Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO-MEREJA®

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja — ETHIO-MEREJA®
ርዕሶች ከሰርጥ:
Ethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 130.68K
የሰርጥ መግለጫ

Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot ✔

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 266

2022-06-14 15:30:26
ፍርድ ቤቱ በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ በ15 ቀን ውስጥ ክስ እንዲመሰረት ትዕዛዝ ሰጠ

በሰለሞን ሹምዬ እና መዓዛ መሐመድ ላይ ለሚያደርገው ምርመራም ተጨማሪ 5 ቀናት ፈቅዷል

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት፤ በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ ዐቃቤ ህግ በ15 ቀናት ውስጥ ክስ እንዲመሰረት ትዕዛዝ ሰጠ።

ፍርድ ቤቱ ፖሊስ በሰለሞን ሹምዬ እና መዓዛ መሐመድ ላይ ለሚያደርገው ምርመራ ተጨማሪ አምስት ቀናትም ፈቅዷል።

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን ጉዳይ የያዘው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምርመራውን አጠናቅቆ ለዐቃቤ ህግ ማስተላለፉን ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 7 ቀን 2014 ለፍርድ ቤቱ በጽሁፍ አስታውቋል። ከፖሊስ የምርመራ መዝገቡን መረከቡን በጽሁፍ ያረጋገጠው ዐቃቤ ህግ የክስ መመስረቻ 15 ቀናት እንዲሰጡት ችሎቱን ጠይቋል።

ጋዜጠኛ ተመስገንን ወክለው በችሎት የተገኙት ጠበቃው ሔኖክ አክሊሉ የዐቃቤ ህግን ጥያቄ ተቃውመው፤ ፍርድ ቤቱ የደንበኛቸውን የዋስትና መብት እንዲያስከብርላቸው ጠይቀዋል። የግራ ቀኙን ክርክር ያደመጠው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት የጠበቃውን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ በማድረግ ለዐቃቤ ህግ የክስ መመስረቻ 15 ቀናትን መፍቀዱን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።

ፍርድ ቤቱ የጋዜጠኛ ተመስገንን ጉዳይ ዛሬ የተመለከተው፤ ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ የፈቀደው የ10 ሺህ ብር ዋስትና በከፍተኛ ፍርድ ቤት ተሽሮ መዝገቡ አንዲመለስ በመደረጉ ምክንያት ሲሆን፤ የዋስትና ትዕዛዙን የሻረው፤ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በትዕዛዙ ላይ ያቀረበውን ይግባኝ በመቀበል ነው።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
13.6K viewsedited  12:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 14:45:18 "ሕዝብ ሳያውቀው የሚደረግ ድርድር የለም።" :- ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ

እያንዳንዷ የሰላም ቀን ለእኛ ትርፍ ታስገኝልናለች። ሕዝብ ሳያውቀው የሚደረግ ድርድር የለም። በይፋ የታወቀ አጥኚ ኮሚቴ ተቋቁሞ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካኝነት እየተመራ ሲሆን፣ እስካሁን ውጤቱን አላሳወቀም። የሚደራደረው ኮሚቴም ይሄ ነው። ውጊያ ሲመጣ ለሕዝብ አሳውቀን የጀመርን ሰዎች፣ ድርድር ከተጀመረ የሚያስደብቀን የለም። ነገር ግን፣ የብቻ ጠላት የለም የሀገር ጠላት እንጂ፣ ለብቻም የሚሰራ ሥራ የለም በጋራ እንጂ። የእኛም የሕዝባችንም ፍላጎት ለጥይት የሚወጣ ውጪ ለልማት እንዲወጣ ነው። ሰላም እንፈልጋለን ማለታችን የተደበቀ ድርድር እናደርጋለን ማለት አይደለም።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለቀርቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት መልስ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች ከታች ቀርበዋል።

"instant view" የሚለውን በመጫን መመልከት ይችላሉ።

https://telegra.ph/የጠቅላይ-ሚንስትሩ-ምላሽ-06-14
13.6K viewsedited  11:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 14:07:20
8ሺህ ቤት እድሳት፤ 80 የእሁድ ገበያ በ31 ዙር ፤ 3.4 ሚሊዬን ዳቦ በቀን ማምረት አቅም!!

ቤት እድሳት አዲስ አበባ ውስጥ ከ8ሺህ በላይ የድሃ ቤት እድሳት ስራ መሰራቱን ምን ያሎቻችሁ ታውቃላችሁ፡፡ አሁንም በጣም በርካታ ቤት እየተገነባ ይገኛል፡፡ የእሁድ ገበያ ለማስፋፋት 80 የእሁድ ገበያ አዲስ አበባ ውስጥ ተፈጥሮ ከ31 ዙር በላይ ሽያጭ አካሂዷል፡፡ ይሄ የዋጋ መረጋጋቱ ላይ ከፍተኛ ሚና አለው፡፡

ዳቦና ፋብሪካን ያገናኘነው እኛ ነን፤ አዲስ አበባ ውስጥ በድምር 20 ምናምን ሺህ ዳቦ ብቻ ነበር የሚመረተው፡፡ በጀመርነው ሪፎርም ሸገርና ብርሃን (በሼህ መሃመድ አላሙዲንና የቀዳማይ እመቤት ) ብቻ ከ2 ሚሊዬን ዳቦ በላይ ይጋግራል፡፡ ያ አልበቃ ብሎ አዲስ አበባ ውስጥ 10 ተጨማሪ ፋብሪካዎች ገንብቷል፤ አብዛኛዎቹ ቴስት እያደረጉ ነው አሁን፡፡ በአጠቃላይ 3.4 ሚሊየን ዳቦ መጋገር አቅም ተፈጥሯል አሁን አዲስ አበባ ውስጥ፡፡ ይሄ አልነበረም አዲስ አበባ ውስጥ፡፡

ጠ/ሚ አብይ አህመድ ለም/ቤቱ የሰጡት ምላሽ
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
13.8K viewsedited  11:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 13:18:28
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለቀርቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት መልስ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች

ማህበራዊ ሚዲያንና ጋዜጠኞችን አሰመልክቶ!

-ከለውጡ በኋላ ሚዲያ እየታፈነ ነው የሚባለው ውሸት ነው፣ ከለውጡ በኋላ የሚዲያ ብዝሃነት ጨምሯል፣ ኢትዮጵያ ውስጥ በዩቱብ ታክስ የሚከፍል አንድም ሰው የለመ፣ ይህ ሊታሰብበት ይገባል፣ ጋዜጠኛ ፣ማህበራዊ አንቂና ፖለቲከኛ ተቀላቅለዋል፣ ሀገር እያፈረሱ፣ በሀገር ሕልውና ላይ እየቆመሩ ሙያተኝነት የለም።

ጋዜጠኝነት የወንጀል መደበቂያ ሳይሆን የሀሳብ ማፍለቂያና ማካፈያ መሆን አለበት፣ የትኛውም አካል የተያዘው በሕግ ማስከበር ሥራ እንጂ በሌላው አይደለም፣ ሀገር የሚጠበቅ መከላከያን መስመር አልፎ መድፈርና ለመከፋፈል መሞከር ዋጋ ያስከፍላል።

የህግ ማስከበር ዘመቻውን አሰመልክቶ

በአማራ ክልል የህግ ማስከበር ዘመቻ የተያዙት 3500 ሰው የከዳ ሰራዊት ነው ከእዚህ 2000 በላይ የከዳ የአማራ ልየ ኃይል ሰራዊት ነው፣ ሰልጥኖ ታጥቆ የከዳ ልዩ ኃይል ከየት የመጣ ፋኖ ነው፣ አማራ አሰልጥኖ አስታጥቆ ጠብቀኝ ያለው።

የህግ ማስከበሩ በክልል የሚተገበር መሆኑን ፣ በህዝብ ጥያቄ መጀመሩን በሂደት ህዝቡ ተደስተ መሆኑን ማወቅ ያስፈልጋል፣ ብቸኛ ኃይል የመጠቀም መብት ያለው መንግስት ብቻ ነው፤ አንድም የፌዴራል ኃይል በክልሎች የህግ ማስከበር ዘመቻ አልተሳተፈም፤ ሁሉም አሰፈላጊውን ድጋፍ ይደረጋል።

በከተማ ተኩስ ብቻ ሳይሆን መዝረፍ ፤ ሴቶች መድፈር ህፃን መጥለፍ ነጋዴመዝረፍ ፤ ግብር መሰብሰብ ፎርጅድ ብር ማምረት ይሄ የፋኖ ስራ ሊሆን አይችልም፣ አደንዛዥ ጽዕ የበርካታ ውጭ ምንዛሪ፣ ሐሰት ገንዘብ፣ የጦር መሳሪያ በአማራም በኦሮሚያ ተይዘዋል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
14.1K viewsedited  10:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 13:03:11
#ድርድር
ከህወሓት ጋር ለመነጋገር የሚያስችል ኮሚቴ ተቋቁሟል” - ጠ/ሚ ዐቢይ

በኢትዮጵያ ሰላምን ለማምጣት የሚያስችል ኮሚቴ መቋቋሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ምላሽ፤ ከህወሓት ጋር ለመደራደር ኮሚቴ ተቋቁሞ አስፈላጊ ሁኔታዎችን እየተደረጉ ነውም ብለዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት፤ አሁን ላይ ሰላምን ለማምጣት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የሚመራ ኮሚቴ መቋቋሙን አስታውቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ከህወሃት ጋር ወደ ጦርነት የተገባው በይፋ ነው ድርድሩም የሚካሄደው በይፋ ነው” ብለዋል፡፡“ህወሓት የአማራ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያም ጠላት“ እንደሆነ ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላምን ለማምጣት “የምንደብቅበት ምክንያት የለም” ብለዋል፡፡

ከህወሓት ጋር ንግግር ሲጀመር ይፋ እንደሚደረግ ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ኮሚቴው ያዘጋጀውን በሚመለከት በሁለት ሳምንት ውስጥ ይፋ እንደሚደረግ አንስተዋል፡፡“ከህወሓት ጋር ድርድር የሚደረገው የምንፈልጋቸው ሲሟሉ ነው” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በመንግስት ወገን ሰላም ስለተፈለገ ብቻ ግን ሰላም ሊመጣ እንደማይችል ገልጸዋል፡፡ጠ/ሚኒስቴር ዐብይ አህመድ ዛሬ በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ቀርበዉ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሳላቸዉ ጥያቄ ምላሽ በመስጠት ላይ ይገኛሉ።

T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
13.8K viewsedited  10:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 12:43:19
"ፋኖ ለአማራም ለኢትዮጵያም ኩራት ነው፤ ምንም ጥያቄ የለውም፡፡ በጀግንነት ተዋግቷል፤ በጀግንነት ይዋጋል ወደፊትም!!

እሱ የአብይን ውዳሴ ፈልጎ የሚዋጋ ሳይሆን አገሩን ወዶ የሚዋጋ ነው፡፡ ከተነካችበት አይቆምም ወደፊትም፡፡ አድርጓል ያደርጋል ወደፊትም፡፡ ይሄ መመስገን አለበት መከበር አለበት ወደፊትም፡፡ ጥያቄ የለውም!!

ይህንን ስም ግን መጠቀሚያ ማድረግ ትክክል አይደለም፡፡በከተማ ተኩስ ብቻ ሳይሆን መዝረፍ ፤ሴቶች መድፈር ህፃን መጥለፍ ነጋዴመዝረፍ ፤ግብር መሰብሰብ ፎርጅድ ብር ማምረት ይሄ የፋኖ ስራ ሊሆን አይችልም፡፡

ፋኖ ፎርጅድ ብር አይሰራም፡፡ፋኖ ህፃን አይጠልፍም ፤ሴት አይደፍርም፤ ሲባጎ ወጥሮ ግብር አይሰበስብም፡፡አማራ ክልል የነበረው ይሄ ነው የአማራ ክልል ተወካዮች ታውቃላችሁ፡፡ ማታውቁ ከሆነ ሄዳችሁ ጠይቁ ህዝባችሁን!!"

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
13.4K viewsedited  09:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 12:40:53
አዲሱን ሁሉግራም 4.0 ያውርዱ!

ሁሉግራም 4.0 አፕዴት ሲያወርዱ፤ የአየር ሰዓት በቀላሉ ይሞላሉ፣ የአየር መንገድ ቲኬቶን፣ የዲኤስቲቪ እና የካናል ፕላስ ክፍያዎችን መፈፀም ይችላሉ።

ሁሉም በሁሉግራም ይቻላል!
Download Hulugram SuperApp

https://play.google.com/store/apps/details?id=plus.ride.huluchat
13.1K views09:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 12:37:55
የልብስ ማስጫ (ማድረቂያ)
Three Layers of clothes hanger
3double layer
780*620*1650 mm
እስከ 40kg መሸከም ሚችል
ማጠፍ መዘርጋት ሚቻል
ቦታ ቆጣቢ ,ለcondominuinm....
ልብስን ሳይገረጣ በፍጥነት የሚያደርቅ
በቤት ውስጥም ሆነ ከቤት ውጭ ልብሶችን ለማድረቅ እና ለመስቀል ተስማሚ የሆነ

ዋጋ-3000 2900 ብር

ውሱን ፍሬ/limited stock

በቴሌግራም ለማናገር @AwasMartAdmin

አድራሻችን:- ቦሌ መድሐኔዓለም ቦሌ መሰናዶ ት/ቤት ፊትለፊት አለምነሽ ፕላዛ ግራውንድ ሱቅ ቁጥር 05

ለወዳጅዎ ስላጋሩ እናመሠግናለን

ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/onlineshoppingce

+251941661030 / +251943190237
14.4K views09:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-13 23:17:22
#ጤናመረጃ
ሙቅ ውሃ መጠጣት የሚያስገኛቸው የጤና ጥቅሞች!!

በቂ ንፁህ ውሃ መጠጣት ለቆዳ፣ ለጡንቻና ለመገጣጠሚያ ክፍሎች ጤንነት ያለው ጥቅም የላቀ ነው። ውኃ የሰውነት ሕዋሳት ንጥረ ነገሮችን እንዲመገቡና በሽታን እንዲከላከሉም ይረዳቸዋል።

ሙቅ ውሃ መጠጣት ደግሞ ጤናን ለማሻሻል የሚረዳ ቀላል ዘዴ መሆኑ የተነገረ ሲሆን፥ ከሚያስገኛቸው ጠቀሜታዎች መካከል፦

1. ውሃን አሙቆ መጠቀም የሽንት ችግር እና ኪንታሮትን እና የሆድ በሽታን ከመከላከል ይረዳል በተጨማሪ የሆድ ድርቀትን ይቀንሳል ሲሉ ባለሙያዎች ገልፀዋል።

2. ምግብ በሆዳችን ውስጥ ቶሎ እንደዲዋሃድ!
አንድ ሰው በቂ ውሃ ካልጠጣ ትንሹ አንጀት በምግብ እና በመጠጥ የሚወስደውን ፈሳሽ መጠቀምን ይመርጣል።

3. መርዛማ ነገሮችን ከሰውነት ለማስወገድ!!

ጥናቶች ሙቅ ውሃ መጠጣት መርዛማ ነገሮችን ከሰውነታችን እንዲወገዱ ያግዛል። የሰውነት ሙቀት መጠን በመጨመር በላብ እንዲወጣ ያደርጋል።

4. የተሻለ የደም ዝውውር እንዲኖር!!
የሞቀ ውሃ መጠጣት የደም ቧንቧን ወይም ሥሮችን በማስፋት የደም ዝውውርን ያሻሽላል። ይህ ደግሞ ጡንቻዎች እንደፈለጉት እንዲንቀሳቀሱ እና ህመምን ለመቀነስ ይረዳል።

5. የሰውነት ክብደት ለመቀነስ!
ሁል ጊዜ ውሃን መጠጣት ሰውነታችን ንጥረ ነገሮችን እንዲመገብ እና ውፍረት እንዲቀንስ ይረዳል።

6. የህመም ስሜት ይቀንሳል!
ለተጎዱ ጡንቻዎች የደም ዝውውርን እና ፍሰትን ያሻሽላል፤ የህመም ስሜታትን ሊቀንስ እንደሚችል ተረጋግጧል።

7. ጉንፋንን በመዋጋት የአፍንጫ ጤንነትን ያሻሽላል እንዲሁም የአፍንጫ መቆጣት ጫና ለመቀነስ ይረዳል።

8. ጭንቀትን ለመቀነስ:- የሞቀ ውሃ መጠቀም የአእምሮ ጭንቀት እና ውጥረት ይከላከላል።
ምንጭ፦ medicalnewstoday

ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ! ሼር!
T.me/ethio_mereja
3.2K viewsedited  20:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-13 22:27:36
ሩሲያ በ100 ቀናት ወደ ውጪ ከላከችው ነዳጅ 98 ቢሊየን ዶላር ገቢ አገኘች!!

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ጦርነት ከገጠመች ወዲህ ባሉት የመጀመሪያዎቹ 100 ቀናት ወደ ውጭ ከላከችው ነዳጅ 98 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ማግኘቷ ተመላከተ።

የሩሲያን ነዳጅ በብዛት ከገዙ ሀገራት ውስጥ የአውሮፓ ሀገራት ቀዳሚውን ስፍራ መያዛቸውም ተነግሯል። የአውሮፓ ሀገራት ከሚያስፈልጋቸው የተፈጠሮ ጋዝ ውስጥ 40 በመቶውን ከሩሲያ የሚያገኙ ሲሆን፤ 27 በመቶ የነዳጅ ፎጆታቸውንም ከሩሲያ በሚያስገቡት ነው የሚሸፍኑት።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
5.4K viewsedited  19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ