Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopia Check

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopiacheck — Ethiopia Check
ርዕሶች ከሰርጥ:
Medialiteracy
Explainer
Ethiopiacheck
የሰርጥ አድራሻ: @ethiopiacheck
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 26.08K
የሰርጥ መግለጫ

ኢትዮጵያ ቼክ በማህበራዊ ሚድያ እና በመደበኛ ሚድያዎች የሚቀርቡ ሀሰተኛ መረጃዎችን በማጣራት ስራዎቹን ለተከታታዮቹ ያቀርባል።

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 51

2022-08-31 16:43:21
3.4K views13:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 10:15:56
#EthiopiaCheck Notes

የፖለቲካ አለመረጋጋት ወይንም ግጭት ሲኖር በየሰዐቱ የሚፈጠሩ ክስተቶችን ለማወቅ ጉጉታችን ይጨምራል።

የማወቅ ጉጉታችንን ለማርካት መረጃ ልናገኝባቸው እንችላለን ያልናቸውን የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ወይንም ቻናሎች አልያም ሚዲያዎች ማሰሳችን ይጠበቃል። በአሰሳችን ወቅት ለክሊክ አጥማጆች (clickbaits) የመጋለጥ እድልም ይኖረናል።

የክሊክ አጥማጆች ለስሜታችን የቀረበ፣ ጉጉት የሚያጭር፣ “አትለፉኝ አትለፉኝ” የሚል የዜና ርዕስ (headline) እና በደንብ የተቀናበረ ፎቶ በመጠቀም ማስፈንጠሪያዎችን እንድንከተል ወይንም ቪዲዮዎችን እንድንከፍት የሚገፋፉ ገጾችና ቻናሎች ሲሆኑ ወደ ውስጥ ገብተን ይዘታቸውን ስንመለከት ከዜና ርዕሳቸው ጋር የማይገናኝ፣ ምንጭ የሌለው፣ ከዚህም ከዚያም የተቃረመ ሆኖ እናገኘዋለን።

ክሊክ አጥማጆች በኢትዮዮጵያ በተለይ በዩትዩብ በርከት ብለው የሚገኙ ሲሆን አብዛኞቹ አላማቸው ብዙ ሰብስክራይበርና ተመልካች በማግኘት ብር ማግኘት ሲሆን ሌሎቹ የፖለቲካ አላማቸውን ለማሳካት ይጠቀሙበታል።

ክሊክ አጥማጆች በአብዛኛው ይዘታቸው ምንጭ የማይጠቅስ፣ የተጋነነ፣ ርዕታዊነት የጎደለውና ወገንተኛ ሆኖ ይገገኛል። በዚህም ለሀሠተኛና የተዛቡ መረጃው ስርጭት ከፍተኛ ድርሻ ይወስዳሉ።

ስለሆነም በክሊክ አጥማጅ የዩቲዩብ ቻናሎች ወይንም ድረ-ገጾች የሚቀርቡ መረጃዎችን ከማመናችን እና ከማጋራታችን በፊት ቆም ብሎ ማሰብ እና የሚከተሉትን ጥያቄዎች መጠየቅ በሀሰተኛና የተዛባ መረጃ ከመጋለጥ ይታደጋል:

* የመረጃ አቅራቢው ሚዲያ ወይንም ግለሰብ ማንነት ይታወቃል?
* መረጃ አቅራቢው ለድርጊቱ ወይንም ድርጊቱ ለተፈጸመበት አካባቢ ምን ያህል ቅርብ ነው?
* መረጃ አቅራቢው ታማኝ ምንጭ ጠቅሷል?
* መረጃውን በአንጻራዊነት ታማኝ የሆኑ የሚዲያ ተቋማት ዘግበውታል?
* መረጃ አቅራቢው መረጃውን በፎቶ ወይንም በቪዲዮ አስደግፏል?
* ፎቶዎች እና ቪዲዮዎች ትክክለኛ እና እውነተኛ ናቸው?

@EthiopiaCheck
4.3K views07:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 10:15:37
4.0K views07:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 12:04:55
#EthiopiaCheck Media Monitoring

ደንበኞቹ ከአጭበርባሪዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሳሰበ።

ደንበኞች የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚያዘጋጃቸውን የሽልማት ፕሮግራሞች በመንተራስ የሌብነት ተግባር ከሚፈፅሙ አጭበርባሪዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ አሳሰቡ፡፡

ወደ ደንበኞች ስልክ ደውለው ሽልማት እንደደረሳቸው በመንገርና ገንዘብ እንዲያስገቡ በመጠየቅ ሌብነት የሚፈጽሙ አጭበርባሪዎች መበራከታቸውን አቶ አቤ ገልፀዋል፡፡

ባንኩ ወደ ደንበኞች ስልክ የሚደውልበት አጋጣሚ መኖሩን የተናገሩት አቶ አቤ፣ ነገር ግን ደንበኞቹ ወደ ባንኩ በአካል እንዲቀርቡ ወይም ሰነድ እንዲያቀርቡ እንጂ በስልክ ይህን አስገቡ ያን አስወጡ የሚለው ነገር እንደሌለ አስረድተዋል፡፡

ደንበኞች ከባንክ ነው በሚል ስልክ ሲደወልላቸው ከሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት ጋር በተያያዘ ምንም አይነት እርምጃ መውሰድ እንደሌለባቸው እና በስልክ መረጃ እንዳይሰጡ ያሳሰቡት አቶ አቤ፣ ይልቁንስ በአቅራቢያቸው ወደሚገኝ ቅርንጫፍ በመሄድ ወይም 951 ላይ በመደወል የመረጃውን ትክክለኛነት ማጣራት እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለሚሰጠው አገልግሎት ስልክ ደውሎ ምንም አይነት ክፍያ እንደማይጠይቅም ነው አቶ አቤ ያስገነዘቡት፡፡

በተጨማሪም ደንበኞች ሞባይላቸው ሲጠፋባቸው ወደ ባንኩ ቅርንጫፍ በመሄድ የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎታቸው እንዲቋረጥ ማስደረግ እንዳለባቸው አቶ አቤ አሳስበዋል፡፡

Via CBE
@EthiopiaCheck
5.2K views09:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 11:03:26
#EthiopiaCheck መልእኽቲ ሰኑይ

ብዛዕባ ሓሶትን ዝኾኑን ዝተዛብዑን መልእኽትታት፣ ዘረባ ጽልኢትን ናይ ሓሶት ኣካውንትታትን እንታይ ክንገብር ንኽእል?

ናይ ሓሶትን ዝተዛብዑን መልእኽትታት፣ ዘረባ ጽልኢትን ናይ ሓሶት ኣካውንትታት ከምኡውን ንኢንተርነት መሰረት ዝገበሩ ናይ ምትላል ተግባራት ዘብጽሑዎ ሰፊሕ ጕድኣት ንምንካይ ዓብዪ ኣበርክቶ ኽንገብር ንኽእል ኢና።

እቲ ቐዳማይ ነጥቢ ነዚኦም ዓይነት ትሕዝቶታት ካብ ምዝርጋሕን ምክፋልን ምቑጣብ፣ ከምኡውን ከምዚኦም ዝኣመሰሉ ትሕዝቶታት ካብ ዝዝርግሑ ኣካላት ምርሓቕ ኢዩ። ብተወሳኺውን ኣሉታዊ ትሕዝቶ ንዝዝርግሑ ሰባት ምቅላዕ፣ ሓበሬታ ንዘጻርዩ ኣካላት ምሕባር፣ ከምኡውን ናይ ባዕልናን ኣብ ከባቢና ናይ ዘለዉ ሰባትን ኣጠቓቕማ ሚዲያ ክጉልብት ምግባር ዓብዪ ለውጢ ከምጽእ ይኽእል እዩ።

ለውጢ ክመጽእ ዘኽእለና እቲ ኻሊእ ኣወንታዊ ተግባር ከዓ ኣብ ማሕበራዊ ሚዲያ ዘጋጥሙና ሓሶት ዝኾኑን ዝተዛብዑን መልእኽትታት፣ ዘረባ ጽልኢት፣ ናይ ሓሶት ኣካውንትታት ከምኡውን መሰረቶም ኣብ ኢንተርነት ንዝገበሩ ናይ ምትላል ተግባራት ንማሕበራዊ ሚዲያ ኣገልግሎት ወሃብቲ ትካላት ሪፖርት ምግባር እዩ ።

ከምቲ ዝፍለጥ ማሕበራዊ ሚዲያ ትካላት ንዘለዎም ፖሊሲ ዝጥሕስ ትሕዝቶ ዝቆጻጸሩን ዝከታተሉን ብሰብ ሓይሊን ብቴክኖሎጂን ዝሕገዝ ኣሰራርሓ ኣለዎም። ኮይኑ ግና ምስቲ ናይቶም ትሕዝቶታት ምብዛሕን ዘለዎም ባህርይ ተለዋዋጢ ምስ ምዃኑን ነቲ ተግባር እቶም ትካላት በይኖም ክቈጻጸርዎ ይኽእሉ እዮም ተባሂሉ ኣይሕሰብን። በብግዚኡ ዝወጽኡ ሪፖርት ናይቶም ትካላትውን ነዚ እዩ ዘርእየና። ነዚ ክፍተት ንምምላእ ቀሊል ግን ከዓ ልዑል ዝኾነ ኣበርክቶ ክነበርክት ንኽእል ኢና ።

ነዚውን ኣብ ማሕበራዊ ሚዲያታት ንዘለዉ ኣሉታዊ ትሕዝቶታትን ንዝዝርግሑ ኣካላትን ሪፖርት ብምግባር ኣብ ትኹረት ንኽኣትዉን ስጕምቲ ንኽውሰደሎምን ጸቕጢ ክንገብር ንኽእል ኢና።

እንታይ ዓይነት ትሕዝቶታት ሪፖርት ክንገብር ንኽእል?
- ኣንጻር ናይ ዝተወሰነ ኣካል መንነት ዝኾነ፣ ብብሄር፣ ብሄረሰብን ህዝብን፣ ብሃይማኖት፣ ብዓሌት፣ ብጾታ ወይ ከዓ ብጉድኣት ኣካል ተመስሪቱ ኣድልዎ ወይ ጥቕዓት ንዘለዓዕል ዘረባ ጽልኢት
- ልዕል ኢሉ ንዝተዘርዘረ መንነት መሰረት ጌሩ ኣብ ውልቀ-ሰብ ኣድልዎ ወይ ጥቕዓት ንዘለዓዕል ዘረባ ጽልኢት
- ስለተዘርግሑ ጕድኣት ከስዕቡ ዝኽእሉ ሓሶት ንዝኾኑን ንዝተዛብዑን መልእኽትታት
- ጽልዋ ናይዘለዎም ውልቀ ሰባትን ትካላትን ሽም ብምጥቃም ዝተኸፈቱ ናይ ሓሶት ኣካውንትታትን ገጻትን ከምኡውን
- ናይ ምትላል ተግባራት ንምፍጻም ብዝብል ንዝተዘርግሑ ትሕዝቶታት ሪፖርት ክንገብር ንኽእል ኢና ።

እዚኦም ዝተዘርዘሩ ትሕዝቶታት ብጽሑፍ፣ ብስእሊ፣ ብድምጺ፣ ብቪዲዮን ብስክሪን ቅዳሓትን ክቐርቡ ይኽእሉ እዮም። ነቶም ትሕዝቶታት ከዓ ኣብ ርእይቶ መውሃቢ ቦታታት (comment boxes)፣ ክፍቲ ወይ ዕጹው ብዝኾኑ ግሩፓት (public or closed groups)፣ ብቀጥታ ፈነወ፣ ብውሽጣዊ መልእኽትታትን (private messages) ካልኦት ተመሳሳሊ ቦታታት ክንርእዮም ንኽእል ኢና።

ነዚኦም ኣሉታዊ ትሕዝቶታት ሪፖርት ምግባር ቀሊልን ኣብ ሓጺር እዋን ክግበር ዝከኣልን እዩ። ቅድም ኢልና ሪፖርት ጌርና ዘይንፈልጥ እንተ ኾይኑ ወይ ከዓ እንተ ተደናጊርና ኢትዮጵያ ቼክ ንዘዳለዎም ሕጽር ዝበሉ ቪድዮታት ንርአ።

ናይ ፌስቡክ ትሕዝቶ ሪፖርት ንምግባር፡



ናይ ዩቱዩብ ትሕዝቶ ሪፖርት ንምግባር፡



ናይ ትዊተር ትሕዝቶ ሪፖርት ንምግባር፡



ናይ ቴሌግራም ትሕዝቶ ሪፖርት ንምግባር፡

4.6K views08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 11:03:15
4.4K views08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 18:41:57
#EthiopiaCheck የአርብ የሚድያ ዳሰሳ

1. የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ረዳት ፕሮፌሰር አሰፋ ወዳጆ የጥላቻ ንግግርን እና የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1185/2012ን በመተላለፍ መከሰሳቸውን አዲስ ስታንዳርድ ዘግቧል። በዘገባው መሰረት ረዳት ፕሮፌሰሩ የአዋጁን አንቀጽ 4፣ 5 እና 7(4) ን በመተላለፍ ነው ክስ የቀረበባቸው። ክሱን የመሰረተው የሶዶ ከተማ አቃቤ ህግ ተከሳሹ ከ5 ሺህ በላይ ተከታዮች ባሉት የፌስቡክ ገጹ ሀሠተኛ መረጃና የጥላቻ መልዕክት አሰራጭቷል ሲል ወንጅሏል። አዲስ ስታንዳር ያነጋገራቸው የተከሳሹ ባለቤት አዋጁ ከመጣቱ በፊት በረዳት ፕሮፌሰሩ የፌስቡክ ገጽ የተጋሩ መልዕክቶች በክሱ መካተታቸውን አመልክተዋል።

2. የሰራዊቱን እንቅስቃሴዎች የተመለከቱ የተዛቡ መረጃዎችን የሚያሰራጩ የማህበራዊ ሚዲያ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ሲል የመከላከያ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ማክሰኞ ዕለት ባወጣው መግለጫ አሳስቧል። መግለጫው “ይህንን ተግባር በግዴለሽነት ወይም በማንአለብኝነት የሚቀጥሉና የማይታረሙ ካሉ” መከላከያ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድና የወንጀል ክስ ለመመስረት እንደሚገደድም አስነብቧል።

3. የናይጄሪያ የመረጃ አጣሪዎች ጥምረት (Nigerian Fact-Checkers Coalition) በሀገሪቱ በመጭው የፈረንጆች አመት የሚደረገው ምርጫ ከሀሠተኛና የተዛቡ መረጃዎች የጸዳ ይሆን ዘንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች የበኩላቸውን እንዲወጡ ጠይቋል። ጥምረቱ በሳምንቱ አጋማሽ ባወጣው መግለጫ የምርጫ ቅስቀሳ የፊታችን መስከረም እንደሚጀመር አስታውሶ ሆኖም ከአሁኑ ምርጫን የተመለከቱ ሀሠተኛና የተዛቡ መረጃዎች ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ የመጨምር ዝንባሌ ማሳየቱ እንዳሳሰበው ገልጿል። የናይጄሪያ የመረጃ አጣሪዎች ጥምረት አፍሪካ ቼክን ጨምሮ ስምንት አባላት አካቷል።

4. አንድ የብራዚል ፍርድ ቤት የሀገሪቱ ፕሬዝደንት አሰራጭተውታል ያለውን የተዛባ መረጃ ከፕሬዝደንቱ የግል የማህበራዊ ሚዲያ አካውንቶችና ከመንግስት ገጾች እንዲሰረዝ የሚያዝ ብያኔ ማስተላለፉን ዘ-ብራዚሊያን ሪፖርት ድረ-ገጽ ዘግቧል። የብራዚል ልዩ የምርጫ ጉዳዮች ፍርድ ቤት ትዕዛዙን ያስተላለፈው ፕሬዝደንት ቦልሶናሮ “የሀገሪቱ የኤሌክትሮኒክ የምርጫ ስርዐት ሊስጠለፍ የሚችል ነው” በማለት የተሳሳተ መረጃ አሰራጭተዋል በማለት ነው። ብራዚል በመጭው ጥቅምት ወር ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ታደርጋለች።

በዚህ ሳምንት ያቀረብናቸው መረጃዎች እና የቴሌራም ሊንኮቻቸው:

- በሰኞ መልዕክታችን በሃቅና በአስተያየት መካከል ያለውን ልዩነት የሚያስቃኝ ጽሁፍ በአፋን ኦሮሞ አቅርበናል: https://t.me/ethiopiacheck/1488

- በተመሳሳይ ቀን “የዘንድሮው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ተሰርቆ ወጥቷል” ከሚል ፅሁፍ ጋር በስፋት የተጋራ ምስል የተቀናበረ መሆኑን የሚያስነብብ መረጃ አጋርተናል:
https://t.me/ethiopiacheck/1490

- ማክሰኞ ዕለት በተደጋጋሚ በአፋን ኦሮሞ ሀሠተኛ መረጃ የሚያሰራጭን የዩትዩብ ቻናል የሚያጋልጥ መረጃ አስነብበናል:
https://t.me/ethiopiacheck/1492

- በትናንትናው ዕለት ደግሞ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም የፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላን ስምና ምስል በመጠቀም ስለተከፈተ ሀሠተኛ ገጽ መረጃ አቅርበናል: https://t.me/ethiopiacheck/1494

- እንዲሁም “የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከል ማን ምን ሚና ሊጫወት ይገባል?’ በሚል ርዕስ በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞና በትግርኛ የተዘጋጁ ቪዲዮዎችን አጋርተናል:
https://t.me/ethiopiacheck/1493

https://t.me/ethiopiacheck/1496

https://t.me/ethiopiacheck/1495

@EthiopiaCheck
5.9K views15:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 18:41:44
4.2K views15:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 18:16:12
#EthiopiaCheck Explainer

በኦጋዴን ቤዚን እንደሚገኝ በጥናት የተረጋገጠዉ የተፈጥሮ ነዳጅ ክምችት ምን ያክል ነዉ?

የማዕድን ሚኒስቴር በዛሬው እለት ኔዘርላንድ፤ ሲዌል ኤንድ አሶሺየተስ ኢንክ (NSAI) ከተሰኘ የአሜሪካ ካምፓኒ በኦጋዴን ቤዚን የሚገኘዉን የተፈጥሮ ጋዝ መጠንና የኢኮኖሚ አዋጭነት የማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተረክቧል።

ይህ ሰርተፊኬት በዓለም አቀፍ ደረጃ የቴክኖሎጂ፣ የፋይናንስ እና ነዳጅ ኢንቨስትመንት አቅም ያላቸው ኩባንያዎች መጋበዝ የሚያስችል እና የመንግስትን የመደራደር አቅም የሚያጎለብት እንደሆነ የማዕድን ሚኒስትሩን ኢንጂነር ታከለ ኡማ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸዉ አስፍረዋል።

ይሁን እንጂ በኦጋዴን ቤዚን ይገኛል ስለተባለዉ የተፈጥሮ ጋዝ መጠን ግልጽ ያልሆኑ መረጃዎች በማህበራዊ ትስስር ገጾች ሲጋሩ ተመልክተናል።

ይህም አንዳንድ ሚዲያዎችና ማህበራዊ ትስስር ገጾች “ ሰባት ትሪሊየን ጫማ ጥልቀት ያለው የተፈጥሮ ነዳጅ ክምችት መኖሩ ተረጋገጠ” ሲሉ አንዳንዶች ደግሞ “ሰባት ትሪሊየን ኪዩቢክ ጫማ የተፈጥሮ ነዳጅ ክምችት መኖሩ ተረጋገጠ” ሲሉ ዘግበዋል።

ስለዚህም ሰባት ትሪሊዮን የምድር ዉስጥ ትልቀት ወይስ ብዛት (volume) የሚለዉን አወዛጋቢ አድርጎታል።

ጉዳዩን በተመለከተ ኢትዮጵያ ቼክ የማዕድን ሚኒስትሩን ኢንጂነር ታከለ ኡማ መረጃ የጠየቀ ሲሆን ትክክለኛ መረጃዉ ሰባት ትሪሊየን ኪዩቢክ ጫማ የሚለዉ እንደሆነ አረጋግጠዋል።

ስለዚህ ጥናቱ በኦጋዴን ቤዚን በሶስት ጉርጓዶች ዉስጥ ሰባት ትሪሊየን ኪዩቢክ ጫማ የተፈጥሮ ጋዝ እንዳለ ያረጋገጠ ነው ማለት ነዉ።

ይህ አራት ወራትን የፈጀዉ ሲዌል ኤንድ አሶሺየተስ ኢንክ (NSAI) ጥናት ከዚህ በፊት ሲነሳ ለቆየዉ “ምን ያክል የተፈጥሮ ጋዝ አለን” ለሚለዉ ጥያቄ ምላሽ የሰጠ እንደሆነ ተነግሯል።
4.8K views15:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 09:57:34
#EthiopiaCheck Video Explainer

Facaatii odeeffannoo sobaa ittisuuf eenyu gahee akkamii bahachuu qaba?

Viidiyoo gabaabaa Itoophiyaa Cheek qopheesse kana yaa daawwannu.

@EthiopiaCheck
5.3K views06:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ