Get Mystery Box with random crypto!

የደ/ም/ሰ/ም/ቅ/ማርያምና ቅ/ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል እውቀት ብርሃን ሰ/ት/ቤት

የቴሌግራም ቻናል አርማ ewketbirhan — የደ/ም/ሰ/ም/ቅ/ማርያምና ቅ/ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል እውቀት ብርሃን ሰ/ት/ቤት
የቴሌግራም ቻናል አርማ ewketbirhan — የደ/ም/ሰ/ም/ቅ/ማርያምና ቅ/ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል እውቀት ብርሃን ሰ/ት/ቤት
የሰርጥ አድራሻ: @ewketbirhan
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.88K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የደ/ም/ሰ/ም/ቅ/ማርያምና ቅ/ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል እውቀት ብርሃን ሰ/ት/ቤት መንፈሳዊ ጽሑፎችን፣ የሰ/ት/ቤታችንን የአገልግሎት እንቅስቃሴ እንዲሁም ወቅታዊ የቤተ-ክርስቲያን መረጃዎችን የምንለቅበት የቴሌግራም ገፃችን ነው።
ይቀላቀሉን👉 https://t.me/EwketBirhan

ለማንኛውም ሀሳብ እና አስተያየት
👉 @meaZina19 ይላኩልን

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-29 18:59:41 የደ/ም/ሰ/ም/ቅ/ማርያምና ቅ/ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል እውቀት ብርሃን ሰ/ት/ቤት pinned a photo
15:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 18:59:31
<><><> ነቅዐ ሕይወት <><><>
284 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, 15:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 18:52:41 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

              የአገልግሎት ጥሪ

ለእውቀት ብርሃን ሰንበት ት/ቤት አባላት በሙሉ


የ2014 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል የመዝሙር ጥናት በታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም ስለተጀመረ ካቴድራላችንን ወክላችሁ መሳተፍ የምትፈልጉ አባላት በአባላት እንክብካቤ እና ግንኙነት ክፍል ወይም በስልክ ቁጥር +251938035698/+251913166536 በመደወል መመዝገብ ትችላላችሁ።

#እውቀት_ብርሃን_ሰንበት_ትምህርት_ቤት
@EwketBirhan
357 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, edited  15:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 16:16:55
እንኳን ለእናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በዓለ ዕረፍት አደረሳችኹ!!
  ➣➣➣ ➢➢➢
ታላቅ የንግስ በዓል ነገ ማክሰኞ ነሐሴ 24 ቀን 2014 ዓ.ም በደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምሕረት ቅ/ማርያምና ቅ/ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል
     ▭▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭▭
ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/UCyuEXl7Cq7UcFLhNeTTIeEQ
ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@ewketbirhan
ፌስቡክ ገፅ፡ fb.me/EwketBirhan21
ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡ t.me/EwketBirhan
የፎቶ ማጋርያ፡ t.me/PhotoEwketBirhan

  ➣➣➣ እውቀት ብርሃን ሰ/ቤት ➢➢➢
566 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, edited  13:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 14:32:54 በዚህም ተደስታ ልብሰ ምንኲስናዋን ይዛ፣ የመጨረሻውን የሦስት ዓመት ሕፃን ልጇን አዝላ ከሞት የተነሳችውን አገልጋይዋን አስከትላ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ሄዳ አስቀድማ ያዘጋጀችውን ልብሰ ምንኲስና ለብሳ ከሴቶች ገዳም ገባች፡፡ ይዛው የተሰደደችው ሕፃን ግን ወንድ ስለሆነ ከገዳሙ ውጭ አስቀምጣው ስለገባች ሕፃኑ አምርሮ ማልቀሱን የተመለከተች ከመነኰሳቱ አንዲቷ ሲያለቅስ ከሚያድር ብላ ወደ በዓቷ ልታስገባው ስትል ቅዱስ ሚካኤል ነጥቆ ወስዶ በገነት አስቀመጠው፤ ታኅሣሥ 29 ቀን ተወልዶ በሦስት ዓመቱ ታኅሣሥ 12 ቀን ብሔረ ሕያዋን አስገብቶታል፡፡
   ከዕለታት በአንደኛው ቀን ቅዱስ ሚካኤል ካለችበት በዓት አውጥቶ በክንፉ ወደ ጣና (ጓንጉት) ደሴት አደረሳት፤ በዚያም ሰውነቷ ተበሳስቶ ዓሣ ሰውነቷን መመላለሻ እስኪያደርጋት ድረስ ለ12 ዓመት በባሕሩ ውስጥ ቁማ ስትጸልይ ኖራለች፡፡ እግዚአብሔርም ከመከራዋ ብዛት ከገድሏ ጽናት የተነሣ 6 የጸጋ ክንፍ ሰጥቷታል፡፡ እግዚአብሔር ‹‹ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ምን እንዳደርግልሽ ትፈልጊያለሽ?›› ብሎ በጠየቃት ጊዜ ‹‹ደቂቀ አዳምን እንዳያስታቸው ዲያብሎስን ማርልኝ›› አለችው፡፡ ‹‹እርሱ ምሕረት አይሻም እንጂ ከወደደ ጥሪው›› ብሎ ቅዱስ ሚካኤልን ረዳት አድርጎ ወደ ሲዖል ላካት፡፡ በዚያም ዲያብሎስን በስሙ ጠርታ ‹‹ፈጣሪ ምሮሃልና ና ውጣ›› አለችው፡፡ ዲብሎስም ‹‹አስቀድሜ ስፈልግሽ እኖር ነበር አሁን አጠገቤ መጣሽልኝ›› ብሎ ጎትቶ ወደ ሲዖል ጣላት፡፡ ከዚያም ቅዱስ ሚካኤል የብርሃን ሰይፉን መዞ ሲዖልን ቢመታት ታላቅ ንውጽውጽታ ሆነ፤ ሲዖልም ብርሃን ለበሰች፡፡ ወዲያው ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ነጥቆ ሲያወጣት በተሰጣት የጸጋ ክንፍ እጅግ የበዙ ነፍሳትን ማርካ ወጥታለች፡፡ ከዚህ በኋላ በጾም በጸሎት ተወስና ስትኖር እግዚአብሔር ‹‹ቅዱስ ሚካኤልን ባልደረባ ሰጥቼሻለሁ፤ ክብረ በዓልሽም በየወሩ ከሚካኤል ጋር ይታሰባል›› ብሎ ቃል ገብቶላታል፡፡ ከዚህም የተነሣ በየዓመቱ ግንቦት 12 ቀን በደማቅ ክብረ በዓል ትታሰባለች፡፡ የዕረፍቷ መታሰቢያ ነሐሴ 24 ቀን ነው፡፡ በረከቷ ለሁላችን ይድረሰን አሜን!
         ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
ምንጭ፦ መድበለ ታሪክ ፣ መዝገበ ቅዱሳን

   •┈┈┈••●◉ ✞✟✞ ◉●••┈┈┈ •
   የእናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በዓለ
   ዕረፍት በደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምህረት
    ቅ/ማርያምና ቅ/ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል የሚከበር ይሆናል።
#አድራሻ ከመገናኛ አያት በሚወስደው መንገድ ጉርድ ሻላ /ሰአሊተ ምህረት አደባባይ ተሻግሮ/
   •┈┈┈••●◉ ✞✟✞ ◉●••┈┈┈ •
                @EwketBurhan
            
396 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, 11:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 14:32:32
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
        #ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ
   በኢትዮጵያ ቡልጋ አካባቢ ልዩ ስሙ ቅዱስ ጌዬ በሚባል ቦታ የተወለደችው ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ከአባቷ ደረሳኒ ከእናቷ ዕሌኒ ግንቦት 12 ቀን ተወለደች። ወላጆቿ የእግዚአብሔርን ሕግጋትና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን በማስተማር አሳደጓት፤ ለዐቅመ ሔዋን በደረሰች ጊዜም ለሠምረ ጊዮርጊስ ዳሯት፤ ካገባትም በኋላ ካህን ሆነ፤ 12 ልጆችንም (ዐሥር ወንዶችና ሁለት ሴቶች) ወለዱ። ቅድስት ክርስቶሰ ሠምራ እግዚአብሔርን የምትፈራ፣ በጾምና በጸሎት ተወስና የምትኖር ደግ ሴት መሆኗን የሰማው በዘመኑ የነበረው ንጉሥ ዓፄ ይስሐቅ (የንግሥና ስሙ ንጉሥ ዓፄ ገብረ መስቀል) እንዲያገለግሏት 174 አገልጋዮችን ‹‹በጸሎትሽ አስቢኝ›› ብሎ ላከላት፡፡ ከአገልጋዮቿ መካከል አንዷ ምግባሯ አስቸጋሪ በመሆኑ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን በጣም ታበሳጫት ነበር። ይህችው አገልጋይ ከዕለታት አንድ ቀን ስታስቸግራት ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የእሳት ትንታግ አንስታ በአገልጋይዋ አፍ አደረገችባትና ወዲው ሞተች፡፡ በዚህም ክርስቶስ ሠምራ ደነገጠችና ወደ ሰማይ አንጋጣ  ‹‹እኔ ክርስቲያንና የካህን ሚስት ስሆን ነፍሰ ገዳይ ሆንኩ፤ ወዮልኝ ነፍሴን ምን እላታለሁ? ልሸከማት የማልችል ኃጢአት አገኘችኝ›› እያለች ፈጣሪዋን ትማጸን ጀመር፤ ዳግመኛም ‹‹ይህችን ነፍስ ከሥጋዋ አዋሕደህ ብታስነሣልኝ ልጆቼን፣ ቤቴን፣ ንብረቴንና ሀብቴን ትቼ አንተን እከተላለው›› ብላ ስዕለት ተሳለች፡፡ ‹‹አቤቱ ጸሎቴን ስማኝ ጩኸቴም ወደ አንተ ይድረስ በመከራዬ ቀን ፊትህን ከእኔ አትመልስ›› (መዝ 101፥1-2) እንዲል ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ ክርስቶስ ሠምራም ይህንኑ መዝሙር ስትዘምር የሞተችዋን አገልጋይ አግዚአብሔር አስነሣላት።
605 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, edited  11:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 14:23:48 ለሰንበት ተማሪዎቻችን #የ12ተኛ ክፍል #ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ

     መልካም የጥናትና ዝግጅት ጊዜ እንዲሆንላችሁ ከወዲሁ እየተመኘን፤ ለጥናታችሁ ያግዛችኋል ብለን ያሰብናቸዉን ጽሑፎች ፣ ምስሎች እንዲሁም ፋይሎችን  https://t.me/EB12Exam ሊንክ በመግባት ማግኘት ትችላላችሁ።
ለምታውቋቸው ሼር አርጓቸው

የደ/ም/ሰ/ም/ቅ/ማርያም እና ቅ/ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል እውቀት ብርሃን ሰ/ ት/ቤት ሕፃናት ማዕከላዊያን ክፍል
@EwketBirhan
662 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, edited  11:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 09:16:02 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
#ቅዱስ_ቶማስ_ዘመርዓስ
ቅዱስ ቶማስ አስቀድሞ በጾም፣ በጸሎትና በስግደት የሚተጋ እንዲሁም ለድኆችና ለምስኪኖች የሚራራ ተጋዳይ ቅዱስ አባት ነበር፡፡ በኋላም መርዓስ ለሚባል አገር ኤጲስ ቆጶስ ይሆን ዘንድ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መረጠው፡፡ ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ በነገሠ ጊዜ ክርስቲያኖችን ያሰቃያቸው ዘንድ ከመኳንንቶቹ አንዱ ቶማስ በተሾመባት አገር (መርዓስ) ደረሰና ቶማስን ወደ እርሱ ያቀርቡት ዘንድ ጭፍሮቹን ልኮ እየደበደቡ በምድር ላይ እየጎተቱ አመጡለት፡፡ መኰንኑም ቅዱስ ቶማስን ለአማልክት/ለጣዖት ስገድ ቢለው ‹‹ከሕያው እግዚአብሔር ልጅ ከጌታዬ ከኢየሱስ ክርስቶስ በስተቀር ለረከሱ ጣዖታት አልሰግድም፤ ለረከሱ ጣዖታት የሚሰግድ ሁሉ የተረገመ ነውና›› ብሎ መለሰለት፡፡
በዚህም መኰንኑ ተቆጥቶ እጅግ የበዛ ስቃይን እያሰቃየው ለብዙ ጊዜ ኖረ፤ ምክንያቱም የከሃድያኑ ልባቸው እንደ ደንጊያ የጸና ስለሆነ ቅዱስ ቶማስ ቶሎ እንዲሞት አይፈልጉምና ነው፡፡ ቅዱስ ቶማስ ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ስለጸና ማሰቃየቱን ከሃድያኑ በተሸነፉ ጊዜ ስለ ስህተታቸው ስለሚዘልፋቸው በጨለማ ቦታ ጣሉት፤ በዚያም 22 ዓመት ኖረ፡፡ ከሃድያኑ በየዓመቱ ወደ እርሱ እየገቡ ከአካል ክፍሎቹ ውስጥ አንዱን (አፍንጫውን፣ ከንፈሮቹን፣ እጆቹንና እግሮቹን) ይቆርጡ ነበር፡፡ ከእርሱ ጋር የነበሩት ሰዎችም ያረፈ መስሏቸው በየዓመቱ መታሰቢያውን ያደርጉ ነበር፡፡ ነገር ግን አንዲት ክርስቲያናዊት ሴት በጣሉት ጊዜ ስላየች ቦታውን ታውቅ ነበርና በሌሊት ወደ እርሱ ተሠውራ በመሄድ ትመግበዋለች፡፡
ንጉሥ ቈስጠንጢኖስም እስከ ነገሠና የቀናች የክርስቶስን ሃይማኖት ክብር እስከ ገለጠበት ድረስ እንዲህ ሲሰቃይ ኖረ፡፡ ይህም ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ በወህኒ ቤት ያሉትን እስረኞች ይፈቷቸው ዘንድ በአዘዘ ጊዜ ያቺ ሲጥሉት የተመለከተችው ሴት ሄዳ ስለ ቅዱስ ቶማስ ለካህናቱ ነገረቻቸው፤ እነርሱም አንስተው ወደ ቤተ ክርስቲያን አደረሱት፡፡ በቤተ መቅደስም ፊት ለፊት በወንበሩ ላይ አስቀመጡትና ምእመናን ወደ እርሱ እየመጡ ከእርሱ ተባርከው የተቆረጡትንም ሕዋሳቱን ተሳልመው ይመለሱ ነበር፡፡ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ 318ቱን ሊቃውንት በኒቅያ በሰበሰበ ጊዜ ቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ አንዱ ነበር፡፡ በኒቅያ ጉባኤ አሪዎስን አውግዘው ከለዩት በኋላ መንፈስ ቅዱስ እንዳስተማራቸውና እንደመራቸው የሃይማኖትን ትምህርት በአንደበታቸው ተናገሩ፣ ሕግና ሥርዓትን፣ ሥጋዊና መንፈሳዊ ፍርድንም ሠሩ፡፡
ከዚህ በኋላ ቅዱስ ቶማስ ወደ መንበረ ሢመቱ በመሄድ ካህናቱንና ምእመናኑን ሁሉ ሰብስቦ በኒቅያ የተደነገገውን ውሳኔ አንብቦላቸው እንዲያስተውሉት፣ እንዲጠብቁትና በመጠበቅም እንዲጸኑ አዘዛቸው፡፡ ጥቂት ዘመናትም ከኖረ በኋላ ነሐሴ 24 ቀን በክብር ዐረፈ፡፡ በረከቱ ደርብን አሜን!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
ምንጭ፦ ስንክሳር ዘነሐሴ 24 ፣ መዝገበ ታሪክ

@EwketBirhan
493 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, edited  06:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 18:54:37 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
                #ነቢዩ_ሚክያስ
   ሚክያስ ማለት ማን እንደ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡ ትውልዱ ከነገደ ንፍታሌም ሲሆን ቍጥሩ ከ12ቱ ደቂቀ ነቢያት ነው፡፡ በዘመኑ እስራኤልን ያስተዳድር የነበረው ንጉሥ አክዓብ የይሁዳን ንጉሥ ኢዮሣፍጥን ‹‹ከእኔ ጋራ ወደ ሬማት ዘገለዓድ አትወጣምን?›› ብሎ ሲጠይቀው ‹‹ፈቃደ እግዚአብሔርን እንጠይቅ›› ብሎ መለሰለት፡፡ ከዚያም ‹‹ደግ ነገር አይናገርልኝም እንጂ የይምላ ልጅ ሚክያስ ነበር›› ብሎ ነቢዩ ሚክያስን አስጠራው፡፡ ነቢዩ ሚክያስም ‹‹እስራኤል ጠባቂ እንደሌለው መንጋ ሲቅበዘበዙ አይቻለሁና ሂድ ተከናወን›› አለው፤ በዚህን ጊዜ አክዓብ ‹‹ይኸውልሃ ክፉ እንጂ ደግ ነገር አይናገርልኝም አላልሁህምን›› ብሎ ለንጉሥ ኢዮሣፍጥ ነገረው፡፡ እነርሱም ‹‹አንተ ከነቢያት ሁሉ የተለየህ ነህን?›› አሉት፤ ሴዴቅያስና ሌሎች ነቢያት በሐሰት ‹‹ሬማት ዘገለዓድን አሳልፎ በእጅህ ይሰጣታልና ሂድ›› ይሉት ነበርና ነው፡፡ 
   ነቢዩ ሚክያስ ግን አክዓብ እንደሚሸነፍ እግዚአብሔር የገለጠለትን እውነት ተናገረ እንጂ አልዋሸም፤ የእውነት ትንቢት በመናገሩም ሴዴቅያስ በጥፊ መትቶታል፤ ከዚያም አክዓብ ‹‹በደህና እስክመለስ ድረስ በግዞት አኑሩት የመከራም እንጀራ መግቡት›› ብሎ ሚክያስን በግዞት እንዲያቆዩት አዝዞ ወደ ሬማት ዘገለዓድ ሄደ፡፡ ነቢዩ ሚክያስ እንደተናገረውም አክዓብ በዚያው በጦር ተወግቶ ሞተ እንጂ ድል አላደረገም፤ (2ዜና መዋዕል ምዕራፍ 18 ሙሉውን ያንብቡት)፡፡   
   ከዚህም ሌላ ነቢዩ ሚክያስ ነገረ ሥጋዌ ተገልጦለት የጌታን ከሰማያት መውረድ፣ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በቤተልሔም መወለድ ትንቢት ተናግሯል፤ (ሚክ 5፥2-3)፡፡ የትንቢት ወራቱን ፈጽሞ ነሐሴ 22 ቀን ዐርፏል፡፡ በረከቱ ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን!

          ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
ምንጭ፦ መጽሐፍ ቅዱስ ፣ ስንክሳር ዘነሐሴ 22
   t.me/EwketBirhan
559 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, 15:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 12:42:56 እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወርኃዊ በዓል አደረሳችሁ!
  ኆኅተ ሰማይ ቅድስት ማርያም ካቴድራል ድሬዳዋ
     
https://t.me/PhotoEwketBirhan/1860?single
532 views𓅪ሀገሬ ሰማይ ዘሬም ፍቅር𓅪, edited  09:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ