2023-03-19 15:33:11
የመስቀለ ክርስቶስ በዓል በዋግኽምራ በታሪካዊው የደብረሰላም ውቅር መስቀለ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ተከበረ።
መ/ር ጌታቸው በቀለ
(EOTC TV //መጋቢት ፲ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ዋግኽምራ )
በዋግኽምራ ሀገረ ስብከት በጥንታዊውና በታሪካዊው የደብረሰላም ውቅር መስቀለ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን መጋቢት ፲ ቀን የጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል የተገኘበት ታላቅ በዓል በድምቀት ተከበረ።
በበዓሉ ላይ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ በርናባስ እና ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትና የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተገኝተዋል። የዕለቱን ትምህርት የሰጡት ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ "ለሚፈሩት ምልክትን ሰጠሃቸው" በማለት ስለ ነገረ መስቀሉ ትምህርት ሰጥተዋል።
ቅዱስ ጳውሎስ በፊልጵስዩስ ፫:፲፰-፲፱ "ብዙዎች ለክርስቶስ መስቀል ጠላቶች ሆነው ይመላለሳሉና፤ ብዙ ጊዜ ስለእነርሱ አልኋችሁ አሁንም እንኳ እያለቀስሁ እላለሁ፤ መጨረሻቸው ጥፋት ነው፤ ሆዳቸው አምላካቸው ነው ክብራቸው በነውራቸው ነው፤ ሐሳባቸው ምድራዊ ነው" እንዲል ጉድገጓድ ቆፍረው በአይሁዳና በኢየሩሳሌም ሁሉ የቆሻሻ መጣያ ሆኖ ዕሌኒ ንግሥት እስከ መጣችበት ድረስ ለ፫፻ ዓመታት ያህል ተቀብሮ ኖረ።
የዕሌኒ ልጇ ቆስጠንጢኖስ በመስቀሉ ኃይል የክርስቲያኖች ጠላት የሆነውን መክስምያኖስን ድል ከነሣ በኋላ ክርስቲያን ሆነ፤ እርሷም ልጄ ክርስቲያን ከሆነ ኢየሩሳሌም ሄጄ የፈረሱትን አብያተ ክርስቲያናት አሠራለሁ፤ የጌታዬን መስቀል ከተቀበረበት አስወጣለሁ ብላ ተስላ ነበር። ስለቷ በመፈጸሙ ደስ ተሰኝታ መስከረም ፲፮ ቀን ደመራን አስደምራለች። የእሳቱ ጢስ ወደ ሰማያት ወጥቶ መስቀሉ ካለበት ቦታ ላይ ተተከለ። በዚህም ፈጣሪዋን አመስግና ቁፋሮውን መስከረም ፲፯ ቀን አስጀመረች። ከዚያም መጋቢት ፲ ቀን በ፫፻፳፯ ዓም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ክቡር ደሙን ያፈሰሰበት ቅዱስ መስቀል ተገኘ።
ይህን መሠረት በማድረግ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በየዓመቱ መጋቢት ፲ ቀን መስቀሉ የተገኘበትን በድምቀት ታከብራለች።
በበዓሉ ላይም በርካታ ምእመናን ተገኝተዋል።
EOTC TV
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
"የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ"
የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት
የዲጂታል ሚዲያ ገጾች
ለመረጃ +251985585858
➽ የዩቲዮብ ገጻችን
http://www.youtube.com/c/eotctv
➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን
https://www.facebook.com/eotctvchannel
➽የቴሌግራም ገጻችን
https://t.me/eotctvchannel
➽ የቲክ ቶክ ገጻችን
https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Eotc tv 2
➽የትዊተር ገጻችን
https://twitter.com/EotcT/
➽የኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/p/CknRF0MtB77/?igshid=MDJmNzVkMjY=
5.3K viewsEOTC TV, 12:33