Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO-MEREJA®

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja — ETHIO-MEREJA®
ርዕሶች ከሰርጥ:
Ethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 130.68K
የሰርጥ መግለጫ

Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot ✔

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 265

2022-06-15 13:03:16
"አሳዛኝ ሽንፈት ገጥሞናል” :- ፕሬዝዳንት ዜሌንስኪ

ዩክሬን በተለያዩ የጦር ግንባሮች አሳዘኝ እና አስከፊ ሽንፈት እንደገጠማት ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ አስታወቁ፡፡

ፕሬዚዳንቱ ዩክሬን አስከፊ እና አሳዛኝ ሽንፈት በዶንባስ እና በሌሎች ግንባሮች እንደገጠማት ልትረዱልን ይገባል ብለዋል፡፡ ዩክሬናውያን ዘመናዊ ፀረ-ሚሳዔል የጦር መሳሪያ እንደሚያስፈልጋቸውም አጽንኦት ሰጥተዋል ፡፡ኪዬቭ የዩክሬን ዳርድንበር የታፈረ እና የተከበረ ይሆን ዘንድ ይህን ማድረግ እጅግ ወሳኝ ነው የሚል አቋም አላት፡፡

የዩክሬን ጦር ራሱን የሚከላከልበት መሳሪያ ጭምር እያጣ ስለመሆኑም ተነሯል። ምዕራባውያን ለዩክሬን ቃል ከገቡት የጦር መሳሪያ ውስጥ ለወታደሩ የደረሰው አስር በመቶ ብቻ ነው። የሞት ሽረት የሚደረግባት እና ወሰኟ ሴቬሮዶኔስክ ከተማ አብዛኛው ክፍል በሞስኮ ጦር እጅ በመውደቁ ዩክሬናውያን አስከፊውን ሽንፈት እያስተናገዱ ናቸው ተብሏል ፡፡ፕሬዚዳንት ዜሌንስኪም ይሄኑ አረጋግጠዋል።

ሽንፈት ቢገጥመንም ግዛታችንን ለማስከበር አሁንም እንፋማለን ይላሉ ፕሬዚዳንቱ፡፡የፑቲን ኃይሎች በተራዘመ ጦርነት ድል የመቀዳጀት ባህልን እንደ ታሪካዊ ልምድ በመውሰድ በኪዬቮች ላይ የከፋ ጥቃት እንዳይሰነዝሩም ስጋት ተጋርጧል ፡፡
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
17.8K viewsedited  10:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 12:32:03
አቺባደም ሆስፒታል ነን!

አሁን በቴሌግራም መጥተናል . . .

አቺባደም በቱርክ ውስጥ 22 ሆስፒታሎች እና 18 የተመላላሽ ታካሚ ክሊኒኮች ያሉት እንዲሁም ሁሉም የህክምና ክፍሎች የተወከሉበት ግንባር ቀደም የጤና እንክብካቤ ማዕከል ነው። የኢንስታግራም መገኛ አካውንታችንን @ acibadem.ethiopia ይከተሉ እና ነፃ ምክሮች ከእኛ ያግኙ፣ ጠቃሚ የጤና ጥቆማዎች፣ የህክምና ወቅታዊ መረጃዎች እና በቱርክ አቺባደም ሆስፒታሎች ስለሚሰጡ የአንደኛ ደረጃ /A-class/ አገልግሎቶች ለማወቅ ከመጀመሪያዎቹ መካከል ይሁኑ።

ለተከታታይ ጠቃሚ መረጃዎች የቴሌግራም ቻናላችንን https://t.me/acibadem_ethiopia ይቀላቀሉ፡፡
17.2K views09:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 01:50:46
#ጤናመረጃ
የአብሽ 10 የጤና ጥቅሞች!


አብሽ ለጤና ምን ያህል ጠቃሚ እንደሆነ ያውቃሉ?

ለልብ ድካም፣ ለደም ግፊት፣ ኮሌስትሮል ለመቀነስ፣ ለጨጓራና በስካር በሽታ ለሚሰቃዩ ፍቱን መድሃኒት ነው::ገና ለወለዱ እናቶችም የጡታቸውን መጠን የተወሰነ ለመጨመር ይጠቅማል።

ጥቅሞቹ በዝርዝር ቀጥሎ ቀርበዋል፦

የስኳር በሽታን ለመቆጣጠር ይረዳል፦ አብሽ ደም ውስጥ የሚገኘውን የስኳር መጠን በመቆጣጠር ኢንሱሊን መቋቋምን ይቀንሳል።

የልብ በሽታን ያስወግዳል፦ የልብ ጉዳትን ለመከላከልና ኦክሲዳቲቭ ውጥረት ለማስወገድ ይረዳል።

የወር አበባ ቁርጥማትን ያስታግሳል፦ አብሽ ከቁርጥማት በተጨማሪ ራስ ምታት፣ ማቅለሽለሽና ድካምን ለመቀነስ ይረዳል።

የጡት ወተት ምርትን ያሻሽላል፦ አብሽን መጠጣት የወተት ምርትን የሚጨምር ውህድ ስላለው፤ ለሚያጠቡ እናቶች ይረዳል።

የምግብ መፍጨት ችግርን ይረዳል፦ የሆድ ድርቀትንና ከጨጓራ መቆጣት የተነሳ ለሚከሰት የምግብ መፍጨት ችግርን ለመከላከል ይረዳል።

የጸጉር መሳሳትን ለመከላከልና ለፀጉር እድገት ጠቃሚ ነው። የተፈጨ አብሽን ሳይወፍር በብርጭቆ ውሀ በማዋሀድ መቀባት።

አብሽ መጠጣት አቅም ማጣትን ለማከምና የወሲብ ችሎታን ለመጨመር ይረዳል።

አብሽ መጠጣት ብጉርን ለመከላከል ይረዳል።

ፀረ-እርጅና ጥቅም አለው፦ለቆዳችን አስደናቂ ጠቀሜታ ያለው ሲሆን የእርጅና ምልክትን እንደ የቆዳ መጨማደድና ቀጫጭን መስመርን ያስወግዳል።

ቆዳን ለማርጠብ፦ የአብሽ የሚሙለጨለጨው በሀሪ የደረቁ ቆዳዎችን በማስወገድ ቆዳችን እንዲረጥብ ይረዳናል።

አጠቃቀሙ፣ በ1 ብርጭቆ ውሃ ውስጥ 2 የሾርባ ማንኪያ ነው መጠጣት ያለብዎት። ተፈጥሯዊ ስለሆነ ምንም አይነት ጉዳት የለውም። ክብደት እንዳይጨምሩ በመጠኑ ይጠቀሙ።

ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ! ሼር!
T.me/ethio_mereja
902 viewsedited  22:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 22:51:51
መስከረም አበራ ከእስር ሳትለቀቅ ቀረች!

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በስር ፍርድ ቤት የተወሰነላትን የ30 ሺህ ብር ዋስትና በዛሬው ውሎው አጽንቶላት የነበረችው መስከረም አበራ፤ በፖሊስ ለሁለተኛ ጊዜ ይግባኝ ተጠይቆባት ከእስር ሳትለቀቅ ቀረች። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን “የህግ ስህተት አለ” በሚል ይግባኝ የጠየቀው፤ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት እንደሆነ ጠበቃዋ አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

የዛሬውን የከፍተኛውን ፍርድ ቤት ውሳኔ ተከትሎ፤ የመስከረም ቤተሰቦች የ30 ሺህ ብር የዋስትና ገንዘቡን ከምሳ ሰዓት በፊት ከፍለው፤ ሂደቱን ጨርሰው እንደነበር ባለቤቷ አቶ ፍጹም ገብረ ሚካኤል ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስረድተዋል።

ሆኖም የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ባልደረቦች “ይግባኝ እንጠይቃለን” በሚል ወደ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ይዘዋት መሄዳቸውን አክለዋል። ኢትዮ ንቃት” የተሰኘ የዩቲዩብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና ባለቤት በሆነችው መስከረም ዛሬ ወደ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ብትወሰደም፤ ፖሊስ ለጠየቀው ይግባኝ “ፋይል ባለማደራጀቱ” ጉዳዩ ለነገ ረቡዕ መቀጠሩን ጠበቃዋ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
4.4K viewsedited  19:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 22:03:59
"የእምነት ተቋማት ህግ ወጥቶ ኦዲት መደረግ አለባቸው" - ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ

ዛሬ ማክሰኞ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በወቅታዊ ሃገራዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያን የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) "የእምነት ተቋማት ህግ ወጥቶ ኦዲት መደረግ አለባቸው" ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ዶ/ር ዐቢይ የእምነት ተቋማት ዋና የሌብነት ምንጭ ናቸውም ነው ያሉት፡፡ ህግ አውጥተን ኦዲት መደረግ አለባቸውም ብለዋል፡፡ የሃይማኖት ተቋማት "ታክስ እንኳን ባይከፍሉ እያንዳንዱ ሃብት ለተቋሙ መዋሉ መረጋገጥ አለበት" ሲሉም ተናግረዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ "ግለሰቦች ሃብት እያከማቹ እንደፈለጉ የሚያተራምሱበት ሃገር አይኖርም ከአሁን በኋላ" ሲሉም ነው የተናገሩት፡፡የሚሰበሰበው ሃብት ኦዲት ተደርጎ ለልማት የሚውልበት መንገድ መፈለግ እንዳለበትም ገልጸዋል፡፡

T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
6.6K viewsedited  19:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 20:39:52
ድሬዳዋ!!

ቤት ተከራዮችን በሚመለከት የድሬደዋ አስተዳደር የሰጠው ውሳኔ!!

በድሬደዋ ከተማ በመኖርያ ቤት ተከራዮች ላይ ምክንያታዊ ያልሆነ እና አለአግባብ ከፍተኛ ጭማሪ እየተደረገ መሆኑን በተለያየ መንገድ አረጋግጫለሁ ያለው የድሬደዋ አስተዳደር ለቀጣዮቹ አምስት ወራት በመኖርያ ቤት ተከራዮች ላይ ጭማሪ ማድረግም ሆነ ተከራዮችን ቤት ማስለቀቅ እንደማይቻል ውሳኔ አሳልፏል።

የድሬደዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ፈለቀ ለሚዲያ በሰጡት መግለጫ የመኖርያ ቤት ኪራይ ጭማሪ በዝቅተኛ ኑሮ በሚገኘው ነዋሪ ላይ ያሳደረውን ጫና የገመገመው የአስተዳደሩ ካቢኔ ጭማሪን ለአምስት ወራት የሚከለክል ውሳኔ ማሳለፉን ገልፀዋል።

"ምክንያታዊ ያልሆነ" ያሉት የመኖርያ ቤት ኪራይ ጭማሪ በተለይ በዝቅተኛ ኑሮ ላይ የሚገኙ ነዋሪዎችን ለከፍተኛ ችግር ያጋለጠና ከማህበረሰቡም ከፍተኛ ቅሬታ እያስነሳ በመሆኑ ውሳኔው መወሰኑን ኃላፊው አስረድተዋል።ሼር
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
10.3K viewsedited  17:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 20:30:02
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት

Join our telegram

https://t.me/+P7ctetopPExiY2Rk
9.8K views17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 18:26:44
በጋምቤላ ከተማ ተከስቶ የነበረው የፀጥታ ችግር ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር እንደተቻለ የክልሉ መንግስት አስታወቀ!

በጋምቤላ ከተማ ተከስቶ የነበረው የፀጥታ ችግር በክልሉ የሚገኙ የፀጥታ ሀይሎች ባካሄዱት ቅንጅታዊ ማጥቃት ከተማውን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር እንደተቻለ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ ገለፁ።

በጥቃቱ በጠላት በኩል ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ መድረሱን ጠቁመው ከወገን ጦር በኩልም መጠነኛ ጉዳት መድረሱን አመልክተዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ኡሞድ ኡጁሉ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በጋምቤላ ከተማ ተኩስ ከፍተው በነበሩ የጠላት ሀይል ላይ የፀጥታ አካላት በወሰዱት የተቀናጀ እርምጃ ከተማዉን ማረጋጋት ተችሏል ብለዋል።

በተለይም የፀጥታ ሀይሉ በወሰደዉ ጠንካራ እርምጃም በታጣቂ ቡድኑ ላይ ከፍተኛ ሰበአዊና ቁሳዊ ኪሳራ መድረሱን አመልክተው በወገን ጦር ላይም መጠነኛ ጉዳት መድረሱን አብራርተዋል።በጋምቤላ ከተማ በሚገኙ የመንግስት ተቋማት ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱን የጠቆሙት ርዕሰ መስተዳድሩ ከጥቂት ሰዓታት በፊት በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የርዕሰ መስተዳድሩን ጽህፈት ቤት ተቆጣጥረዋል በሚል የተናፈሰው ወሬ ሀሰተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ ሊገነዘብ ይገባል ብለዋል።

በአሁኑ ሰዓት በከተማው በአንዳንድ አካባቢ ተደብቆ የሚገኝ የጠላት ሀይል ካለ በአቅራቢያቸው ለሚገኝ የፀጥታ ሀይል ጥቆማ እንዲሰጡ ጠይቀዋል።

ህብረተሰቡ አካባቢውን ነቅቶ በመጠበቅ በተለይም ከምሽቱ 2 ሰዓት ጀምሮ በቤቱ በመቀመጥ ለሠላሙ ተባባሪ መሆን እንደሚኖርበት አስረድተዋል።በጥቃቱ ህይወታቸውን ላጡና ጉዳት ለደረሰባቸው አካላት በክልሉ መንግስት እና ህዝብ ስም መጽናናትን ተመኝተዋል ሲል የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤቱ በኩል ባሰራጨው መረጃ አስታዉቋል።
T.me/ethio_mereja
12.9K viewsedited  15:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 17:23:22
የድምፃዊ ዳዊት ነጋ ስርአተ ቀብር ተፈፀመ።

የአርቲስት ዳዊት ነጋ ስርዓተ ቀብር ወዳጅ ዘመዶቹ ፤ አድናቂዎቹ በተገኙበት በአ/አ ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን ዛሬ ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ/ም ተፈፅሟል፡፡

በድጋሜ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና አድናቂዎቹ መጽናናትን እንመኛለን። ነብስ ይማር
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
13.1K viewsedited  14:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 16:16:14
በጋምቤላ ክልል ተኩስ ከፍተው ነበሩ በተባሉ የሸኔ እና የጋምቤላ ነፃነት ግንባር ታጣቂዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ክልሉ አስታወቀ!!

ክልሉ እንዳለው በታጣቂዎቹ ላይ በተወሰደው ጠንካራ እርምጃ ከተማዉን ማረጋጋት መቻሉን አስታውቋል። አክሎም በተወሰደዉ እርምጃ በታጣቂ ቡድኑ ላይ ከፍተኛ ሰበአዊና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሷል ሲል አመልክቷል።

ክልሉ የከተማው ህብረተሰብ ከቤት ባለመውጣት ለፀጥታ ሀይሉ እያደረገ ላለው ትብብር ምስጋና አቅርቧል። በከተማው ከጠዋቱ 12:30 ጀምሮ ያለማቋረጥ ለረጅም ሰዓት የተኩስ ልውውጥ ሲደረግ እንደነበር አስታውሶ በአሁኑ ሰዓት ተቆርጠው የቀሩ የቡድኑ አካላትን የማጥራት ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድቷል።

"ታጣቂ ቡድኑን ሙሉ በሙሉ ለመደምሰስ በመንግስት ፀጥታ አካላት እየተወሰደ ያለዉ የማያዳግም እርምጃም ተጠናክሮ ይቀጥላል " ሲልም የክልሉ አስተዳደር አስታውቋል።

ታጣቂዎቹ ዛሬ ማክሰኞ ማለዳ ላይ ጥቃት ከፍተው የከተማዋን የተወሰነ ክፍል ተቆጣጥረው እንደነበረም ክልሉ ገልጿል። ክልሉ በመግለጫው እንዳመለከተው በጋምቤላ ከተማ “የሸኔ እና የጋምቤላ ነፃነት ግንባር” በጋራ ጥቃት ከፍተው እንደነበረና ከረፋድ አራት ሰዓት በኋላ መጠነኛ መረጋጋት እንዳለ አመልክቷል።

በታጣቂዎች እና በፀጥታ ኃይሎች መካከል ዛሬ ማክሰኞ ከማለዳ ጀምሮ በተካሄደ የተኩስ ልውውጥ በክልሉ የፀጥታ አባላት እና በታጣቂዎቹ ላይ ጉዳት መድረሱንም ተገልጿል። አንድ የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣን ክስተቱ በጋምቤላ ከተማ ውስጥ ማጋጠሙን አረጋግጠው፣ በዚህም የሰው ህይወት መጥፋቱንና የተጎዱ መኖራቸውን ገልጸዋል።

የደረሰው ጉዳት በቀጣይ እንደሚገለጽ ተገልጿል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮመረጃ
14.1K viewsedited  13:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ