Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopia Check

የሰርጥ አድራሻ: @ethiopiacheck
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 26.05K
የሰርጥ መግለጫ

ኢትዮጵያ ቼክ በማህበራዊ ሚድያ እና በመደበኛ ሚድያዎች የሚቀርቡ ሀሰተኛ መረጃዎችን በማጣራት ስራዎቹን ለተከታታዮቹ ያቀርባል።

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 48

2022-09-20 08:30:25
#EthiopiaCheck Explainer

Waa’ee labsii haasaa jibbiinsaafi odeeffannoo sobaa ittisuufi to’achuuf bahe dhimmoota kunneen beektuu?

Labsiin haasaa jibbiinsaafi odeeffannoo sobaa ittisuufi to’achuuf bahe namnootni wayita mirga yaada isaanii bilisa ta’anii ibsachuu fayyadamanitti haasaa walitti bu’iinsa yookin hookkara kakaasu taasisuurraa akka of qusatan gochuuf yaadamee kan ragga’e dha.

Namootni sabummaa, amantaa, sanyii, koorniyaa yookin miidhama qaamaa bu’ura godhachuun haasaawwan nama dhuunfaa yookin garee irratti jibbiinsa yookin loogii babal’isan gochuurra akka of qusatan taasisuunis kaayyoo labsii kanaati.

Labsichi maal hima?

Namni kamiyyuu haasaa jibbiinsaa yookiin odeeffannoo sobaa gama birodkaastii, maxxansa, miidiyaalee hawaasummaafi maloota walfakkaatoo birootiin barreeffamaan, suuraan, sagaleen yookin viidiyoodhaan tamsaasuun dhorkaa akka ta’e labsichi hima.

Labsiin kun jecha ‘tamsaasuu’ jedhu “haasaa bifa kamiinuu namoota baay’ee bira akka gahu gochuu yemmuu ta’u maxxansaalee miidiyaa hawaasaa ‘jaalachuu’ fi ‘tag’ gochuu (like and tag) ofkeessatti hin qabatu” jechuun hiika.

Adabbiinsaa hagami?

Yakki haasaa jibbiinsaa yookin odeeffannoo sobaa tamsaasuu fuula miidiyaa hawaasaa hordoftoota 5,000 ol qabuun yookiin tajaajila birodkaastiin yookiin maxxansa yeroo yeroon bahuun raawwatame yoo ta’e hidhaa hanga waggaa sadii fi adabbii maallaqaa birrii 100,000 hin caalle adabsiisa.

Kana malees labsichi gosa badii raawwatamefi miidhaa qaqqabe irratti hundaa’uun adabiiwwan garaagaraas kaa’ee jira.

Gama biraatiin wayita labsiin haasaa jibbiinsaafi oduu sobaa ittisuufi to’achuuf bahe ragga’utti namootni baay’een komiisaanii dhageesisaa turan.

Yaaddoowwan ‘labsiin kun mirga yaada ofii bilisaan ibsachuu ni daangessa’ jedhanis dhagahamaa turan.

Dabalataan akkaataan labsichi maalummaa haasaa jibbiinsaafi oduu sobaa itti ibse iftoomina guutuu kan hin qabnedha kan jedhus dhimma komii biraa ture.

@EthiopiaCheck
4.9K views05:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-20 08:30:11
4.0K views05:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-19 16:57:50
#EthiopiaCheck Fake Account Alert

የዶክተር ዳኛቸው አሰፋን ስምና ምስል በመጠቀም የተከፈቱ የትዊተር አካውንቶች።

የዶክተር ዳኛቸው አሰፋን ስምና ምስል በመጠቀም የተከፈቱ የትዊተር አካውንቶች መኖራቸውን ተመልክተናል። ከአካውንቶች መካከል አንደኛው እ.አ.አ ሚያዚያ 2014 ዓ.ም የተከፈተ ሲሆን 5,338 ተከታዮች አሉት።

ሌላኛው ከሳምንታት በፊት የተከፈተ ሲሆን ከ1,900 በላይ ተከታዮችን ማፍራት ችሏል። ይህ ‘Dr. Dagnachew Assefa of AAU’ የሚል ስያሜን የሚጠቀመው የትዊተር አካውንት በሚያጋራቸው መልዕክቶች በመቶዎች የሚቆጠሩ ግብረመልሶችን እንደሚያገኝም አስተውለናል።

ኢትዮጵያ ቼክ አካውንቶቹን በተመለከተ ዶክተር ዳኛቸውን አነጋግሯል። ዶክተር ዳኛቸው ትዊተር ተጠቅመው እንደማያውቁ ገልጸው ከላይ የተገለጹት አካውንቶችም ሆነ በአካውንቶቹ የሚጋሩት መልዕክቶች የእርሳቸው አለመሆናቸውን አሳውቀዋል።

ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ የፍልስፍና መምህር ሲሆኑ በጋዜጣ፣ በሬዲዮ፣ በቴሌቪዝን እንዲሁም በአደባባይ ሀሳባቸውን በመግለጽ ይበልጥ ይታወቃሉ።

ተመሳስለው የተከፈቱ ሀሰተኛ ገጾችን እና አካውንቶችን ባለመከተል ከሀሰተኛና ከተዛቡ መረጃዎችን ስርጭት እራሳችንን እንጠብቅ።

@EthiopiaCheck
4.8K views13:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-19 10:20:39
#MondayMessage መልእኽቲ ሰኑይ

ፈነወ ዘረባ ጽልኢትን ሓበሬታ ሓሶትን ንምክልኻልን ንምቍጽጻርን ዝወጽአ ኣዋጅ፡

ዕላማ ናይዚ ኣዋጅ ሰባት ሓሳባቶም ብናጽነት ናይ ምግላጽ መሰሎም ኽጥቀሙ ከለዉ ጎንጺ ወይ ዕግርግር ወይ ከዓ ንብሄር፣ ንሃይማኖት፣ ንዘርኢ፣ ንጾታ ወይ ከዓ ንጉድኣት ኣካል መሰረት ገይሩ ኣብ ልዕሊ ሓደ ሰብ ወይ ከዓ ጉጅለ ጽልኢ ወይ ኣድልዎ ካብ ዘስፋሕፋሕ ዘረባ ንኽቑጠቡ ተሓሲቡ ዝወጽአ ኣዋጅ እዩ።

ዝኾነ ይኹን ሰብ ናይ ጽልኢት ዘረባ ወይ ሓበሬታ ሓሶት ብብሮድካስት፡ ብሕታም ወይ ከዓ ብማሕበራዊ ሚዲያታት ወይ ብኻሊእ ተመሳሳሊ ሜላታት ኣቢሉ ናይ ጽሑፍ፣ ስእሊ፣ ድምጺ ወይ ከዓ ናይ ቪድዮ ፈነወ ከም ዝተኸልከለ ይገልጽ። ኣብዚ ዘሎ “ፈነወ” ዝብል ቃል ክትርጎም ከሎ ከዓ ‘ንዘረባ ብዝኾነ ይኹን ዓይነት መገዲ ንብዙሕ ሰባት ንኽበጽሕ ምግባር ማለት እንትኸውን ብማሕበራዊ ሚዲያ ላይክ ምግባርን ታግ ምግባርን ኣይሓውስን እዩ’ ይብል።

እቲ መቕጻዕቲ’ኸ እንታይ ይመስል ?
እቲ ዝተፈጸመ ገበን ምዝርጋሕ ዘረባ ጽልኢት ወይ ሓበሬታ ሓሶት ልዕሊ 5,000 ሽሕ ተኸተልቲ ኣብ ዘለዉዎ ናይ ማሕበራዊ ሚዲያ ገጺ እንተኾይኑ ወይ ብኣገልግሎት ብሮድካስት ወይ ከዓ በብጊዚኡ ብዝወጽእ ሕታም እንተኾይኑ እቲ መቕጻዕቲ ክሳብ ሰለስተ ዓመት ብዝበጽሕ ቀሊል መእሰርቲን ካብ ብር 100,000 ሽሕ ዘይበልጽ ቅጽዓትን ካልኦት ተመሳሳሊ መቕጻዕቲታትን ዝሓዘ እዩ።

እዚ ኣዋጅ ኣብ ዝጸደቐሉ እዋን ሰባት ጥርዓኖም ኣስሚዖም ነይሮም። ናይዚ ኣዋጅ ምውጻእ ሓሳብ ብናጽነት ናይምግላጽ መሰል ይዓግት’ዩ ዝብሉ ስግኣታት ተራኢዮም ኢዮም። ብዙሓት’ውን እዚ ኣዋጅ ንዘረባ ጽልኢትን ሓበሬታ ሓሶትን ዝገለጸሉ መገዲ ንጹርነት ዝጎደሎ እዩ ይብሉ።

@EthiopiaCheck
4.8K views07:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-17 21:59:30
#EthiopiaCheck Fact Check

በ4ኛ ክፍል የሂሳብ መፅሃፍ ላይ አለ ተብሎ የተሰራጨው መረጃ በትክክልም ቀደም ብሎ በትምህርት ቢሮ በኩል ለትምህርት ቤቶች የተሰራጨው ሶፍት ኮፒ ላይ ይገኛል።

ባለፉት ጥቂት ቀናት በ4ኛ ክፍል የሂሳብ መፅሃፍ ላይ "የግዕዝ ቁጥሮች ምልክቶች በቀጥታ ከግሪክ ፊደል ቁጥሮች የተወሰዱ ናቸው" የሚል መረጃ እንዳለ የሚገልፁ መረጃዎች በስፋት ማህበራዊ ሚድያ ላይ ሲሰራጩ ነበር። ይህን መረጃም በርካታ ተከታይ ያላቸውን ገፆች ጨምሮ በርካታ ግለሰቦች ሲያጋሩት ነበር።

ይህን ተከትሎ ዛሬ ማምሻውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ "በአንዳንድ አካላት በ4ኛ ክፍል የሂሳብ መፅሐፍ ላይ አለ ተብሎ እየተሰራጨ ያለው ፅሁፍ በመሐሃፉ ላይ የማይገኝና የተሳሳተ ነዉ" የሚል መረጃ በፌስቡክ ገፁ አጋርቷል።

ትምህርት ቢሮው አክሎም "ዛሬ ይፋ በተደረገውና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት የ4ኛ ክፍል የሂሳብ መጻሕፍት ገፅ 18 ላይ የግእዝ ቁጥርን አስመልክቶ ወጥቷል ተብሎ የተገለፀው ሃሳብ በመፅሐፍ ውስጥ የማይገኝ ሆነ ተብሎ የሃሰት መረጃ በማሰራጨት ውዥንብር ሊፈጥሩ በሚፈልጉ አካላት የተፈበረከ ነዉ" ያለ ሲሆን ይህም በመንግስት ሚድያዎች እና በበርካታ ሚድያዎች ተዘግቧል።

በዚህ ዙርያ ኢትዮጵያ ቼክ ማጣራት አርጓል።

ኢትዮጵያ ቼክ በመጀመርያ ያናገራቸው በኮልፌ ቀራንዮ በሚገኝ አንድ ትምህርት ቤት የሚያስተምሩ መምህር "የግዕዝ ቁጥሮች ምልክቶች በቀጥታ ከግሪክ ፊደል ቁጥሮች የተወሰዱ ናቸው የሚለው መረጃ የአመቱ መጀመርያ ላይ ከትምህርት ቢሮ በደረሰን የሶፍት ኮፒ PDF ላይ ይገኛል። የመፅሀፍ ህትመት በወቅቱ ስላልተጠናቀቀ እሱን ተጠቀሙ ተብሎ ነበር የተሰጠን" ብለዋል። መምህሩ ለማስረጃ እንዲሆን ይህንን ፋይል ለኢትዮጵያ ቼክ አሳይተዋል፣ እኛም መረጃው እንዳለ አረጋግጠናል።

ኢትዮጵያ ቼክ በመቀጠል ያናገራቸው ወላጅም ይህ ከላይ ስለ ግዕዝ የተጠቀሰው መረጃ በ PDF እንደደረሳቸው አረጋግጠዋል። "ስለዚህ ዛሬ ምሽት ለትምህርት ቢሮው እንደተባለው የሀሰት ነው ሳይሆን ስህተቱን አስተካክለናል መሆን ነበረበት" ብለው አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። እርሳቸውም ይህንን ልጃቸው ሲማርበት የነበረውን እና ከትምህርት ቤቱ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ያገኙትን የ PDF ፋይል ለኢትዮጵያ ቼክ አሳይተዋል።

ስለዚህ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ማምሻውን "የግዕዝ ቁጥሮች ምልክቶች በቀጥታ ከግሪክ ፊደል ቁጥሮች የተወሰዱ ናቸው በሚል የተሰራጨው መረጃ የሀሰት ነው" ብሎ ያወጣው መግለጫ በራሱ የተሳሳተ ነው፣ ምክንያቱም አዲስ የታተመው እና ዛሬ ርክክብ የተደረገበት መፅሀፍ ላይ ማስተካከያ ቢደረግም ቀድሞ ለትምህርት ቤቶች የተሰራጨው ሶፍት ኮፒ ላይ መረጃው ሰፍሮ ይገኛል።

በዚህ ዙርያ ማብራርያ ለመጠየቅ ኢትዮጵያ ቼክ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮን የኮሚኒኬሽን ክፍል ለማናገር ቢሞክርም አልተሳካም።

@EthiopiaCheck
6.2K viewsedited  18:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-17 21:59:20
4.9K views18:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-16 18:54:29
#EthiopiaCheck የአርብ የሚድያ ዳሰሳ

1. ግዙፎቹ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ሜታ፣ አልፋቤት፣ ማይክሮሶፍት እና አማዞን በኢንተርኔት አማካኝነት የሚሰራጩ የጥላቻ ንግግሮችን ለመቀነስ ይረዳሉ የተባሉ እርምጃዎችን ለመውሰድ ማቀዳቸውን በትናትናው ዕለት በዋይት ሀውስ በተደረገ ጉባዔ ላይ ይፋ አድርገዋል። ኩባንያዎቹ የጥላቻ ንግግር እያስከተለ ያለውን ዘርፈ ብዙ ጉዳት ከግምት ውስጥ በማስገባት አዳዲስ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ለማድረግ፣ በተለይ በታዳጊዎችና በወጣቶች ላይ ያተኮሩ የሚዲያ አጠቃቀም ንቃትን ላይ ለመስራት፣ ምርምሮችን ለመደገፍ እና ሌሎችንም እርምጃዎች ለመውሰድ ማሰባቸውን ገልጸዋል። በጸረ-ጥላቻ ላይ ባተኮረው የትናንቱ ጉባዔ የዩናይትድ ስቴት ፕሬዝደንት ጆ ባይደን እንዲሁም የጥላቻ ንግግር ሰላባ የሆኑ ግለሰቦችና ቤተሰቦች የተገኙበት ነበር።

2. በቲክቶክ ከሚታዩ አምስት የፍለጋ ውጤቶች (search results) አንዱ ሀሠተኛ፣ የተዛባ ወይም አሳሳች ይዘት መሆኑን ያደረኩት ጥናት አሳይቷል ሲል ኒውስጋርድ (NewsGuard) የተባለ ተቋም ይፋ አድርጓል። ተቋሙ ኮቪድ-19ን፣ የአየር ንብረት ለውጥን፣ ምርጫን እንዲሁም የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት የተመለከቱ ይዘቶችን ለጥናቱ መጠቀሙን ገልጿል። በተጨማሪም የቲክቶክ የፍለጋ ውጤቶች ከጎጎል የፍለጋ ውጤቶች አንጻር ከፍ ያለ የሀሠተኛ፣ የተዛባ ወይም የተሳሳተ ይዘት እንዳሳዩ ተመልክቻለሁ ብሏል።

3. የትዊተር ባለድርሻዎች ኩባንያው ለባለጸጋው ኢሉን መስክ በ44 ቢሊዮን ዶላር እንዲሸጥ የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ በአብላጫ ድምጽ ማጽደቃቸውን ቢቢሲ ዘግቧል። ውሳኔው ከግዥው ለመውጣት አፈግፍጓል የተባለውን ኢሉን መስክ ግዥውን እንዲፈጽም ለማስገደድ ያለመ መሆኑ በዘገባው ተካቷል። በዚህም ኩባንያውና ኢሉን መስክ የፍርድ ቤት ሙግታቸውን የሚቀጥሉ ይሆናል። ሁለቱ ወገኖች በፕላትፎርሙ የቦቶች ምጣኔ ባለመስማማታቸው ምክንያት ወደ ፍርቤት ማቅናታቸው ይታወቃል።

4. የአየር ንብረት በጥላቻ ንግግር ስርጭት ላይ የራሱ የሆነ ተጽኖ እንዳለው መቀመጫውን ጀርመን ያደረገው የፖስትዳም የአየር ንብረት ጥናት ተቋም (Potsdam Institute for Climate Impact Research) ከቀናት በፊት ይፋ ያደረገው ጥናት አሳይቷል። ጥናቱ በትዊተር በሚሰራጩ የጥላቻ ንግግሮች ላይ ያተኮረ ሲሆን ሞቃታማ በነበሩ ቀናቶች (ከ42 ዲግሪ ሴንትግሬድ በላይ) በፕላትፎርሙ የተሰራጩ የጥላቻ ንግግሮች በ22% ከፍ ማለታቸውን አስነብቧል። እንዲሁም ቀዝቃዛ በነበሩ ጊዜያት የስርጭት መጠኑ በ12% ጭማሪ ማሳየቱን የጥናት ውጤቱ አሳይቷል። ተቋሙ እ.አ.አ ከግንቦት 1/2014 እስከ ግንቦት 1/2020 ዓ.ም አድራሻቸው የተለየ (geolocated) 4 ቢሊዮን ትዊቶችን በናሙናነት መጠቀሙ ተገልጿል።

በዚህ ሳምንት ያቀረብናቸው መረጃዎች እና የቴሌራም ሊንኮቻቸው:

- በሰኞ መልዕክታችን ሀሠተኛና የተዛቡ መልዕክቶችን በተመለከተ በአዲሱ አመት ማድረግ ያለብንን ጥንቃቄ የተመለከተ ጽሁፍ በአፋን ኦሮሞ አስነብበናል:
https://t.me/ethiopiacheck/1534

- እንዲሁም በኦሮሞ ነጻነት ግንባር ስም ወጣ የተባለን ሠተኛ መግለጫ አጋልጠናል:
https://t.me/ethiopiacheck/1535
https://t.me/ethiopiacheck/1537

- በተመሳሳይ ቀን በኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የጥቆማ መቀበያ ስልክን የተመለከተ ማብራሪያ ወደናንተ አድርሷል:
https://t.me/ethiopiacheck/1539

- ማክሰኞ ዕለት ከረጅም ቪድዮዎች ላይ ተቆርጠው የሚጋሩ አጠር ያሉ ቪዲዮዎች ሊያሳስቱን ስለሚችሉ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለብን የሚያስታውስ ጽሁፍ በትግርኛ አስነብበናል:
https://t.me/ethiopiacheck/1540

- ሀሙስ የሂጅራ ባንክን ስም እና ምስል በመጠቀም የተከፈቱ ሀሰተኛ የቴሌግራም ቻናሎች የተመለከተ ጽሁፍ አጋርተናል:
https://t.me/ethiopiacheck/1541

- እንዲሁም የጋዜጠኛ መዓዛ ብሩን ስምና ምስል በመጠቀም የተከፈተ የትዊተር አካውንት መኖሩን አሳውቀናል:
https://t.me/ethiopiacheck/1542

- በተጨማሪም በአዲስ አበባ መምህራን ማህበር ስም እና ማህተም ተቀናብሮ እየተሰራጨ ያለ ሀሰተኛ ደብዳቤን የሚጋልጥ መረጃ አጋርተናል:
https://t.me/ethiopiacheck/1544

@Ethiopiacheck
5.6K views15:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-16 18:54:18
4.6K views15:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-15 21:07:00
#EthiopiaCheck Fact Check

በአዲስ አበባ መምህራን ማህበር ስም እና ማህተም ተቀናብሮ እየተሰራጨ ያለ ሀሰተኛ ደብዳቤ።

“የመምህራን የር/መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች የጋራ መኖሪያ ይመለከታል” በሚል ርዕስ በአዲስ አበባ መምህራን ማህበር እንደተጻፈ የሚገልጽ ደብዳቤ በማህበራዊ ሚዲያ ሲዘዋወር ተመልክተናል።

ይህ በ12/11/2014 ዓ.ም የተጻፈ ደብዳቤ የመኖሪያ ቤቶቹን አደረጃጀት፣ ብዛት፣ ስፋትና ዋጋ በሰንጠረዥ መልክ የሚያስነብብ ሲሆን በማህበሩ ፕሬዝደንት ፊርማ መውጣቱን ያሳያል።

ኢትዮጵያ ቼክ አንዳንድ የማህበሩ አባላት የደብዳቤውን ትክክለኛነት ሲጠይቁ የታዘበ ሲሆን በደብዳቤው ቅርጽና አቀራረብ በርከት ያሉ ግድፈቶች መኖራቸውን ታዝቧል።

ኢትዮጵያ ቼክ ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥም የደብዳቤውን ቅርጽና አቀራረብ ቀደም ካሉ የማህበሩ ደብዳቤዎች ጋር አነጻጽሯል። በተጨማሪም የአዲስ አበባ መምህራን ማህበር ፕሬዝደንትን አነጋግሯል።

በንጽጽሩም በደብዳቤው ራስጌ በእንግሊዘኛ የተጻፈው የማህበሩ ስም ግድፈት እንዳለበት ማየት ችለናል። ቀደም ባሉት የማህበሩ ደብዳቤዎች ላይ የማህበሩን ስም በትክክል የሚገልጽ ‘Addis Ababa City Administration Teachers’ Association’ የሚል የእንግሊዘኛ ጽሁፍ የሚነበብ ሲሆን በዚህኛው ደብዳቤ ግን ‘Addis Ababa City Administration Association’ በሚል ተጽፏል። በተጨማሪም በማህበሩ ደብዳቤዎች ከላይ በስተግራ ይቀመጥ የነበረው የማህበሩ አርማ በዚህኛው ደብዳቤ አይገኝም።

ኢትዮጵያ ቼክ ያነጋገራቸው የማህበሩ ፕሬዝደንት አቶ ድንቃለም ቶሎሳ ይህ በእርሳቸው ስም እንደወጣ የሚገልጸው ደብዳቤ ትክክለኛ አለመሆኑን የገለጹ ሲሆን ይህንንም በቀን 28/12/2014 ዓ.ም በጻፉት ምላሽ ለሁሉም የከተማ አስተዳደሩ መምህራን ማህበር ማስታወቃቸውን ተናግረዋል። ምላሽ የሰጡበትንም ሰነድ ለኢትዮጵያ ቼክ አሳይተዋል።

ፕሬዝዳንቱ ማህበራቸው የመኖሪያ ቤቶችን ጉዳይ እየተከታተለ መሆኑን አስረድተው ሆኖም በደብዳቤው ላይ የቀረበውን ዋጋ ማህበራቸው እንደማያወቀውም ጨምረው ገልጸዋል።

@EthiopiaCheck
5.6K views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-11 06:23:19
ሰላም የኢትዮጵያ ቼክ ተከታታዮች፣

እንኳን አደረሳችሁ! መልካም አዲስ ዓመት!

@EthiopiaCheck
2.6K views03:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ