የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ስፖርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
14.97K
የሰርጥ መግለጫ
የአፄዎቹ ፈጣን የመረጃ ምንጭ
The oldest and most popular Fasil Kenema Sport Club was established in 1960. This legendary Emperors Club has been around for 55 years.
🔴 ለአስተያየት @FASILKFCBOT
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
0
4 stars
1
3 stars
1
2 stars
0
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8
2023-05-08 19:59:10
የጨዋታ 178 ውጤት !
@FASILSC
4.5K viewsedited 16:59
2023-05-08 19:47:52
84'
ፋሲል ከነማ 1-1 አርባምንጭ ከተማ
78' በዛብህ መለዮ | 41' ተመስገን ደረሰ
@FASILSC
4.2K views16:47
2023-04-26 20:03:12
የደረጃ ሰንጠረዥ ከጨዋታ 164 በኋላ !
@FASILSC
2.6K viewsedited 17:03
2023-04-26 19:53:25
ፋሲል ከነማ አሸንፏል !
በቤት ኪንግ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ሀያ አንደኛ ሳምንት መርሐ ግብር ፋሲል ከነማ ከ ሀዋሳ ከተማ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።
- የአፄዎቹን የማሸነፊያ ግብ የሀዋሳ ከተማው ግብ ጠባቂ መሐመድ ሙንታሪ በራሱ ግብ ላይ ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።
- ፋሲል ከነማ ማሸነፉን ተከትሎ በሊጉ ደረጃ ሰንጠረዥ ሰላሳ ነጥቦችን በመሰብሰብ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ሀዋሳ ከተማ በሰላሳ አንድ ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
- በቀጣይ የሊጉ መርሐ ግብር ፋሲል ከነማ ከ ሀድያ ሆሳዕና እንዲሁም ሀዋሳ ከተማ ከ ሲዳማ ቡና ይገናኛሉ።
@FASILSC
2.7K views16:53
2023-04-26 19:51:26
የጨዋታ 164 ውጤት !
@FASILSC
2.5K viewsedited 16:51
2023-04-26 19:46:32
80'
ፋሲል ከነማ 1-0 ሀዋሳ ከተማ
58' መሐመድ ሙንታሪ (በራስ ላይ)
@FASILSC
2.4K views16:46
2023-04-26 19:22:44
65'
ፋሲል ከነማ 1-0 ሀዋሳ ከተማ
58' መሐመድ ሙንታሪ (በራስ ላይ)
@FASILSC
2.2K views16:22
2023-04-26 18:48:42
እረፍት
ፋሲል ከነማ 0-0 ሀዋሳ ከተማ
@FASILSC
2.2K views15:48
2023-04-24 10:10:05
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 20ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎቹ !
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 20ኛ ሳምንት በተደረጉ ጨዋታዎች ሰባት ጨዋታዎች በመሸናነፍ አንድ ጨዋታ በአቻ ውጤት ሲጠናቀቅ 15 ጎሎች ተቆጥረዋል። በሳምንቱ 39 ተጫዋቾችና የቡድን አመራሮች በቢጫ ካርድ ሲገሰፁ አንድ የቡድን አመራር ቀይ ካርድ ተመልክቷል።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ እሁድ ሚያዝያ 15 2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የተደረጉ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያ(ዎች)ከዳኞች እና ከታዛቢዎች የቀረቡለትን የዲሲፕሊን ሪፖርት ከመረመረ በኋላ የተለያዩ ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
በተጫዋች እና ቡድን አመራሮች ደረጃ በተላለፉ ውሳኔዎች ተሾመ ሸዋነህ(አርባምንጭ ከተማ) የክለቡ የቡድን መሪ ሆነው የዳኛን ውሳኔ በመቃወምና ቁሳቁስ በመወርወር ከጨዋታ ሜዳ የተወገዱ ስለመሆኑ ሪፖርት
የቀረበባቸው ለፈፀሙት ጥፋት በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ደንብ መሰረት 3 ጨዋታ እንዲታገዱና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 10000 /አስር ሺ/ እንዲከፍሉ እንዲሁም በተጫዋቾች ምንይሉ ወንድሙ(መቻል) እና ሱሌማን ሀሚድ(ቅዱስ ጊዮርጊስ) 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ በመመልከታቸው በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገዱና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍሉ ተወስኗል።
በክለቦች ደረጃ በታዩ ሪፖርቶች በሶስት ክለቦች ላይ የተለያዩ ውሳኔዎች ተላልፈዋል። አርባምንጭ ከተማ በሳምንቱ ጨዋታ የክለቡ ስድስት ተጫዋቾች በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል ፥ ኢትዮጵያ ቡና በተጫወተበት እለት የክለቡ ደጋፊዎች የእለቱን ዳኛ አፀያፊ ስደብ ስለመሳደባቸው ሪፖርት በመቅረቡ የክለቡ ደጋፊዎች ለፈፀሙት ጥፋት ክለቡ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት ብር 50000/ሃምሳ ሺህ/ እንዲከፍል ፥ ቅዱስ ጊዮርጊስ በተጫወተበት እለት የክለቡ ደጋፊዎች በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ስታድየም ጥላ ፎቅ የሚገኙትን 22/ሃያ ሁለት/የፕላስቲክ ወንበሮችን ስለመስበራቸው ሪፖርት የተደረገ ሲሆን ክለቡ የተሰበሩትን ወንበሮች እንዲያሰራ ወይም የዩኒቨርስቲው አሰተዳደር የሚያቀርበውን የንብረትን ዋጋ እንዲከፍል ተወስኗል።
@FASILSC
1.8K views07:10
2023-04-23 18:22:52
ሻጭና ገዥ የተነፋፈቁትን ያህል የሚገናኙበት አፄዎቹ የንግድ ትርዒትና ባዛር በጎንደር ኮሌጅ ማዞሪያ(ዕዉቀት በር)በእለተ ማክሰኞ በድምቀት ይከፈታል
ምርትና አገልግሎትዎን ለመሸጥ ወይ ለማስተዋወቅ ሀሳብ ካለዎ ቅዳሜና ዕሁድን ጨምሮ ዳሽን ባንክ ዋናዉ መስሪያ ቤት 3ኛ ፎቅ በሚገኘዉ የደጋፊዎች ማህበር ቢሮ በመገኘት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን
ለበለጠ መረጃ 0993369033
#እኛኮ_የአፄዎቹ_ደጋፊዎች_ነን
@FASILSC
2.6K viewsedited 15:22