Get Mystery Box with random crypto!

የደ/ም/ሰ/ም/ቅ/ማርያምና ቅ/ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል እውቀት ብርሃን ሰ/ት/ቤት

የቴሌግራም ቻናል አርማ ewketbirhan — የደ/ም/ሰ/ም/ቅ/ማርያምና ቅ/ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል እውቀት ብርሃን ሰ/ት/ቤት
የቴሌግራም ቻናል አርማ ewketbirhan — የደ/ም/ሰ/ም/ቅ/ማርያምና ቅ/ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል እውቀት ብርሃን ሰ/ት/ቤት
የሰርጥ አድራሻ: @ewketbirhan
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.88K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የደ/ም/ሰ/ም/ቅ/ማርያምና ቅ/ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል እውቀት ብርሃን ሰ/ት/ቤት መንፈሳዊ ጽሑፎችን፣ የሰ/ት/ቤታችንን የአገልግሎት እንቅስቃሴ እንዲሁም ወቅታዊ የቤተ-ክርስቲያን መረጃዎችን የምንለቅበት የቴሌግራም ገፃችን ነው።
ይቀላቀሉን👉 https://t.me/EwketBirhan

ለማንኛውም ሀሳብ እና አስተያየት
👉 @meaZina19 ይላኩልን

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-26 20:28:44
4. ቅኔ ማኅሌት ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲገቡ የሚገኘው የመጀመሪያው ክፍል ነው፡፡ ቀሳውስትና ዲያቆናት በመንፈቀ ሌሊት ሰዓታት የሚቆሙበት፣ ኪዳን በነግህ የሚያደርሱበት በየተኛው አቅጣጫ ነው?
Final Results
40%
ሀ. በምዕራብ በኩል
32%
ለ. በመስዕ (በሰሜናዊ ምሥራቅ) በኩል
10%
ሐ. በሌብ (በደቡባዊ ምሥራቅ) በኩል
18%
መ. በምሥራቅ በኩል
111 voters563 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, 17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 20:27:25
3. ላም ጠባቂ የነበረና የእስራኤል ንጉሥ የዮአስ ልጅ ኢዮርብዓም እግዚአብሔርን ባለመፍራቱ በሰይፍ እንደሚሞት እስራኤልም እንደሚማረክ ትንቢት የተናገረው ደቂቀ ነቢያት ማን ነው?
Final Results
8%
ሀ. ነቢዩ ዮናስ
23%
ለ. ነቢዩ ኤርሚያስ
24%
ሐ. ነቢዩ ሚልክያስ
44%
መ. ነቢዩ አሞጽ
98 voters522 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, 17:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 20:26:03
2. ንፍቅ ዲያቆን በቅዳሴ ወቅት ከማያነባቸው ቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ አንዱ የቱ ነው?
Final Results
14%
ሀ.የያዕቆብ መልእክት
38%
ለ. ወደ ዕብራውያን ሰዎች
32%
ሐ. የጴጥሮስ መልእክታት
17%
መ. የይሁዳ መልእክት
103 voters481 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, 17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-23 13:07:24 የሐምሌ 17 ምስባክ- "ያዐርግ ደመናተ እምአፅናፈ ምድር"
በመ/ር ላአከ ማርያም መልአከ ጽዮን
ሰብስክራይብ በማድረግና ለሌሎች በማጋራት አገልግሎቱን ይደግፉ!


197 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, 10:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 16:18:50 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
#ቅዱስ_ኤፍሬም_ሶርያዊ
ቅዱስ ኤፍሬም በ306 ዓ.ም በግንቦት 1 ቀን ተወለደ፡፡ ይህም ቅዱስ ከዋክብትን ከሚያመልኩ ሰዎች ሀገር ነው፡፡ አባቱም የክርስቶስን አምላክነት የሚጠላ የጣዖት ካህን ነበር፡፡ በዚያን ጊዜም ቅዱስ ኤፍሬም የእግዚአብሔር ቸርነት አነሳስቶት እንዲሁም ለክርስትና እምነት ከልጅነቱ ጀምሮ ዝንባሌ ስለነበረው በአቅራቢያው የነበረ የንጽቢን ኤጲስ ቆጶስ ወደ ሆነው ወደ አባ ያዕቆብ ሄዶ የክርስትና ሃይማኖት በሚገባ አስተምሮታል፤ በተወለደ በ18 ዓመቱም አጠመቀው፡፡
ቅዱስ ኤፍሬም ከተጠመቀ በኋላ ሕይወቱ ኹሉ የምነና፣ የምንኩስና ሕይወት ነበር፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ በአቅራቢያው በሚገኝ ገዳም ሄዶ የገዳሙን ኃላፊ (አበምኔቱን) በማስፈቀድ አነስተኛ ጎጆ ሠርቶ በጾምና በጸሎት ተወስኖ በብሕትውና መኖር ጀመረ፡፡ ለገዳሙ በሚያስፈልገው ከባድ ተግባር ኹሉ የጉልበት ሥራ ይሠራ ነበር፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም በሕይወቱ ኹሉ ገንዘብ በእጁ ነክቶ አያውቅም፤ የግል ሀብትና ንብረትም ኖሮት አያውቅም፡፡ ኒቅያ በሚባል ከተማ የሦስት መቶ ዐስራ ስምንት አባቶች ኤጲስ ቆጶሳት ጉባኤ በተደረገ ጊዜ ያዕቆብ አንዱ ስለነበረ ለኒቅያ ጉባኤ ሲሄድ ቅዱስ ኤፍሬምን አስከትሎት ሄዶ ነበር፡፡ በዚያም አርዮስን አውግዘው ሃይማኖትን መልሰው ከተመለሱ በኋላ ቅዱስ ኤፍሬም በዚያች ሌሊት ከምደር እስከ ሰማይ የሚደርስ የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ አየ፤ ከዚህ ራዕይም የተነሳ አደነቀ፡፡ ይገለጥለት ዘንድ ወደጌታ ቢጸልይ ‹‹ይህ የቂሣርያ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ባስልዮስ ነው›› የሚል ቃል ከሰማይ ወደ እርሱ መጣ፡፡
ቅዱስ ኤፍሬምም ያየው ዘንድ ወድዶ ወደ ቂሣርያ ሀገር ተጓዘ፤ በደረሰም ጊዜ ወደ ቤተክርስቲያን ገብቶ በማዕዘኑ በኩል ቆመ፡፡ ቅዱስ ባስልዮስንም ወንጌልን ሊያነብ በወጣ ጊዜ ዋጋው ብዙ የኾነ ከወርቅ የተሠራ ልብሰ ተክህኖ ለብሶ አየው፡፡ ሦስት ምልክቶችንም እስኪያይ ድረስ ተጠራጠረ፤ ምልክቶቹም እነዚህ ናቸው፦
፨ ነጭ ርግብ መጥታ በራሱ ላይ አረፈች፤
፨ ሁለተኛም በልብሱ ላይ የሚያርፉ ተዋሕሲያን ይቃጠሉና ይረግፉ ነበር፤
፨ ሦስተኛም ከአፉ የእሳት ነበልባል ወጥቶ በምእመናን ላይ ያድር ነበር።
በኋላም ቅዱስ ባስልዮስ ቅዱስ ኤፍሬምን በስሙ ጠራውና እርስ በርሳቸው ሰላምታ ተለዋወጡና በአስተርጓሚ ይነጋገሩ ጀመር። የየራሳቸውንም ቋንቋ ይገለጽላቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እንዲጸልዩ ቅዱስ ኤፍሬም ቅዱስ ባስልዮስን ለመነው። በጸለዩ ጊዜ ተገልፆላቸው ያላስተርጓሚ ተነጋገሩ።
ከዚያም ቅዱስ ኤፍሬምን ዲቁና ሾመው፤ ከጥቂት ወራትም በኋላ ቅስና ሾመው፡፡ ከእርሱም ብዙ ቱርፋቶች ተገለጡለትና በመንፈሳዊ ተጋድሎ ኹሉን ተጋደለ። ቅዱስ ኤፍሬም በቅዱሳት መጻሕፍት ባለው ዕውቀት እንዲሁም ለኦርቶዶክስ ሃይማኖት ባላው ቅንዓትና ለምንኩስና በነበረው ታማኝነት እጅግ የታወቀ ነበር። በ363 ዓ.ም የንጽቢን ግዛት በጦርነት ወደ ፋርስ ግዛት በተዛወረች ጊዜ ቅዱስ ኤፍሬም የሶርያ ግዛትና የክርስቲያን ሀገር ወደ ኾነችው ወደ ኤዴሳ ሄዶ መኖር ጀመረ። ኤደሳም በዚያን ጊዜ ከፍተኛ የመንፈሳዊ ትምህርት ማዕከል ነበረች፡፡ ቅዱስ ኤፍሬምም መንኖ በኤዴሳ ከተማ አጠገብ በምትገኝ አንድ ታላቅ ዋሻ ውስጥ በብሕትውና ይኖር ጀመር። በዚያም ተቀምጦ በምንኩስና ሕይወት ላይ ከሚያደርገው ተጋድሎ ሌላ ብዙ መጻሕፍትን በመጻፍና ስለጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስና ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የውዳሴ መዝሙር በመጻፍ ወርቃማ ጊዜ ያሳልፍ ነበር።
ቅዱስ ኤፍሬም እጅግ ብዙ መጻሕፍትን ደርሷል፡፡ ከድረሰቶቹ አብዛኛዎቹ ስለ ቅዱሳት መጻሕፍት የአንደምታ ትርጓሜና በመጻሕፍቱ ላይ የተመሠረቱ ንግግሮችና ድርሰቶች ናቸው። እንዲሁም ለክርስትና ሃይማኖት በመከራከር በአይሁድና በአረማውያን ላይ በሺህ የሚቆጠሩ ድርሰቶችን ጽፏል። ስለ መናፍቃንም ብዙ መጻሕፍትን ጽፏል። ቅዱስ ኤፍሬም ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ታላቅ ፍቅርና አክብሮት ስለነበረው ስለ እርሷ ብዙ ውዳሴዎችንና ድርሰቶችን ደርሷል። በኢትዮጵያ እጅግ የሚታወቀው በሳምንቱ ቀናት በእያንዳንዱ ቀን ለእመቤታችን የሚቀርብ ውዳሴና ምስጋና የጻፈው ነው። ቅዱስ ኤፍሬም ከደረሳቸው ድርሰቶች ለኢትዮጵያ ወደ ግዕዝ የተተረጎመው እነዚህ የሰባቱ ቀናት ውዳሴና ምስጋና ሲሆን በሃይማኖተ አበው ውስጥ በኤፍሬም ሶርያዊ ስም አንድ ድረሳን ይገኛል። ቅዱስ ኤፍሬም አቤቱ የጸጋህን ማዕበል ግታልኝ እስኪል ድረስ ድርሳናትን ደርሷል።
የቅዱስ ኤፍሬም የዕረፍቱ መታሰቢያ ሐምሌ 15 ቀን ነው። በረከቱ በሁላችን ላይ ይሁን አሜን!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
ምንጭ፦ መድበለ ታሪክ
@EwketBirhan
339 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, 13:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 09:41:39
መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ዘውዲቱ መሸሻ የሕጻናትና ቤተሰብ መርጃ
እሑድ ሐምሌ 24 ከቅዳሴ በኋላ
▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭
ገጾቹን በመቀላቀል እና ለሌሎችም በማጋራት አገልግሎቱን ይደግፉ!!
ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/UCyuEXl7Cq7UcFLhNeTTIeEQ
ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@ewketbirhan
ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡ t.me/EwketBirhan
የፎቶ ማጋርያ፡ t.me/PhotoEwketBirhan
ፌስቡክ ገፅ፡ fb.me/EwketBirhan21
500 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, 06:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 21:37:18 ለክረምት የመደበኛ የማጠናከሪያ ትምህርት ለመማር ፍላጎት ያላችሁ ።

የሚሰጠው የቀለም ትምህርት

እንግሊዝኛ
ሒሳብ
ሳይንስ
ሕብረተሰብ
ፊዚክስ
ባዮሎጂ
ኬሚስትሪ
life skill
ስዕል እና ዕደ ጥበብ

ከ4ኛ-8ኛ ክፍል ሲሆን መደበኛ ትምህርቱ የሚሰጠው ከሰኞ-አርብ ከጠዋቱ 2፡30-6፡30 ሰዓት (በሰ/ት/ቤታችን አዳራሽ ነው)

እስከ ሐምሌ 17ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ከምሽቱ 11፡00-1፡00 ሰዓት በጎ አድራጎት ን/ክፍል መመዝገብ ትችላላችሁ።

ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፦ +251917554516
+251946710671
+251912070899


#የእውቀት_ብርሃን_ሰንበት_ትምህርት_ቤት
@Ewketbirhan
434 viewsAklilu, edited  18:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 19:32:03
መጽሔተ ሕይወት (የሕይወት መስታወት)
ልዩ የሥልጠና መድረክ
◃▸◃▸◃▸ መንፈሳዊ ሕይወት ◃▸◃▸◃▸
እሑድ ሐምሌ 17 ከ3:00 ጀምሮ በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ
▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭
ገጾቹን በመቀላቀል እና ለሌሎችም በማጋራት አገልግሎቱን ይደግፉ!!
ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/UCyuEXl7Cq7UcFLhNeTTIeEQ
ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@ewketbirhan
ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡ t.me/EwketBirhan
የፎቶ ማጋርያ፡ t.me/PhotoEwketBirhan
ፌስቡክ ገፅ፡ fb.me/EwketBirhan21
706 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, 16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-18 17:30:15 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
#ቅዱስ_ሚካኤል_ወደ_ንጉሥ_ሕዝቅያስ_እንደተላከ
የአካዝ ልጅ ሕዝቅያስ በይሁዳ በነገሠ በ14 ዓመት የፋርስ ንጉሥ ሰናክሬም ወደ ኢየሩሳሌም ዘመተ፡፡ እስራኤላውያንም ኃጢአት እየሠሩ ጣዖት እያመለኩ እግዚአብሔርን አሳዝነውት ነበርና በእግዚአብሔር ፈቃድ ታዞ መጥቷል፤ (2ነገሥ 18፥9-37)፡፡ ሰናክሬም ራፋስቂስንና ራፋስሮስን ላካቸው፤ እነርሱም ከቅጥሩ ሆነው ‹‹የሕዝቅያስ ብላቴና›› ብለው ሲጣሩ ሕዝቅያስ ደግሞ ዮአስን፣ ሳምናስንና ኤልያቄምን ልኮ ‹‹የሚናገሩትን ብቻ ሰምታችሁ ኑ›› ብሎ ላካቸው፡፡
ሰናክሬም የላካቸው እነዚያ ሁለቱ መልእክተኞች ‹‹በማን ተማምነሀል? ሰማርያን እንዳጠፋሁ ኢየሩሳሌምንም አጠፋታለሁ፤ ፈጣሪ አለኝ የምትለው ያድንህ መስሎህ ከሆነ ድንኳንህን ቆልፈህ ደጅህን ዘግተህ ቆየኝ ብሎሀል በሉት›› ብለው ሕዝቅያስ ለላካቸው መልእክተኞች ነገሯቸው፡፡ የሕዝቅያስ መልእክተኞችም ገብተው ነገሩት፤ እርሱም ‹‹እንዲህ ያለ ጠላት በጸሎት እንጂ በጦር አይመለስምና ሄዳችሁ ለነቢዩ ለኢሳይያስ ንገሩት›› ብሏቸው ሄደው ለነቢዩ ኢሳይያስ ነግረውታል፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስም ሲጸልይ የሚሆነው ተገልጾለት ‹‹አይዞህ ከከተማ ሳይደርስ በመጣበት ይመለሳል›› ብሎ ወደ ሕዝቅያስ ላከ፡፡ ከዚህ በኋላ ሰናክሬም ኢየሩሳሌምን አልፎ ለኪሶን በምትባል ሥፍራ ሰፈረ፤ ሌሊቱን ቅዱስ ሚካኤል ሰይፉን መዞ ቢታያቸው ብዙ ሺህ ሠራዊት አንቀላፍተው/አልቀው ተገኝተዋል፡፡ ሰናክሬምንም መላእክት የነጋሪት ድምጽ የፈረስ ኮቴ እያሰሙት ‹‹ሕዝቅያስ መጣብኝ›› ብሎ ልብሱን ዘውዱን ጥሎ ወደ ሀገሩ ተመልሷል፡፡ የሰናክሬምን ዘውድ ነቢያት አግኝተውት ለሕዝቅያስ አቀዳጅተውታል፡፡
ሰናክሬም ከቤቱ ደርሶ ለጣዖቱ ሲሰግድ ልጆቹ ‹‹ሠራዊቱን ወዴት ጥለህ መጣህ?›› ብለው ቢጠይቁት ‹‹የሕዝቅያስ አምላክ ፈረደብኝ፤ ሞቱ›› አላቸው፡፡ ኃያላኑን ሁሉ ይዞ ሄዶ ነበርና ልጆቹ ‹‹ያን ያህል ሠራዊት አጥፍተህ ዳግመኛ በማን ላይ ልትነግሥ መጣህ?›› ብለው ከጣዖቱ ሥር ቀጥቅጠው ገድለውታል፤ (ውድ አንባብያን ሁለተኛ ነገሥት ከምዕራፍ 18 እስከ 20 ያለውን ሙሉውን ያንብቡት)፡፡
ሰናክሬም እንዲያጠፋ ከእግዚአብሔር ታዞ ከመጣ ለምን እንዲህ ሆነ ቢሉ ኃጥአኑን ሊያጠፋ እንጂ በእግዚአብሔርና በደጉ ንጉሥ ላይ እንዲገዳደር አልነበረምና ነው፡፡ አንድም ሕዝቅያስ ‹‹ተመለስልኝ›› ብሎ ወርቅና ብር ቢሰጠውም ‹‹በማን ተማምነሃል?›› ብሎ ዘብቶበታልና ነው፡፡ ይህ የተፈጸመው ሐምሌ 12 በመሆኑ ዕለቱ ቅዱስ ሚካኤል ለሕዝቅያስ ያደረገለት ተአምር ይታሰብበታል፡፡ ቅዱስ ሚካኤል ንጉሥ ሕዝቅያስን እንደረዳው እኛንም ይርዳን አሜን!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
ምንጭ፦ መጽሐፍ ቅዱስ
@EwketBirhan
483 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, 14:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-18 13:14:15
415 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, edited  10:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ