተንፍሰው
ትንፍሻቸውን መልስው ከስበሰብ በኋላ ንግግራቸው እንዲ ሲሉ
ጀመሩ እየውልክ አዳም አሁን በምነግርክ
ነገር በጭራሽ እንዳታዝን እንደውም ጠንካራ ሁን የአዳም የልብ
ምት በጣምም ፍጠነ ልብ በአፉ ሊወጣ ደርሰ እሺ ዶክተር ቀጥሉ
እኛ ሄዋን ብለው አሁንም ረጅም
ትንፋሽ ወስዱ አዳም ሊያብድ ምንም አለቀርውም እና ምን ዶክተር
ንገሩኛ እእእእ
ዶክተር ወሬያቸውን ቀጠሉ ሄዋንንንን አዳም ሰፍ ብሎ ሄዋን ምን
ብሎ አፈጠጠባቸው ሄዋን በደርስባት የመኪና አደጋ ምክንያት
ብለው አሁንም ዝም አሉ
አዳም እራሱን መቆጣጠር አቃተው እኔ ላብድ ነው በሉ ይናገሩ
ምንድነው መሄድ አችልም ሊሉኝ ነው ወይስ ጭንቅላቷ ውስጥ
ደም ፈሷል ስለዚህ አተርፍም የምታያት ዛሬ ማታ ብቻ ነው ልትሉኝ
ነው አለ ዶክተር አይ እሱ አደለም እንደዛ አደለም ሄዋንንን
የምታያት ነገ ነው መዳኒቷን አስተካክዬላት ነገ እንድነቃ
አርጊዋለው ግን ሄዋን ጭንቅላቷ በሀይል ስለተመታ ብሎ ዶክተሩ
ወሬውን ሳይጨርሱ ይህው ብያለው በቃ ትሞታለች ልትለኝ ነው
አደል አለ በለሆሳስ ዶክተርም አይ አይ ሄዋን አልዛይመር ወይም
የመርሳት በሽታ ይዞታል ሰለዚህ
አንተንም ሆነ በዙሪያዋ ያሉትን ነገሮች አታስታውስም አለው አዳም
ስቅስቅ ብሎ አለቀስ እናትዬ መከራሽ በዛ የኔ ህይወት አያለ...

ይቀጥላል...
@fetaenbeel
168 views17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 20:17:35 ​​. ​ ◉●◦ አለሜ ነሽ ◦◉

ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ

▣ አንብበው ሲጨርሱ ሼር ያርጉ ▣


#ክፍል_3



ደራሲ ቤዛዊት ፋንታዬ( የሸዋ ልጅ)




... ጩኸቱን ሲጨርስ ረዥም ሳቅ ሳቀ። በረዥሙ ተንፍሶ ወደ ቀልቡ ተመለሰ ። ዲና አሁን ላይ ይህቺ ሴት ማን እንደሆነች ልትጠይቀው ወሰነች ። ጉሮሮዋን
ከጠራረገች በኋላ" እእእእእ እስቲ ስለ ሄዋን ንገረኝ አዳም" አለችው
" ምን ልንገርሽ" አላት
"ማለቴ ያው እንዴት እንደተዋወቃችሁ... ፍቅር እንዴት
እንደጀመራችሁ እና እንዴት እንደዚህ ልታፈቅራት እንደቻልክ" ዲና ይህንን ብላ
ቁልቁል አዳምን አየችው ።
ፊቱ በፈገግታ በርቷል ። ልክ እንደ ነፀብራቅ ፈክቷል ።
ባለፈው ፈገግ ካለው ይልቅ ሲስቅ በጣም
እንደሚያምር አወቀች ።
" ኡፍፍፍፍ እሷን ያወቅኩበትን ቀን ላንዴም
አልዘነጋውም ። ከ5 አመት በፊት የካምፓስ ተማሪ ነበርኩ ። 6 ጓደኞች ነበሩኝ ። ከእኔ
ጋር 7 ማለት ነው ። የሁለተኛ አመት ተማሪ ነበርን ። ከእነሱ በጣም የተለየ ፀባይ ነበረኝ ። ማለቴ እነሱ ሴት ማተራመስ እና መላከፍ በጣም ይወዳሉ ። ወሬያቸው ሁሉ
ሰለ ሴት ነው ። እኔ ደግሞ ሀሳቤ ሁሉ መፅሀፎቼ ላይ ነው ። ፀጥ ያለ ቦታ ይመቸኛል ። ግን ጓደኞቼ አብሬያቸው እንድሆን ሲጠይቁኝ እንቢ ማለት አልችልም ። ሄዋኔን
ያየኋት የሁለተኛ አመት ትምህርት ለመጀመር ተማሪው ከቤቱ ወደግቢ
የሚጎርፍበት ሰአት ላይ ነበር ። ጓደኞቼ እንደለመዱት ለመላከፍ ወደሚመቻቸው
ቦታ ሄደው ተደላድለው ተቀምጠው ነበር ። ያኔ እኔም ነበርኩኝ ። አንድ መካከለኛ
ቁመት ያላት በጣም ቀይ እና ፀጉሯ በጀርባዋ የወርደ ግን በቅጡ ያልተያዘ ፀጉር ያላት...የወንድ የሚመስል አለባበስ ለብሳ በአጠገባችን ልታልፍ
ስትል አንዱ ጓደኛዬ "ኧረ ይቺ ልጅ ፍሬሽ ናት መስለኝ አይቼያት አላዉቅም ። እስቲ
ላስደስታት" አለና ድምፁን ሰልከክ አርጎ "እሙዬ ሻንጣውን ላግዝሽ " አላት
እሷም ፈገግ ብላ "አመሰግናለው ወንድሜ አጋዥ አያስፍልግም" አለችው ቀጠል አድርጎ "ወይም አንቺን ተሽክሜሽ ልግባ " አላት...
ጥቂት ሄድ ካለች በኋላ ፊቷን
ፍክት አድርጋ ፈገግ እያለች "አንዴ እስኪ ና " አለችው...
ደስ እያለዉ ወደ እሷ
ቀረበ ። ሌላኛው ጓደኛችን "ኧረ ንቀት እራስሽ አትመጪም እንዴ..ምንሼ ነው" አላት...
እሷም ዝም ብላ ያኛውን ጎደኛችንን በአይኖቾ አታላ አጠገቧ አመጣችው ። ከዛም
በጥፊ ጭንቅላቱን አዞረችበት ። ሁሉም ደነገጡ ። እኔ እራሴም ደነገጥኩ ። 'ትስማኛለህ '
አለች እየጮኸች...
" አንተ ከንቱ.. የማትርባ አፍክህ በከፈትክ ቁጥር ባዶነትህን
ነው የሚያሳየው ። ዳግም እንዲህ ብታደርግ አንላቀቅም ።" ብላው ሄደች... ስታወራ...ጩከቷ አለም ላይ ያለ ሰዉ ድምፅ አዋጥቶ ለእሷ የተሰጣት ይመስላል ።
በጣም በጩከት ነው የምታወራው ። ልጅቷ ከሄደች በኋላ ጓደኛችን በድንጋጤ
ደርቆ ጉንጩን እየሸፈነ መጣ ።
ምን ብለሃት ነው ስንለው...' ለምንድነው
ወንድሜ የምትይኝ ..ይልቅ ማታ አልጋ ይዘን ለምን አናወራም ' ነበር ያልኳት አለ ።
ሁላችንም በጣም ሳቅንበት ። ይቺ ሴት ሄዋን ነበረች ። ሁሉም ሴት
ሲለከፉ እያፈሩ እና እየተሽኮርመሙ ሲሄዱ እራስዋን ያላስበገርችው ሄዋን ናት ።
ሄዋን ልጁን መታው ከመሄዷ በፊት አንድ ቃል ተናግራለች ። "እኔ ሄዋን ነኝ እሺ
የምሽኮርመምልህ ወይም የምፈራህ እንዳይመስልህ ። በጭራሽ እንዳትሳሳት.. ቀና ብለህ እንዳታየኝ ። ተግባባን !! ብላ አስጠንቅቃዉ ነበር ።
በጣም ገርመችኝ... ወኔዋ በእራስ
መተማመኗ እና ሁሉ ነገሯ አስገረመኝ ። ለፍቅር ያጨኋት ማለቴ
በአይነ ህሊናዬ የሳልኳት አይነት ሰው ሳትሆን ግን ልቤን እና ሁሉ ነገሬን በአንድ
ጊዜ ተቆጣጠረችው ።" አለ አዳም ። ፈገግ እያለ ነበር የሚያወራው ።
" በቃ የቀረውን ደግሞ
ሌላ ጊዜ" አላት የእጅ ሰአቱን እየተመለከተ ።
" ኧር አለስማህም... ልቤን
እንደዚህ አንጠልጥለኸዉ ወልፈት የለም ። በቃ እንደውም ዛሬ ሆስፒታል ነው የማድርው።" አለችው ።
አዳም በአግራሞት እያያት "ዛሬ እረፍት አደለሽ እንዴ " አላት
"አዎ ነኝ ግን የእረፍት ጊዜዬን ጣፋጭ የፍቅር ታሪክ በመስማት ላሳልፍው
ወስኛለሁ" አለችው ።
የመድሀኒት መደብሩ ጋር ደርሱና መድሀኒቱን ገዙ ። መድሀኒቱ በጣም ውድ ነው ። ቢሆንም ግን የገንዘብ ችግር የለበትም ። ገዛና ወደ ሀኪም ቤቱ ተመለሱ ።
ከመድሀኒት ቤቱ እስከ ሆስፒታሉ ምንም ነገር አላወሩም ነበር ። ሆስፒታሉ በር
ላይ ሲደርሱ
ዲና "በቃ አሁን ቤቴ ሄጄ እርፍት ላድርግ..አመሻሹ ላይ መጥቼ
የጀመርክልኝን ትጨርስዋለህ። እንገናኛለን" ብላዉ ተሰናበተችዉ ። ባይኑ ሽኛትና ሄዋን ወደተኛችበት ክፍል አመራ ። ሄዋን አሁንም ኮማ ውስጥ ናት ። ግን ደግሞ
ልትነቃ ትንሽ ለሊት ማታ እና ቀን ወይም ሰአት ነው የቀረው ።
"ሄዋኔ " አለ በለሆሳስ
ደምፅ ...
"አንቺን አለማፍቀር ይቻላል...? እእ አንቺን አለመውደድስ ...? አይ በጭራሽ
አይቻልም ። አዎ አይቻልም.. የኔ አስተዋይ .. የእኔ ጩኸታም.. የኔ አኩራፊ ንቂ ...ንቂልኝ ።
ሄዋኔ ሄዋኔ አንቺ ነሽ ሰላሜ
እናቴ ልበልሽ በቃ ነሽ አለሜ
የፍቅርሽ ወላፈን ከአድማስ ባሻገር
ልቤን አሳመመሙ ለኔ ሳይናገር ።
ኮማ ውስጥ ያለሽው ፍቅሬ ተይ ንቂልኝ
ጨርቄን ጥዬ ሳላብድ ባክሽ ድርሽልኝ ።
እያለ አጠር ያለችውን የግሉን ግጥም በውስጡ አዥጎረጎርው ።
በተመስጦ
እሷን በማየት ግጥሙን ቀጠለዉ...

ትነቂያለሽ ብዬ በተስፋ ልጠብቅ
አትነቂም ብሎ ውስጤ እንዳይጨነቅ።
እያለ በሀዘን ፊት ያያት ጀመር ።
"ትነቂያለሽ ውዴ" አለ በለሆሳስ....
እዚህ ሀስብ ውስጥ ሆኖ ጠና ያለው ዶክተር ትካሻውን ለመጣራት እና
ለማፅናናት ያክል መታ አደረገው።
"ከአንድ ሰአት በኋላ ቢሮ ና" ብለውት ሄዱ...
"ምን ሊሉኝ ነው...? አትተርፍም ትሞታለች ሊሉኝ ነው...? ለምን እንዲህ አዘኑ..? እእእ "

ይቀጥላል...
@fetaenbeel
161 views17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 20:42:20 ​​. ​ ◉●◦ አለሜ ነሽ ◦◉

ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ

▣ አንብበው ሲጨርሱ ሼር ያርጉ ▣

#ክፍል_2


ደራሲ ቤዛዊት ፋንታዬ የሽዋ ልጅ



... የዚህችን ሴት ምንነት ለመግለፅ ምን ይሆን የከበደው..? የሚለውን ጥያቄ ሲጮኽ
የሰሙት ሰዎች በውስጣቸው ያለ ማቋረጥ እያሰቡት ነው ። አለሙ ማን ናት
ህይወቱስ ማን ናት?
ድቅደቁ ምሽት ተገፎ ወደ መነጋጋቱ ወስዶታል ። ብርሀን እየመጣ ነው ።
ጨለማው ለውጦ ፀሀይ ቦታዉን ተረክባለች። ኮማ ውስጥ ያለችው
ሴት ቀኑን እና ለሊቱን ያለ ልዩነት በስቃይ ውስጥ ነች።
ማታ ሆስፒታሉን ሲቀውጠው ያደረው ያ ለግላጋ ስውም በእንባ እና በእንቅልፍ
አብጦ አይኑን እያሻሽ ተነስቶ ኮማ ውስጥ ወዳለችው ሴት አመራ ።
በጉጉት እና በናፍቆት ሲከንፍ ሄዶ አያት ። ምንም የተነቃነቀም ሆነ የተለወጠ ነገር
የለም ። ዛሬ ከትላንት ለእሱ የተለየው መሽቶ መንጋቱ ብቻም አይደለም። የሚሳሳላት ሴት በህይወት መኖሯም ተመስገን አስኝቶታል ።
ሰላም ስላሳደራት...ሰላም እንዲያውላት እና እንዲያኖራት ወደ ቤተ ክርስቲያን ፈጣሪዉን ሊያመስገን ፤ ሊማፀን ሄደ ። በሃሳብ ሩቅ ስለነጎደ ረዥሙ መንገድ አልታወቀውም ። በስተመጨርሻ
እራሱን ቤተ ክርስቲያኑ ደጃፍ ላይ አገኘዉ። ሰማይ እና ምድርን..ሙት
እና በህይወት ያሉትን ነገሮችን በሙሉ የማንቀሳቀስ እና የማዘዝ መብት ላለው
ፈጣሪ ስላምታውን አቀርበ ። ወደ ግቢው ዘልቆ ገባና አንድ ድንጋይ
ላይ ቁጭ አለ።

ግማሹ ቁሞ ሌላው ተቀምጦ ከፊሉ ደግሞ ተንበርክኮ ምልጃውን ያደርሳል ። በጉልበቱ ተንበርክኮ አለሙ የሆነችውን.. እስትንፋሱ የሆነችውን ሴት እንዳይወስድበት
ተማፀነው ። ቀጥሎ ዝም ብሎ ቆየ ። ከራሱ ጋርም እንዲ ሲል ሙግት ገጠመ
"ቆይ ፈጣሪ ቂም ያዉቃል እንዴ..? ለምንድነው አዳምና ሄዋንን ይቅር ያላላቸው። አይ..አይ ለነገሩ
አታድርጉ የተባለውን ነገር ስላደረጉ ነው ። ቆይ ታድያ ፈጣሪ ሀጢያት እንደሚሰሩ
ካወቀ ለምን አላስቆማቸውም..? ለነገሩ ማሰቢያ አእምሮ ሰጥቷቸዋል.. ማስብ የእነሱ ድርሻ ነው ። ልንሞት ነገርስ ለምን ተፈጠርን..? ምን ሆኜ ነው ...ፈጣሪ
የፈጠርንኮ ለመግደል ብሎ አይደለም ። እሱማ ያረገው ነገር ቢኖር ነፃነትን
ከእውቀት ጋር መስጠት ነው ። ፈጣሪን ከምወቅስ አታድርጉ ተብሎ ላረግነው እኛ
ለምን ክስ አላቀርብም..? ምን እየሆንኩኝ ነዉ!! ፈጣሪ ፍቅር ነው ።
ጥላቻን እንድናውቅ ያረገን የፍቅርን ሀያልነት ሊያሳየን ስለፈለገ ነው ። አዳም
ብቻውን ቆዝሞ ከራሱ ጋር ያወጋል ። ስለማንም ግድ አልሰጠውም ። የእሱ ሄዋን አሁን አጠገቡ የለችም ።
ወደ ራሱ ተመለሰ በሀዘኑ ምክንያት የተንጨበረረ ፀጉሩን እና ፂሙን በተራ እየዳበሰ ተንጠራርቶ ተነሳ ። ወደ ሀኪም ቤት ተመለሰ።

በጣም ርቦታል መብላት ፍልጓል። ያለ እሷ መብላቱን ሊለምደው አልቻለም ።
ከትላንት ጀምሮ ምግብ በአፉ አልዞረም ። ለመብላት በማስብ ወደ ሀኪም ቤቱ ካፌ ሄደና ተቀመጠ ።

ቀጫጫ ረዘም ያለ አስተናጋጅ ቀልጠፍ ብሎ " ምን ይምጣ ወንድሜ " አለው
"እእ ቀለል ያለ ቁርስ ባንተ ምርጫ ይሁንልኝ" አለው ።
አስተናጋጁም ሲከንፍ ሄዶ ምርጥ ዱለት ከውሀ ጋር አመጣለትና መልካም ምግብ ብሎት ሄደ ። እጁን ታጥቦ ዱለቱን
በፍጥነት በልቶ ጨርሰ ። የራሱን ሆድም በጣም ታዘበው ። "ለካስ ስጋና ነብስ የተለያዩ ናቸው ።" አለ በውስጡ
"እሷ ተኝታ እኔ ግን በላሁ" አለ
ምግብ መቅመሱ በትንሹ ያረጋጋው ይመስላል ። ከበላ በኋላ አረፍ ማለት ቢፈልግም አልቻለም ። ልቡ እና ሀሳቡ ሄዋኑ ጋር ነው ። እርሷ ጋር ሲደርስ ብቻዋን አልነበርችም ። አጭሯ ነርስም
ነበረች ። በውስጡ "ይህቺ ነርስ ቀንና ለሊት ነው እንዴ የምትሰራው" ሲል እያሰበ ተጠጋት ።
በስስ ፈገግታ ስላም ተባባሉ።
ነርሷ አተኩራ እያየችው " ትላንት ግን" አለችና ፀጥ አለች
"ትላንት ምን..?" አላት
"አይይይ በጣም ጮኸክ በስላም ነው..?" አለችው
የትላንቱ ትዕይንት በአይነ ህሊናዋ እየታያት ።
"ልብሽን አሞሽ ወይም ልቡን የታመመ ሰው አጋጥሞሽ ያዉቃል ..?" አላት
" ዉይ አዎ !! ይገርምሃል ጎረቤቴ ልቡን አሞት ነበር ። ማለቴ የልብ ድካም
አለበትና በቃ ሊሞት ለጥቂት ነው የተረፈው " አለችው ።
አዳም ትንሽ ሊስቅም
ቃጣው ። ሌላ ጊዜ ቢሆን በደንብ ይስቅ ነበር ። አሁን ግን የሚስቅበት አንደበት የለውም ።
ፈገግ ብሎ እያያት
" እሱኛውን የልብ ህመም አደለም ያልኩሽ ። በፍቅር ምክንያት ሰለሚታመም
ልብ ነው የጠየቅኩሽ ። ልክ እንደኔ በፍቅር መስቃየት የሚወዱትን.. የሚያፈቅሩትን ስው በቅርብ በአይን እያዩት በእጅ የማይነኩትን ነዉ የምልሽ..የሚወዱትን ሰው ትንፋሽ
ካጠገቡ ሳትርቂም እስትንፋሱን አለመስማት... ድምፁን መራብ በጣም ያማል ። ቅስምን ይስብራል ። ይህንን ህመም . ..
ይህንን ስቃይ ነው ያልኩሽ" አላት
አሳዘናት... ያላትን ነገር
ተረደተዋለች። እጇን ወደእሱ ሽቅብ እየዘረጋች "እንተዋወቅ ዲና እባላለው... ቅር ካላለህ የሁለታችሁንም ስም ብትነግርኝ " አለችው ። ዳግመኛ ስለ ስሟ ስጠይቀው እንደ ማታው እንዳይጮኽ በመፍራት...
የጨበጣትን እጁን ከእጇ አላቀቀና " እኔ
አዳም እባላለሁ። እሷ ደግሞ" አለ አልጋዉ ላይ ዟ ብላ ወደተኛችው ልጅ እየጠቆመ "ሄዋን ትባላለች" ብሎ ሌላ ወሬ ሊያወራ ሲል ተናዳ "አትቀልድ
ባክህ ትክክለኛ ስማችሁን ንገረኝ" አለችው ...
"ማለት?" አላት
"ማለትማ ስማችሁን በስርአት ንገረኝ"
" ነገርኩሽኮ" እየተባባሉ ሲጨቃጨቁ አንድ ጠና ያለ ዶክተር ሄዋን ክፍል
ገብቶ ካያት በኋላ ወደ አዳም ዞረና "አቶ አዳም ለወይዘሪት ሄዋን መድሃኒት
ያስፍልጋታል ። ነገ ማታ ትነቃለች የሚል ግምት አለኝ "ብሎት ሄደ ...
ነርስ ዲናም እንዳልቀለደ ገባት ። አዳም እና ሄዋን መገጣጠም ነው ወይስ
ለእራሳቸው አውጥተውት ነው..? ብላ ተገረመች ። አዳም በደስታ ጮቤ ረገጠ ። መቼም የሚያየው ያልመስለውን አይን ሊያይ ቀጠሮ ተስጥቶታል ። ሮጥ ሮጥ እያለ መራመድ ጀመረ... ዲና "የት ልትሄድ ነው
አለችው"
"መድሃኒቱን ልገዛ ነዋ " ፊቱ ላይ ደስታ ይነበባል ።
"አብርን እንሂድ " አለችው
ፈገግ ብላ ...
"ሾልሽሾ? "
"ፈረቃዬን ጨርሻለው። ከመውጣቴ በፊት ላያችሁ ነበር የመጣሁት ።
"እሺ እንሂድ" አላት አዳም እየተጣደፈ
እስታፍ ልብሷን ቀይራ መጥታ መንገድ ጀመሩ ።
መንገድ ላይ "አለሜ ልትነቃ ነው። አዎ ልትነቃ ነው ። እናትዬ ልትነቃ ነው " አለ ጮኽ ብሎ...
ዲና ግራ ገባት ። እንደመሳቅም እየቃጣት
" አረ ባክህ ዝም በል..ቆይ ይህቺ
ሴት ምን አይነት እድለኛ ብትሆን ነው እንዲህ ያለ አፍቃሪ የሰጣት። ...
አይ ሄዋን " አለች በውስጧ ስለሁለቱ ታሪክ ለመስማት እየጓጓች....

ይቀጥላል...

@fetaenbeel
235 views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 20:42:06 ​​​​. ​ ◉●◦ አለሜ ነሽ ◦◉

ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ

▣ አንብበው ሲጨርሱ ሼር ያርጉ ▣


#ክፍል_1



ደራሲ ቤዛዊት ፋንታዬ የሽዋ ልጅ
.
.
.
ዛሬ አንድ ግሩም ለግላጋ ስው ኮማ ውስጥ ያለችውን ሴት በክፍሉ ማሳያ በኩል በሀዘን እና በጭንቀት በፍቅር አይን አትኩሮ እያያት ነው ። በጣም
ተመስጧል ። በእርግጠኝነት ይህ ስው የሴቲቱን መንቃት እንደሚጠባበቅ በህይወቱ ምንም ተጠባብቆ
የሚያዉቅ አይመስልም ። አንድ አጠር መጠን ያለች ቀልቃላ ነርስ መጣችና ደንደን ያለውን ትከሻውን መታ አድርጋዉ ከሃሳቡ አነቃችው ። ይህ ስው ከሃሳቡ ቢነቃም የነቃ
አይመስልም ። ይህች ጀርባ መቺ ከማጠሯ የተነሳ ያቀረቀረው አንገቱን ቀና አርጎ መመልከት አልተጠበቀበትም ። ባይኑ ስላምታ ስጥቷት.. ልብ
ሰራቂ የሆነውን ፈገግታዉን በትንሹ የግዱን አሳያት።
" እኔ እምልህ" አለችው አጭሯ ነርስ እሱም ቀጥይ ወሬሽን የሚል በሚመስል
መልኩ አያት "ይህቺ ሴት ምንህ እንደሆነች እስቲ ንገርኝ አለችው "
ረዥም ዝምታ በመካከላቸው ሰፍነ ። ትግስት ያጣችው አጭሯ ነርስ "ምነው ዝም አልክ ...? መቼም ምንህ እንደሆነች ጠፍታብህ እንዳልሆነ ተስፋ አረጋለው ። በቃ ልገምት እእእእ
እህትህ ናት" አለችው...
"አይደለችም" አለ እንባው መተናነቅ የጀመረው ይመስላል...
"እና መቼም ልጅህ አትሆንም" አለችና ፈገግ አለች ። እሱ ግን ስምቶት
ወይስ ችላ ብሎት ፈገግም አላለ...
ፊቱን በአተክሮት አየችው እንደተከዘ ነው ። " እሺ እና ፍቅርኛህ ናት..?" አለችው
"አይ እሷ" አላስጨረሰችውም "እእእ መቼም እናትህ አደለችም ..ወልዳ አንተን
አታደርስ" አሁን የሰማት ይመስላል ፈገግ አለ ።
እሷም "እና ቆይ ሚስትህ ነች ማለት ነዉ ። አለችው...
ዝምም አለ በድጋሜ ። ረዥም ዝምታ
በመሀከላቸው ስፈነ ። አጭሯ ነርስ ግራ ገባት ። ከፊቱ የተኛችውን እንስት ማንነት
ለማወቅ ከፊቷ ከቆመው ሚስኪን ሰው ብጠይቅም መልስ አልሰጣትም ።
" እና ምንህም ካልሆነች እዚህ ምን ትስራለህ...? ወይስ" ስትለው "እንዳጨርሽው በቃ "
አላት እየጮኸ
"እሷ ማለት ለእኔ አለሜ ናት ። ምንህ ነች ስትይኝ ምኔ ነች ልበልሽ...? ሁሉ ነገሬ
ናታ !" የተናነቁት እንባዎች በትንሹ ተከታትሉ። ብዙም ሳይቆዩ እየተሽቀዳደሙ ይፈሱ ጀመር ።
አጭሯ ነርስ በጩኸቱ ተደናገጠች ። በቃላቱም ተገርዠረመች " አለሜ ናት ፤ ህይወቴ ናት ፤ ደስታዬ ናት ፤
ፍቅሬ ናት በቃ ሁሉ ነገሬ ናት ። " አለ መልሶ...
አጭሯ ነርስ አሁን ምኗ እንደሆነ የገባት
ይመስላል ። እየደጋገመ አለሜ ነሽ ፤ አለሜ ነሽ ..አለሜ ናት.. አልተዋትም
አፍቅራታለሁ ። ህይወቴ ናት ።" እንደ መፍክር እየጮኸ መናገር ጀመረ ።
ጭኸቱ በረታ ። ክፍሉን አናወጠው በእዚህ መሀል አጭሯ ነርስ ፈዛ
ደንዝዛ ቀረች ። ጩኸቱ ያስደነገጣት መልሱም ያልጠበቀችው ትመስላለች ። ለቀናት በሀዘን ተክዞ የሷን መንቃት የሚጠባበቀውን ሰው የሀኪም ቤቱ ዘበኞች እና ሁኔታውን እያዩ ሲያዝኑ የነበሩት ሰዎች እያዋከቡ አስወጥተው የሀኪም ቤቱ ግቢ ማረፊያ ወንበር ላይ አስቀመጡት ።
ወደራሱ የተመለስ አይመስልም ። አሁንም አለሜ ነች ፤ ሁሉ ነገሬ !!
ምንህ ናት አትበሉኝ። ሁሉ ነገሬ ናት.. ምንህ ናት እያላቹህ አታስጨንቁኝ ። ስንቴ ነው የምትደጋግሙብኝ ።" ቀስ በቀስ ድምፁ ሰለለ...ድካም ተስማውና ባለበት አግዳሚ ወንበር ላይ ጋደም አለ።
"ዘመድ የለኝም ዘመድ የላትም ። ምንህ ነች አትበሉኝ ..ሁሉ ነገሬ ናት። ይላል አሁንም አልፎ አልፎ ።
ድምፁን እየቀነስ እየቀነሰ በስተመጨረሻ ዝምምም አለ ። ዘበኞችም ፎጣ
ፈላልገው አልብስውት እዛው እንቅልፍ ወሰደው ። ሁሉም በውስጡ ይህቺ ሴት
ማናት ይላል.. እውነትም ይህቺ ሴት ማናት?...

ይቀጥላል...


@fetaenbeel
2.1K views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 20:41:06 ብቀመጥ ይሻለኛል›› ሲል ሰማችና ዞራ ተመለከተች፡ ኒኪ ይህንን ሰው
የሚቀመጥበትን ቦታ እያሳየው ሲሆን ሰውየው ጀርባውን የሰጣት ስለሆነ ማን እንደሆን አላወቀችም፡፡ ሰውየው ጸጉረ ነጭ ሲሆን ሰማያዊ ሱፍ ልብስ ለብሷል ኒኪም ‹‹ደህና ሚስተር ቫንዴርፖስት ያሉት ቦታ መቀመጥ ይችላሉ፡

! ሰውየው ዞር ሲል ከማርጋሬት ጋር ዓይን ላይን ግጥም አሉ።ስሙ ቫንዴርፖስት አይደለም ሰውየውን ከዚህ ቀደም ታውቀዋለች፡
አሜሪካዊም አይደለም፡ ሄሪ ለማስጠንቀቅ ገልመጥ አደረጋት ሆኖም ዘግይቷል፡፡

‹‹ወይ እግዚአብሔርl›› ስትል ለራሷ አጉተመተመችና ‹‹ሄሪ ማርክስ!››
ስትል ተጣራለች፡....

ይቀጥላል
128 views17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 20:41:06 #ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


...."አስተናጋጁ ሁለተኛውን ዙር ምግብ አመጣላቸው፤ ኮተሌትና ሰላጣ ቪኖም ቀዳላቸው:

አባትም የቀረበላቸውን ምግብ በሹካ እየወጉ አፋቸው ውስጥ ከተው
በንዴት ያኝካሉ፡፡ ማርጋሬት የአባቷን ፊት ስታይ ከንዴታቸው በስተጀርባ
የግራ መጋባት ሁኔታ ይነበብባቸዋል፡ እንደዚህ ድንብርብራቸው ሲወጣ
አይታ አታውቅም፡፡ ሰማይ እንደተደፋባቸው ተገንዝባለች ይህ ጦርነት
ራዕያቸውን ሁሉ ድባቅ መቶባቸዋል፡፡ የእሳቸው ፍላጎት የእንግሊዝ ህዝብ
ፋሺዝምን በእሳቸው መሪነት እንዲቀበል ነበር፤ ጭራሽ እንግሊዝ በፋሺዝም
ላይ ጦርነት አውጃ እሳቸውን ለስደት ዳረገቻቸው፡

የተመኙት የፖለቲካ ሁኔታ አፈር መብላቱ ሳያንስ ልጆቹ ደግሞ እያመጹ አስቸገሩ: ፔርሲ ይሁዳዊ ነኝ እያለ ይቀባጥራል፤ ማርጋሬት
ልትጠፋ ሞከረች ከሁሉም በላይ የእሳቸው አስተሳሰብ ተከታይና የአመለካከታቸው ተጋሪ የነበረችው ኤልሳቤት ደግሞ ትዕዛዛቸውን ጣሰች፡

ማርጋሬት ለመብላት ብትሞክርም የጎረሰችው አልዋጥልሽ አላት፡፡
እናትም ‹‹በርሊን ፍቅረኛ አለሽ?›› ሲሉ ጠየቋት፡፡

‹‹የለኝም›› አለች ኤልሳቤት፡ ማርጋሬት አምናታለች። ማርጋሬት እንደምታውቀው ኤልሳቤት ጀርመንን የምትወደው በሚከተሉት የፖለቲካ አመለካከት ብቻ አይደለም፧ እነዛ ጸዳ ያለ ዩኒፎርም የሚለብሱትና
የሚያብረቀርቅ ጉልበት የሚደርስ ቦት ጫማ የሚያጠልቁት ዘንካታና ጸጉረ ነጭ ወታደሮች ልቧን ሰልበዋታል፡፡ ኤልሳቤት እንግሊዝ ውስጥ መልከ ጥፉ ተብላ ብትቆጠርም ጀርመን ውስጥ ግን የጀርመንን ናዚዝም የሚያደንቅና የሚደግፍ የእንግሊዝ ባላባት ልጅ ናት ተብላ ትከበራለች፡፡ የሁለተኛው ዓለም ጦርነት መቀስቀሻ ላይ አገሯን ከድታ የመጣች መሆኗ ዝነኛ ያደርጋታል፡፡ እዚያ ‹‹አንበሳ›› ነው የምትባለው፡ከቀናትም አንዱን ወጣት
መኮንን ታፈቀርና ወይም ስልጣን በስልጣን ላይ የጫነ የናዚ ፓርቲ አባል
ታገባና ጸጉረ ነጭ ልጆች ትወልድለታለች፧ ልጆቹም ጀርመንኛ እየተነጋገሩ
ያድጋሉ፡፡

‹‹አሁን ልታደርጊ ያሰብሺው ነገር አደገኛ ነው የኔ ማር፤ አባትሽ እና እኔ የተጨነቅነው ለደህንነትሽ ነው›› አሉ እናት፡፡

ማርጋሬትም አባታችን የኤልሳቤት ደህንነት ያስጨንቀው ይሆን?›
ስትል አሰበች፡፡ እናታቸው ያስጨንቃቸዋል፤ አባታቸው ግን የተናደዱት ኤልሳቤት ትዕዛዛቸውን ባለማክበሯ ነው፡፡ በእርግጥ ከቁጣቸው በስተጀርባ የሩህሩህነት ጭላንጭል ይታያል፡፡ ድሮ እንዲህ ጨካኝና ክፉ አልነበሩም፤ አንዳንዴም ልጆቹን ያጫውቷቸው ነበር፡ ይህ ሁሉ በሃሳቧ መጣና አዘነች።

‹‹አደገኛ እንደሆነ አውቃለሁ, አለች ኤልሳቤት ‹‹የወደፊት እጣ ፈንታዬ በዚህ ጦርነት ላይ የተመሰረተ ነው፤ በይሁዳውያን ባለሃብቶችና
በቆሻሻ ኮሚኒስት የሰራተኛ ማህበራት የተሞላ ዓለም ውስጥ ከምኖር ሞቴን
እመርጣለሁ››

‹‹ታዲያ ከኛ ጋር ሂጂያ
አሜሪካ ጥሩ አገር ነው›› አሉ እናት፡፡

‹‹የአሜሪካ የባንክ ቢዝነስ ማዕከል (ዎል ስትሪት) በይሁዳውያን እጅ
ነው ያለው›› አለች ኤልሳቤት፡፡

‹‹ይሄ መቼም ተጋኗል›› አሉ እናት ፈርጠም ብለው የባላቸውን አይን እየሸሹ፡፡ ‹‹በእርግጥ በአሜሪካ የቢዝነስ ስራ ውስጥ በርካታ ይሁዳውያንና
ብልሹ ሥነ-ምግባር ያላቸው ሰዎች መኖራቸው እርግጥ ነው፡፡ አያትሽ
ደግሞ የባንክ ባለንብረት እንደሆኑ አትዘንጊ፡፡››

‹‹በሁለት ትውልድ ከቀጥቃጭነት ወደ ባንክ ባለንብረትነት መለወጣችን
የሚደንቅ ነው›› አለ ፔርሲ፡፡ ሆኖም ማንም ጆሮ የሰጠው የለም፡፡

እናትም ቀጠሉና ‹‹በፖለቲካ አመለካከትሽ እኔም እስማማለሁ፤ አንቺም
ይህን ታውቂያለሽ ነገር ግን በአንድ ነገር ስላመንሽ ለእሱ ስትይ ህይወትሽን
ትሰውያለሽ ማለት አይደለም›› አሉ
ማርጋሬት ይህን ስትሰማ ደነገጠች፤ እናታቸው የፋሺስት አስተሳሰብ
ህይወት የሚሰዉለት አላማ አይደለም እያሉ ነው፤ ይህም በአባታቸው ዘንድ
ክህደት እንደመፈጸም ይቆጠራል፡ እናታቸው እንደዚህ አባታቸውን ፊት
ለፊት ሲቃወሙ ማርጋሬት አይታ አታውቅም፡፡ ኤልሳቤትም የእናታቸው
አነጋገር ገርሟታል፡፡ ሁለቱም አባታቸውን ገርመም አደረጓቸው፤ ‹ምን ይል ይሆን?› በማለት፡፡ እሳቸው ግን ፊታቸው በርበሬ ከመምሰሉና በመጠኑ ከማጉረምረም በስተቀር በንዴት አልጮኹም፡፡

ቡና ለተሳፋሪዎች ሲታደል ማርጋሬት ከሳውዝ ሃምፕተን ከተማ ጥግ
መድረሳቸውን ተገነዘበች፡፡ ባቡር ጣቢያ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ
ይደርሳሉ፡ ኤልሳቤት እንደ ፎከረችው ታደርግ ይሆን?›
ባቡሩ ፍጥነቱን ቀነሰ፡፡
ኤልሳቤትም አስተናጋጁን ጠራችና ‹‹የሚቀጥለው ጣቢያ ላይ ወራጅ
ነኝ›› አለችው፤ ‹‹የሚቀጥለው ፉርጎ ውስጥ እመቤት ኤልሳቤት ኦክሰንፎርድ የሚል የተጻፈበት ሻንጣ አለልህ ይዘኽልኝ ና››

‹‹እሺ እመቤት›› አለ አስተናጋጁ፡

ማርጋሬት አባቷን ታያቸዋለች፡ ምንም ቃል ባይተነፍሱም ፊታቸው
በታመቀ ንዴት መወጠራቸውን ያሳብቅባቸዋል፡ ሚስታቸው እጃቸውን እባላቸው ጭን ላይ አስቀመጡና ‹‹እባክህ ሰው እንዳይሰማ ዝም በል፣ የኔ ውድ›› አሏቸው፡፡ ባላቸው ግን መልስ አልሰጡም፡፡

ባቡሩ ጣቢያው ጋ ደርሶ ቆመ::

ኤልሳቤት የተቀመጠችው በመስኮቱ በኩል በመሆኑ ማርጋሬትን አየት ስታደርጋት ማርጋሬትና ፔርሲ መንገድ ለቀቁላት፡፡ አባትም ቆሙ
ተሳፋሪው በሙሉ በአባትና በልጅ መካከል የተከሰተውን ፍጥጫ እንደ ትንግርት ያያል፡፡
ኤልሳቤት ተገቢውን ጊዜ መርጣለች፡ በዚህ ሁኔታ አባቷ ኃይል ተጠቅመው እንደማያስቀሯት አውቃለች፡፡ በፍርሃት ሰውነቷ እየራደ
ቢሆንም፤ ከሞከሩም ሌሎች ተሳፋሪዎች አይፈቅዱላቸውም።

አባቷ ፊታቸው በንዴት ቀልቷል፡፡ ዓይናቸው ተጎልጉሎ ሊወጣ የደረሰ
ይመስላል ኤልሳቤት በፍርሃት ብትንቀጠቀጥም ፈርጠም እንዳለች ነው፡፡

‹‹ከዚህ ባቡር ብትወርጂ ዳግም አይንሽን አላይም፤ መቃብሬም ላይ
እንዳትቆሚ›› አሏት።

‹‹እባክህ አባባ እንዲህ አትበል›› ስትል ማርጋሬት አለቀሰች፡ አባት አንድ ጊዜ ብለውታል፡፡ የተናገሩትን መልሰው ሊውጡት አይችሉም፡፡

እናት ይነፋረቃሉ፡

ኤልሳቤትም ‹‹ደህና ሁኚ እንግዲህ›› አለቻት እህቷን፡
ማርጋሬት እህቷ አንገት ላይ ተጠመጠመችና ‹‹መልካሙን ሁሉ
እንዲገጥምሽ እመኝልሻለሁ እታለም!››

‹‹ለአንቺም እንዲሁ›› አለችና ጀርባዋን መታ መታ አደረገቻት፡

ኤልሳቤት የወንድሟን ጉንጭ ሳመችና ወደ አባቷ ዞራ ድምጿ እየተንቀጠቀጠ ‹‹አባባ አትሰናበተኝም?›› ብላ እጇን ዘረጋች፡

አባትም ፊታቸው በጥላቻ ተጀቡኖ ‹‹ልጄ ከእንግዲህ ሞታለች፤ ልጄ አይደለሽም፧ ክጄሻለሁ›› አሏት፡

እናት ይሄን ሲሰሙ በተስፋ መቁረጥ እዬዬያቸውን አቀለጡት፡

የቤተሰቡ ውዝግብ እንዴት እንደሚጠናቀቅ ለማየት ተሳፋሪው በሙሉ
ትንፋሹን ውጦ ይጠባበቃል፡፡

ኤልሳቤት ፊቷን አዙራ ወደ በሩ አመራች፡፡

ማርጋሬት የአባቷ አድራጎት አበሳጭቷታል፡ ለአንዴ እንኳን እንዴት አይረታም! ስትል አሰበች፡፡ ኤልሳቤት ልጅ አይደለችም። እድሜ ልኳን አባት እናቷ የሚሉትን ሁሉ አሜን ብላ ስትቀበል አትኖርም፡ አባቷ ዕድሜ
ልካቸውን ሊቀጧት መብት የላቸውም፡፡ በቁጡ ባህሪያቸው ቤተሰቡን
ለያዩት፡ እዚያ በንዴት ጦፈው እንደ አበያ በሬ እንደተገተሩ ‹‹የተረገምክ!›፣
ጨቋኝ!›፣ ደደብ›፣ ብትላቸው በወደደች፡ ነገር ግን እንደልማዷ ከንፈሯን
ከመንከስ በስተቀር ምንም ቃል አልወጣትም፡፡
127 views17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 20:41:06 ማርጋሬት አባቷ ድንግርግር እንዳላቸው ከፊታቸው አነበበች፡፡ እሷ አገሬ ቆይቼ ፋሺስቶችን እዋጋለሁ ባለች ጊዜ የስድብ ናዳ ለማውረድ ቀላል ነበር፡፡ ነገር ግን ኤልሳቤት የእሳቸውን ሀሳብ አራማጅ ስለሆነች በቀላሉ
ውሳኔዋን ሊያጣጥሉት አልቻሉም፡፡

አስተናጋጁ እንደሄደ ‹‹ይህን በፍጹም አልፈቅድም›› አሉ አባት ይህ.አባባል ንግግራቸውን በሙሉ እንደሚያጠቃልልላቸው ሁሉ።

ማርጋሬት እህቷ ላይ አፈጠጠች፤ ‹ምን ትል ይሆን?› ብላ፡፡
ኤልሳቤትም ፍጹም እርጋታ በተላበሰ ሁኔታ ‹‹አባባ እንዳልሄድ ልትከለክለኝ አትችልም፤ አሁን ሃያ አንድ አመቴ ስለሆነ ያሻኝን ማድረግ እችላለሁ›› አለች፡
‹‹በኔ ስር እያለሽ አታደርጊውም›› አሉ አባት፡፡
‹‹ያንተ እርዳታ አሁን አያስፈልገኝም፤ ትንሽ ገንዘብ አለኝ››
‹‹ያም ሆነ ይህ አልፈቅድልሽም›› አሉ አባቷ፡

ማርጋሬት ኤልሳቤት በዚሁ የሚያበቃላት መሆኑን ማመን ጀምራለች፡፡
ኤልሳቤት አባቷን ማሸነፍ ይሁን ናዚዎችን መቀላቀል የሚያስደስታት ማወቅ አልቻለችም፡፡

ኤልሳቤት በፍርሃት ፊቷ አመድ ቢመስልም ቆራጥነት ይነበብባታል፡፡
ማርጋሬት የእህቷን ዓላማ ባትደግፍም ጽናቷን ታደንቃለች።

‹‹ወደ አሜሪካ የማትሄጂ ከሆነ ባቡር ውስጥ ለምን ገባሽ ታዲያ?››ሲል ፔርሲ ጠየቃት፡፡

‹‹ከሳውዝ ሃምፕተን የሚወስደኝ መርከብ ላይ ለመሳፈር አስቀድሜ
ቦታ ይዣለሁ›› አለች፡

‹‹ከዚች አገር ወደ ጀርመን የሚሄድ መርከብ አታገኚም›› አሉ አባት
በድል አድራጊነት መንፈስ፡፡

ማርጋሬት ደንገጥ አለች አዎ አታገኚም ኤልሲ›› አለች፡፡ በዚህ ምክንያት ውጥኗ ይከሽፍ ይሆን? አለች በሆዷ፡
ኤልሳቤት ረጋ ብላ ‹‹ከሳውዝ ሃምፕተን ሊዝበን (ፖርቹጋል) በመርከብ
እሄዳለሁ፡፡ እዚያ የሚገኝ ባንክ ገንዘብ አስተላልፌያለሁ ሆቴልም ቦታ ይዣለሁ›› አለች።

‹‹አንቺ እርጉም!›› አሉ አባት በንዴት ጮኸው፡፡ በሚቀጥለው ወንበረ
ላይ የተቀመጠው ሰው ጩኸቱን ሰምቶ ወደ እነሱ ዞረ።

ኤልሳቤት አባቷ ያሉትን እንዳልሰማች ሆና ‹‹ሊዝበንከ ከደረስኩ በኋላ
ወደ ጀርመን የሚሄድ መርከብ ላይ እሳፈራለሁ›› አለች።
‹‹ከዚያስ?›› ሲሉ ጠየቁ እናት፡
‹‹ከዚያማ በርሊን ጓደኞች እንዳሉኝ ታውቂያለሽ እማማ››
‹‹አዎ አውቃለሁ›› አሉ እናትም በሲቃ፡
ማርጋሬት ይህን ስታይ እናቷ የፈቀዱ መሰላት፡፡
ሲጮኹ ብዙ ሰዎች ምንድነው?› ምንድነው?› እያሉ ፊታቸውን ወደ እነሱ
አቅጣጫ ዞር ዞር አደረጉ፡፡

‹‹ቀስ ብለህ ተናገር የኔ ውድ›› አሉ እናት ባላቸውን፡፡

አባትም ‹‹ገና በርሊን እንደደረስሽ አፋፍሰው የሚመልሱልኝ ጓደኞች
አሉኝ›› አሉ ድምጻቸውን ዝቅ አድርገው፡፡

ማርጋሬት አፏን ያዘች: አባቷ ኤልሳቤት ጀርመን እንዳትገባ ማስከልከል ይችላሉ፡ በፋሺስት አገር መንግሥት ያሻውን ያደርጋል። ታድያ ኤልሳቤት ወደ ጀርመን ልትገባ ስትል ኬላ ላይ ያለው ተቆጣጣሪ ‹መግባት አትችይም ይላት ይሆን?› ስትል አሰበች ማርጋሬት፡

‹‹ጀርመኖች አይከለክሉኝም›› አለች ኤልሳቤት በሙሉ ልብ፡፡
‹‹እናያለና!›› አሉ አባት፡፡ ማርጋሬት አባቷ ይህን ሲሉ እርግጠኛ እንዳልሆኑ ከድምጻቸው አወቀች፡፡

‹‹አባባ ጀርመኖች እንኳን ደህና መጣሽ ነው የሚሉኝ›› አለቸ ኤልሳቤት፡ ‹‹ከእንግሊዝ አምልጬ እነሱን እንደተቀላቀልኩ ለዓለም በሙሉ ዜናውን ያበስራሉ ልክ የእንግሊዝ ቆሻሻ ፕሬሶች ታዋቂ የጀርመን አይሁዶች ከጀርመን አምልጠው ሲወጡ እንደሚያናፍሱት››

‹‹ስለአያታችን ፊሽቤን ካላወቁ ነው አንቺ የምትይው የሚሰራው››
አላት ፔርሲ፡

ኤልሳቤት ከአባቷ የሚሰነዘርባትን ጥቃት ለመመከት ታጥቃ ተነስታለች፡፡ ነገር ግን የፔርሲ መራራ ቀልድ አንገዳግዷታል፡፡ ‹‹ዝም በል
አንተ ልጅ!›› አለችና ማልቀስ ጀመረች።

አስተናጋጁ ሁለተኛውን ዙር ምግብ አመጣላቸው፤ ኮተሌትና ሰላጣ ቪኖም ቀዳላቸው:፡....

የቀጠላል
112 views17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 20:41:06 ‹‹መቼም እንዳልረበሸሽ ነው›› ስትል መለሰች ማርጋሬት
‹‹በፍጹም ራሼል ፊሽቤን ስለተባሉት አያታችሁ እያጫወተኝ ነው››
ማርጋሬት በፔርሲ አድራጎት አፈረች፡፡ ለእንግዳ ሰው ውሽት መንገር ብልግና ነው ብላው ነበር፡፡ ምን ይሆን ያላት ለዚች ምስኪን ሴት?› በፔርሊ አድራጎት ብትናደድም ከእናቷ እንደተማረችው የውሸት ፈገግታ ለሉሉ ብልጭ አደረገችላትና አልፋ ሄደች
ፔርሲ ሁልጊዜ ሸር መስራት ይወዳል፡፡ አሁን አሁንማ ደፋር እየሆነ መጥቷል፡ ቁመቱ እየጨመረ ድምጹ እየጎረነነ ነው፡ አሁንም አባቱን የሚፈራ ሲሆን ማርጋሬት ካገዘችው ግን መጋፈጡ አይቀርም፡ ሆኖም ፔርሲ አባቱን ፊት ለፊት የሚቃወምበት ጊዜ ሩቅ አይደለም፡፡ አባታቸው
ሴት ልጆቹን ሲያስፈራሩ ወንድ ልጃቸውንስ ያስፈራሩ ይሆን?› ማርጋሬት
እርግጠኛ አይደለችም::

ፉርጎው መጨረሻ ማርጋሬት በቅጡ
የማታውቃቸው ሰው
ተቀምጠዋል፡ ሰውየው ቁመተ ሎጋ፣ በትኩረት የሚመለከቱ፣ እንደ ቋንጣ
የደረቁ፣ የለበሱት ልብስ ተራና ጨምዳዳ በመሆኑ እዚህ ግሩም ልብስ
በለበሱና ሰውነታቸው ሞላ ባለ ሰዎች መካከል ሲታዩ አለ ቦታቸው የገቡ
መሆናቸው ያስታውቅባቸዋል፡ ፀጉራቸውን ባጭር የተከረከሙ ሲሆን
ሲያዩዋቸው የተጨነቁና ድንጉጥ ይመስላሉ፡፡

ማርጋሬት ሰውየው ላይ ዓይኗ ሲያርፍ እሳቸውም አይዋትና አስታወሰቻቸው፡፡ በአካል አይታቸው ባታውቅም ጋዜጣ ላይ ፎቶግራፋቸውን
አይታለች፡፡ ካርል ሀርትማን ይባላሉ፡ የጀርመን ሶሻሊስት አስተሳስብ
አራማጅና ሳይንቲስት ናቸው፡ እንደ ወንድሟ ደፈር አለችና ከሃርትማ ፊት ለፊት ተቀምጣ ራሷን አስተዋውቃ ወግ ጫረች፡ ሃርትማን ለረጅም ጊዜ የሂትለር ተቃዋሚ በመሆናቸው እንደ ማርጋሬት ባሉ ወጣቶች ዘንድ እንደ ጀግና ይቆጠራሉ፡

‹‹ለዓመት ያህል
የደረሱበት ሲጠፋ ሁሉም
ሰው ክፉ ነገር አግኝትዎታል ብሎ ገምቶ ነበር›› አለች፡ ማርጋሬት ከጀርመን ጠፍተው የሄዱ መስሏት ነበር እንደዛ ከሰውነት ጎዳና ወጥተው ሲታዩ ከገሃነም
ያመለጠ ሰው ነው የሚመስሉት፡፡

የቁም እስር ላይ ብቆይም የምርምር ስራዬን ግን ቀጥዬ ነበር››
‹‹ከዚያስ?››

‹‹አገሬን ጥዬ ወጣሁ›› አሉና አጠገባቸው የተቀመጠውን
አስተዋወቋት፡፡ ‹‹ጓደኛዬን ባሮን ጋቦንን ታውቂዋለሽ?›› አሏት፡፡
ማርጋሬት ባሮኑን በዝና ታውቃቸዋለች፡ ፊሊፕ ጋቦን ፈረንሳዊ የባንክ ባለቤት ሲሆኑ ጽዮናዊነትን ለማራመድ ሀብታቸውን ስለሚያፈሱ በእንግሊዝ
መንግሥት ዘንድ እጅግ የተጠሉ ናቸው፡፡ ብዙ ጊዜያቸውን በዓለም እየዞሩ አገሮች ከናዚ ጭቆና የሚያመልጡ ይሁዳውያንን በአገራቸው እንዲያስጠልሏቸው ይማጸናሉ፡፡ ማርጋሬት ለሀርትማን
የአይሮፕላን ቲኬት ባሮኑ
እንደከፈሉላቸው ጠረጠረች፡፡ የጋቦንን እጅ ጨበጠችና ትኩረቷን ወደ ሳይንቲስቱ አደረገች፡፡

‹‹ከአገር ወጥተው መሄድዎ በጋዜጣ ላይ አልወጣም››

‹ካርል ከአውሮፓ በደህና እስኪወጣ በምስጢር ይዘነው ነበር›› አሉ ባሮን፡፡

ከባሮኑ አባባል ናዚዎች ሰውየውን እየፈለጓቸው መሆኑን አረጋገጠች፡
‹‹አሜሪካ ውስጥ ታዲያ ምን ሊሰሩ ነው?››
‹‹አሜሪካ ፕሪንስተን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በፊዚክስ የትምህርት ዘርፍ
ውስጥ ስራ እጀምራለሁ፡፡›› ፊታቸውን ቅጭም አደረጉትና ‹‹አገሬን መልቀቅ አልፈልግም ነበር፡፡ ነገር ግን እዚያ ብቆይ ደግሞ ለናዚ ድል አስተዋጽኦ ማድረጌ አይቀርም ነበር፡፡››

ማርጋሬት ሃርትማን ሳይንቲስት መሆናቸውን ከማወቋ በስተቀር ስለ
ስራቸው ምንም አታውቅም፡፡ እሷን የሚስባት የፖለቲካ አቋማቸው ነበር፡ ‹‹ወኔዎ በብዙ ሰዎች ዘንድ እንደ ምሳሌ ይቆጠር ነበር›› አለች፡፡ ሃርትማን ንግግር ማድረግ በሚፈቀድበት ጊዜ ያደርጓቸው የነበሩትን ንግግሮች
የሚተረጉምላት ኢያን ነበር፡፡ ሳይንቲስቱ የማርጋሬትን ሙገሳ ብዙም ስላልወደዱት ንግግሯን አቋረጡና ‹‹ብቀጥል ኖሮ ደስ ባለኝ›› አሉ ‹‹በጅምር ትቼው መምጣቴ ይቆጨኛል፡››
ባሮን ጋቦንም ጣልቃ ገቡና ‹‹አልተውከውም እኮ ማድረግ ያለብህን ነው ያደረግኸው›› አሏቸው፡፡

ሃርትማን ጋቦን ያሉትን በመቀበል ራሳቸውን ነቀነቁ፡፡ በኋላም የፓን
አሜሪካን አየር መንገድ ሰራተኛ ምሳ ተዘጋጅቷል የሚቀጥለው
መመገቢያ ፉርጎ ሂዱና ቦታ ቦታችሁን ያዙ›› አለ፡፡

‹‹እንገናኛለን›› አሉ ሃርትማን ለመጀመሪያ ጊዜ ፈገግ ብለው ‹‹ከዚህ በኋላ ሶስት ሺህ ኪ.ሜ ይቀረናል፡››

ማርጋሬት ምግብ መመገቢያ ክፍል ሄዳ ከቤተሰቦቿ ጋር ተቀላቀለች:
እናትና አባት በአንድ በኩል ሶስቱ ልጆች ደግሞ በሌላ በኩል ተቀምጠዋል ፔርሲ እህቶቹ መካከል ተቀምጧል፡፡ማርጋሬት እህቷን የጎንዮሽ ታያታለች፡፡ መች ይሆን ያንን የቦምብ ናዳ የምታወርደው?

ኤልሳቤት አንድም ቃል ሳትተነፍስ በመስኮት ውጭ ውጪውን
ታያለች፡፡ ማርጋሬት ደግሞ በጭንቀት ትቁነጠነጣለች፡፡ እናት አንድ ችግር እንዳለ ጠርጥረው ኖሮ ‹‹ልጆች ምን ሆናችኋል?›› ሲሉ ጠየቁ።
ማርጋሬት ዝም ስትል ኤልሳቤት የሞት ሞቷን አንድ ነገር
ልነግራችሁ እፈልጋለሁ›› አለች፡

‹‹ምንድነው የኔ ማር›› አሉ እናት፡
ማርጋሬት በጭንቀት ምራቋን ዋጠች፡፡
‹‹አሜሪካ ከእናንተ ጋር አልሄድም›› አለች ኤልሳቤት።
‹‹ምንድነው የምትቀባጥሪው?›› አሉ አባት የሰሙትን ማመን
አቅቷቸው ‹‹ወደሽ ነው ትሄጃለሽ››
‹‹ከእናንተ ጋር አይሮፕላን ላይ አልሳፈርም›› አለች ኤልሳቤት ፈርጠም ብላ፡ ማርጋሬት
የእህቷን ፊት አነበበች ኤልሳቤት ስትናገር ድምጿ ባይንቀጠቀጥም
ፊቷ በጭንቀት መወጠሯን ያሳብቅባታል፡ ማርጋሬት ይህን
ስታይ ለእህቷ አዘነችላት፡፡

እናትም ቀበል አድርገው ‹‹ጅል አትሁኚ አልሲ አባትሽ ትኬት
ገዝቷል›› አሉ፡፡

ፔርሲም ጣልቃ ገባና ‹ካልሄድሽ ገንዘቡን ተመላሽ እናደርጋለን›› አለ
በዘወትር ቀልደኛነቱ፡፡

‹‹ዝም በል አንተ ጅል›› አሉ አባት ተቆጥተው፡
ኤልሳቤትም ‹‹አባባ መቼም በግድ ልትወስደኝ አትችልም፤ አየር
መንገዱም እኔን እየደበደብክ እንድትወስድ አይፈቅድልህም››
‹ኤልሳቤት እንዴት ዘዴኛ ነች? አለች ማርጋሬት በሆዷ አባቷን
በድንገት ምንም ሳያስቡት ምንም ማድረግ በማይችሉበት ጊዜ ያዘቻቸው እሷን በግድ አይሮፕላኑ ውስጥ ማሳፈር እንደማይችሉ ሁሉ ከእሷም ጋለመደራደር ሲሉ ወደ ኋላ መቅረት እንደማይችሉ አውቃለች አባቷ የፋሺስት ፓርቲ አባል በመሆናቸው የእንግሊዝ ፖሊሶች እያደኗቸው ነው።

የምሯን መሆንዋን ቢገነዘቡም አባት ገና አልተረቱም፡፡ ማንኪያቸው
ጣል አደረጉና ‹‹ወደኋላ ቀርተሽ ምን ልታደርጊ ነው?›› አሉ በመረረ
አነጋገር፡ ‹‹ውትድርና ልትገቢ ነው ልክ እንደ ዶሮ ጭንቅላት እህትሽ?››
ማርጋሬት ዶሮ ጭንቅላት በመባሏ ብትበግንም ጥርሷን ነክሳ ዝም
አለች፡፡

‹‹ጀርመን እሄዳለሁ›› አለች ኤልሳቤትም፡፡

አባት በድንጋጤ ምላሳቸው ተያያዘ፡፡

‹‹አላበዛሺውም›› ሲሉ እናት ልጃቸውን ጠየቋት፡

ፔርሲም ጣልቃ ገባና የአባቱን አነጋገር ወስዶ ‹ሜሪ ስቶፕስን ነው
ለዚህ ተጠያቂ የማደርገው›› አለ፡፡
‹‹ዝጋ›› አለችው ማርጋሬት ጎኑን በክርን ጎሸም አድርጋ፡

የምግብ ቤቱ አስተናጋጅ የበሉበትን ሰሃን እስኪያነሳና ጠረጴዛውን
እስኪጠራርግ ድረስ ጠበቁ፡፡ ወንድ ናት አደረገችው› አለች ማርጋሬት በሆዷ እሷ ድሮም ደፋር ናት ታዲያ ሃሳቧን ዳር ታደርሰው ይሆን?›
122 views17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 20:41:06 #ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_በወንዳየሁ_ንጉሴ


ከሳውዝ ሃምፕተን ወደ ፎየንስ (አየርላንድ)


ባቡሩ ጫካውን እየሰነጠቀ ወደ ሳውዝ ሃምፕተን ሲያመሩ የማርጋሬት
ኦክሰንፎርድ እህት ኤልሳቤት አንድ አስደንጋጭ ነገር ለእህቷ ነገረቻት
የኦክስንፎርድ ቤተሰቦች በአየር በራሪው በተያዘላቸው ልዩ ፉርጎ ውስጥ ተቀምጠዋል፡ ማርጋሬት ፉርጎው መጨረሻ ላይ ተቀምጣ በመስኮት ውጭ ውጩን ታያለች፡፡ አገሯን በችግሯ ጊዜ ጥላት መሄዷ ክፉኛ ቢያበሳጫትም አሜሪካ የመሄዷ ነገር ደግሞ በሌላ በኩል ደስታ አጭሮባታል፡
እህቷ ኤልሳቤት ከቤተሰቡ ነጠል ብላ ወደ ማርጋሬት መጣችና
‹‹እወድሻለሁ ማጊ›› አለቻት።
ማርጋሬት በእህቷ አባባል ልቧ ተነካ፡ በዓለም ላይ የሚካሄደውን የፖለቲካ አስተሳሰብ ልዩነትና ጦርነት መረዳት ከጀመሩ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ተቃራኒ አቋም በመያዝ በነገር መጠዛጠዛቸው አራርቋቸው ነበር።ማርጋሬት ይህ የአስተሳሰብ ልዩነት ከእህቷ ስለነጠላት ታዝን ነበር
እንደገና ጓደኛ ቢሆኑ በወደደች፡፡ ‹‹እኔም እወድሻለሁ እታለም›› አለቻትና እቅፍ አደረገቻት፡፡

ትንሽ ቆየችና ‹‹አሜሪካ ከእናንተ ጋር አልሄድም›› አለች ኤልሳቤት ማርጋሬት ይህን ስትሰማ ደነገጠች ‹‹እንዴት እባክሽ?››

‹‹ለእማማና አባባ እንደማልሄድ በቀጥታ ልነግራቸው ነው፤ ሃያ አንድ
ዓመት ስለሆነኝ ሊያስገድዱኝ አይችሉም››
ማርጋሬት የእህቷ ውሳኔ ትክክል ይሁን አይሁን አላወቀችም ‹‹የት ነው የምትሄጂው?››

‹‹ወደ ጀርመን››

‹‹ሊሆን አይችልም ኤልሲ›› አለች ማርጋሬት በፍርሃት፡፡ ‹‹ትሞቻለሽ››
‹ሶሻሊስቶች ብቻ አይደሉም ላመኑበት ዓላማ የሚሰዉት››

‹‹ግን ለፋሺዝም ብለሽ?››

‹‹ለፋሺዝም ብዬ አይደለም›› አለች
ኤልሳቤት፡፡ ዓይኗ ላይ እንግዳ አመለካከት ይነበባል፡፡ ‹‹በጥቁሮችና በክልሶች የመዋጥ አደጋ ላንዣበበበት ንፁህ ነጭ ዘር ብዬ ነው፡፡››

ማርጋሬትን ያበሳጫት እህቷን ማጣቷ ብቻ አይደለም፡፡ በዚህ ሰይጣናዊ ዓላማ ከእህቷ መለየቷ ነው ያሳዘናት፡ ሆኖም የቀድሞውን ጊዜ የፖለቲካ ጭቅጭቃቸውን አሁን ማንሳት አልፈለገችም፡ አሁን ያስጨነቃት ጉዳይ
የእህቷ ደህንነት ነው፡፡

‹‹እንዴት ትኖሪያለሽ ጀርመን ውስጥ?›› ስትል ጠየቀቻት

‹‹ገንዘብ አለኝ››

ማርጋሬት አያታቸው ሲሞቱ ያወረሷቸውን ገንዘብ አስታወስች፡፡ ገንዘቡ
ብዙ ባይሆንም ያኖራል፡
ማርጋሬት አንድ ነገር በሃሳቧ መጣ፡፡ ‹‹ሻንጣሽ ወደ ኒውዮርክ ተልኳል እኮ››

‹‹ኒውዮርክ የተላኩት ሻንጣዎች የተሞሉት በጠረጴዛ ልብስ ነው::
ልብሴን በሌላ ሻንጣ ሞልቼ ሰኞ ዕለት ልኬያለሁ።››

ማርጋሬት በእህቷ ብልህነት በእጅጉ ተደነቀች፡፡ ኤልሳቤት ሁሉንም
ነገር አቅዳ በትክክልና በምስጢር አከናውናለች፡፡ እሷ ከዚህ ቀደም ያደረገችው የማምለጥ ሙከራ እህቷ ካደረገችው ጋር ሲነጻጸር ምን ያህል የተውሸለሸለና በሚገባ ያልታቀደ እንደሆነ ተረዳች፡፡ እኔ ምግብ አልበላም እያልኩ ስተክዝ እሷ ግን ለጉዞዋ ቦታ ለመያዝና ዕቃ ለመላክ ትሯሯጥ ነበር፡
እህቷ የያዘችው የፖለቲካ አስተሳሰብ የተሳሳተ ቢሆንም ከእሷ በተሻለ
ሁኔታ መንቀሳቀስ መቻሏ የዝቅተኝነት ስሜት ፈጠረባት፡፡ ወዲያው ደግሞ ከእህቷ ጋር እስከ ወዲያኛው መለያየቷ ገባት፡፡ ምንም እንኳን ብዙም ባይቀራረቡም አብረው አድገዋል፡ ብዙ ጊዜ በሃሳብ ሲከራከሩና አንዷ ያንዷን አስተሳሰብ ስታጣምም ቢኖሩም ማርጋሬት ይሄም ሊቀርባት ነው: በችግር ጊዜ ይረዳዱ ነበር፡፡ ኤልሳቤት የወር አበባዋ በመጣ ቁጥር ህመም ሲሰማት ማርጋሬት አልጋ ላይ አስተኝታት የሚጠጣ ትኩስ ነገርና የሚነበብ መጽሔት ታመጣላታለች፡ የማርጋሬት ፍቅረኛ ኢያን ሲሞት መሪር ሀዘን ላይ ወድቃ የነበረ ጊዜ ምንም እንኳን ኢያንን ባትወደውም ታጽናናት ነበር
ማርጋሬት ዓይኗ በእምባ ተሞልቶ ‹‹ትተሽኝ ልትሄጂ ነው?›› አለቻት እህቷን፡፡

‹‹ግርግር አታብዢ›› አለች ኤልሳቤት ‹‹ገና አልነገርኳቸውም››
ማርጋሬት መነፋረቋን አቆመችና ‹‹መቼ ልትነግሪያቸው ነው?›› ስትል ጠየቀቻት፡፡
‹ መጨረሻው ደቂቃ ላይ፤ አንቺም እስከዚያው አታስነቂ››
‹‹እሺ እታለም›› ብላ የግድ ፈገግታ አሳየቻት፡
«አይ ማርጊ›› አለች ኤልሳቤት እምባ እየተናነቃት፡፡ ሳጓን ዋጥ
አደረገችና ‹‹እኔ እስከምረጋጋ ድረስ ሂጂና አዋሪያቸው::››

ማርጋሬት የእህቷን እጅ ጨበጥ አደረገችና ወደ መቀመጫዋ ተመለሰች
እናት የፋሽን መጽሔት ያገላብጡና የሚነገር ነገር ሲያገኙ ለአባት ያነባሉ ሎርድ ኦክሰንፎርድ ደግሞ ለማዳመጥ ፍላጎት የላቸውም፡፡ እናት
ግን ተስፋ ሳይቆርጡ ያነባሉ፡፡ ሎርዱ የንቀት ፊት ይነበብባቸዋል፡ ትልቋ
ልጃቸው የደገሰችላቸውን አያውቁም፡

ለማርጋሬት መንገር አንድ ነገር ነው፤ ለአባቷ መንገር ግን ሌላ ነገር.ነው፡፡ ኤልሳቤት በመጨረሻ ደቂቃ ለመንገር ድፍረት ታጣ ይሆናል፡፡
ማርጋሬትም ከዚህ ቀደም ከአባቷ ጋር እሰጥ አገባ ልትገጥም ነበር በኋላ
እጇን ሰጠች እንጂ፡

ኤልሳቤት ወንድ ወጥቷት ለአባቷ ከነገረች ወደ ጀርመን መሄዷ
የተረጋገጠ ላይሆን ይችላል፡ ሃያ አንድ አመት የሞላትና ገንዘብ ያላት
ብትሆንም እሳቸው ግን አቋመ ፅኑና ያሻቸውን ከማድረግ የማይመለሱ ሰው ናቸው፡ ኤልሳቤት ከፈቃዳቸው እንዳትወጣ ማቆም የሚችሉ ከሆነ
እንደሚያደርጉት ማርጋሬት አትጠራጠርም: በመርህ ደረጃ ኤልሳቤት
የፋሺስት ፓርቲን ብትቀላቀል አይጠሉም፤ ነገር ግን ትዕዛዛቸውን ጥሳና ቤተሰቡን ትታ ብትሄድ ግሥላ እንደሚሆኑ ጥርጥር የለውም፡፡

ማርጋሬት ከአንዴም ሁለት ሶስቴ ከአባቷ ጋር ተጣልታለች። ያለሳቸው
ፈቃድ መኪና መንዳት በተማረች ጊዜ ተቆጥተዋታል፡ የእርግዝና መከላከያ ፈር ቀዳጅ የሆነችው የሜሪ ስቶፕስን ንግግር ለመስማት መሄዷን ያወቁ ጊዜ.ፊታቸው በንዴት በርበሬ መስሎ ነበር፡ አባቷ ሳያውቁ ካላደረገች በስተቀር ፊት ለፊት ተጋፍጣ እንደማይሆንላት ታውቃለች፡፡ የአስራ ስድስት ዓመት ኮረዳ ሳለች ከአጎቷ ልጅ ጓደኞች ጋር ትምህርት ቤት ሲዘጋ ሽርሽር ልሂድ
ብላ ስትጠይቃቸው አልፈቀዱላትም፡፡ ያልፈቀዱላት ከሴቶችም ከወንዶችም.እንዳትቀላቀል ነው: ትልቁ ጦርነት የነበረው ትምህርት ቤት ልሂድ ያለች
ጊዜ ነበር፡ ትምህርት ቤት ለመግባት እንዲፈቀድላት ብትለምንም፣ ብታለቅስም ወይም ብታኮርፍም አባት ጆሮ ዳባ ልበስ አሉ፡ ‹‹ትምህርት ለሴቶች ምንም አያደርግላቸውም ሴቶች ቤት ውስጥ አድገው ባል
አግብተው መቀመጥ ነው ያለባቸው›› ነበር ያሏት፡፡

ማርጋሬት እረፍት አጣች፡ አንድ ነገር አገኝ ብላ ተነሳችና ፉርጎው
ውስጥ ተንጎራደደች፡ የሰማይ በራሪው ጀልባ ተሳፋሪዎች ሲታዩ ገሚሶቹ
የተከፉ ከፊሎቹ የተደሰቱ ይመስላሉ፡፡

ከተሳፋሪዎቹ መካከል አንዲት በዓለም የታወቀች አሜሪካዊት ኮከብ የፊልም ተዋናይ ስላለች ሁሉም ስለእሷ በሹክሹክታ ያወራል፡ ሉሉ ቤል ትባላለች፡ ፔርሲ ከሷ ጋር ቁጭ ብሎ ልክ ረጅም ጊዜ እንደሚተዋወቁ ሁሉ
ያወራታል፡ ማርጋሬት ከተዋናይዋ ጋር ማውራት በወደደች፤ ነገር ግን
ዓይኗን በጨው አጥባ ሄዳ ልታወራት አልደፈረችም፡፡ ፔርሊ ዓይን ቀቅሎ
የበላ ነው፡፡

ሉሉ ቤል በፊልም ስትታይ ወጣት ብትመስልም በአካል ሲያይዋት ግን ያረጀች ትመስላለች፡ አንድ አርባ ዓመት ሳይሆናት አይቀርም ስትል ማርጋሬት አሰበች ምንም እንኳን ፊልሞቿ ላይ ወጣቶችንና በቅርብ ያገቡ
ሴቶች ገጸ ባህሪ ወክላ ብትጫወትም፡፡ ምንም ሆነ ምን አሁንም ውብ
ሽንቃጣና ተግባቢ ናት፡፡

ማርጋሬት ሉሉን ስታይ ፈገግ አለች፡፡ ሉሉም ‹‹ታናሽ ወንድምሽ ያጫውተኛል›› አለች፡፡
185 views17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ