Get Mystery Box with random crypto!

El OlaM ▣

የቴሌግራም ቻናል አርማ elolam_the_everlasting_god — El OlaM ▣ E
የቴሌግራም ቻናል አርማ elolam_the_everlasting_god — El OlaM ▣
የሰርጥ አድራሻ: @elolam_the_everlasting_god
ምድቦች: ንድፍ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.10K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ገፅ የምታገኟቸው፤
#የሚያንፁ መንፈሳዊ ፅሁፎች✉️፤
#የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን በምስል🖼፤
#መንፈሳዊ መፅሀፎችን📚፤

#ማራናታ🙌

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-20 01:40:52
ይህ መዝሙር ብዙ ተንበርክኬ የሰማሁትና አብሬ የዘመርኩት ነው። አድምጡት፤ ዘምሩት፤ ጸልዩት።

በደልን ይቅር የሚል፥ ዓመጻን የሚያሳልፍ፥
ከጠላት ሊያድናቸው በሕዝቡ ላይ የሚሰፍፍ፥
እንዳንተ ያለ አምላክ ምሕረቱ የበዛ፥
ቅዱሳንንህ ሲሰደዱ መከራውም ሲበዛ።

ርስትህን ለማላገጫ አሳልፈስ አትስጥ፤
የተቀደሰ መቅደስህን ለጠላት አታስረግጥ።

የእግዚአብሔር እድል ፈንታ ተጽፏል ሕዝቡ ነው፤
ሊያመልከው ሊያገለግለው ከግብጽ አገር ያፈለሰው፥
አርነቱን በባርነት ሊተካ የሚከጅለው፥
ይገባኛል የሚል ማነው? ሕዝቡ የእግዚአብሔር ነው።

እስከዛሬ ከብረሃል በአሕዛብ ተፈርተሃል፤
የጠላትን እርግማን በረከት አድርገሃል፤
ያሳዳጁን ፈረሶች በባህር አስጥመሃል፤
በክንድህ ተከላክለህ ርስትህን ጠብቀሃል።
(መዝሙር በተስፋዬ ጋቢሶ)
1.1K viewsSam Sisay, 22:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 01:39:41 ርስትህን ለማላገጫ አሳልፈህ አትስጥ

የኢዩኤል ዘመን ወይም ትንቢተ ኢዩኤል የተጻፈበት ዘመን የታወቀ አይደለም። በመጽሐፉ የትኛውም ንጉሥ በስም ስላልተጠቀሰ ወይም ምንም ፍንጭ ስላልተሰጠ፥ ወይም በመጽሐፉ ውስጥ የተጻፈው በተከታታይ ዓመታት የተፈጸመ የአንበጣ ወረራ በሌሎች መጻሕፍት እና ታሪኮች ውስጥ ስላልተዘገበ፥ ኢዩኤል ስለኖረበት ወይም መጽሐፉ ስለተጻፈበት ዘመን የሚታወቅ ነገር የለም። ስለ ካህናት፥ ስለ እግዚአብሔር ቤት፥ ስለ መቅደስ አገልጋዮች፥ ስለ ይሁዳ፥ ስለ ጽዮን፥ ስለ ኢየሩሳሌም ስለሚናገር ኢዩኤል ያገለገለው በኢየሩሳሌም ወይም በይሁዳ ሆኖ ከኢየሩሳሌም መወረርና ከመቅደሱ መፍረስ በጣም ቀድሞ ሳይሆን አይቀርም። በትንቢቱ ውስጥ ከልመናዎቹ አንዱ ርስቱን ለማላገጫ አሳልፎ እንዳይሰጥ ነው።

አስፈሪው ነገር፥ ኋላ ግን ሰጠ። እግዚአብሔር ርስቱን በገዛ እጁ አሳልፎ ሰጠ። (ዳን. 1፥2)

ርስቱ ሕዝቡ ነው፤ ርስቱ ሕዝቡ ነን።

ኢዩ. 2፥12-17
12፥ አሁንስ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ በፍጹም ልባችሁ፥ በጾምም፥ በልቅሶና በዋይታ ወደ እኔ ተመለሱ። 13፥ ልባችሁን እንጂ ልብሳችሁን አትቅደዱ፤ አምላካችሁም እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ፥ ቍጣው የዘገየ፥ ምሕረቱም የበዛ፥ ለክፋትም የተጸጸተ ነውና ወደ እርሱ ተመለሱ። 14፥ የሚመለስና የሚጸጸት እንደ ሆነ፥ ለአምላካችሁም ለእግዚአብሔር የእህልና የመጠጥ ቍርባን የሚሆነውን በረከት የሚያተርፍ እንደ ሆነ ማን ያውቃል? 15፥ በጽዮን መለከትን ንፉ፥ ጾምንም ቀድሱ፥ ጉባኤውንም አውጁ፥ 16፥ ሕዝቡንም አከማቹ፥ ማኅበሩንም ቀድሱ፥ ሽማግሌዎቹንም ሰብስቡ፥ ሕፃናቱንና ጡት የሚጠቡትን አከማቹ ሙሽራው ከእልፍኙ፥ ሙሽራይቱም ከጫጉላዋ ይውጡ። 17፥ የእግዚአብሔርም አገልጋዮች ካህናት ከወለሉና ከመሠዊያው መካከል እያለቀሱ፦ አቤቱ፥ ለሕዝብህ ራራ፥ አሕዛብም እንዳይነቅፉአቸው ርስትህን ለማላገጫ አሳልፈህ አትስጥ፤ ከአሕዛብ መካከል፦ አምላካቸው ወዴት ነው? ስለ ምን ይላሉ? ይበሉ።

ይህ መዝሙር ብዙ ተንበርክኬ የሰማሁትና አብሬ የዘመርኩት ነው። አድምጡት፤ ዘምሩት፤ ጸልዩት።

በደልን ይቅር የሚል፥ ዓመጻን የሚያሳልፍ፥
ከጠላት ሊያድናቸው በሕዝቡ ላይ የሚሰፍፍ፥
እንዳንተ ያለ አምላክ ምሕረቱ የበዛ፥
ቅዱሳንንህ ሲሰደዱ መከራውም ሲበዛ።

ርስትህን ለማላገጫ አሳልፈህ አትስጥ፤
የተቀደሰ መቅደስህን ለጠላት አታስረግጥ።

የእግዚአብሔር እድል ፈንታ ተጽፏል ሕዝቡ ነው፤
ሊያመልከው ሊያገለግለው ከግብጽ አገር ያፈለሰው፥
አርነቱን በባርነት ሊተካ የሚከጅለው፥
ይገባኛል የሚል ማነው? ሕዝቡ የእግዚአብሔር ነው።

እስከዛሬ ከብረሃል በአሕዛብ ተፈርተሃል፤
የጠላትን እርግማን በረከት አድርገሃል፤
ያሳዳጁን ፈረሶች በባህር አስጥመሃል፤
በክንድህ ተከላክለህ ርስትህን ጠብቀሃል።

(መዝሙር በተስፋዬ ጋቢሶ)

ዘላለም መንግሥቱ
920 viewsSam Sisay, 22:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 11:37:15 ይህ ከሆነ እንደተቀበልነው በእርሱ መመላለስ አለብን። እርሱ ጌታችን ስለሆነ እኛ እንደ እርሱ ተከታዮች፥ ደቀ መዝሙሮች፥ እንደ ክርስቲያኖች ሆነን መመላለስ አለብን። እንግዲህ ጌታን ክርስቶስ ኢየሱስን እንደ ተቀበላችሁት በእርሱ ተመላለሱ። ሰዎች ጌታን መቀበል የማይፈልጉት ስጦታውን ሳይፈልጉ ቀርተው ሳይሆን ስጦታው ጌታ ነውና ጌታ ስለሆነ የሚጠይቀው የፈቃድ ዋጋ ስላለ ነው። የመመላለስ ዋጋ። እርሱን የመምሰል ዋጋ። ግን ይህ ዋጋ ኋላ ከምንቀበለው ደመወዝ ጋር ሲነጻጸር ተመን የለውም።

የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነውና፤ የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ ግን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን የዘላለም ሕይወት ነው። ሮሜ 6፥23

ይህንን አጭር ትምህርት ስጨርስ ልጋብዛችሁ እወዳለሁ። እግዚአብሔር ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ሰጥቶናል፤ ስጦታ ነው። እኛስ ተቀብለነዋል? ይህ መቀበል ከላይ እንዳልኩት ሥርዓት መፈጸም አይደለም። ፈቃድን ለፈቃዱ ማስገዛት ነው። እርሱን የሕይወታችን ጌታ ማድረግ ነው።

ምናልባት ጌታን መቀበል ሳይገባችሁ ኖራችሁ አሁን የተከሰተላችሁና ጌታን ለመቀበል የምትፈልጉ ከኖራችሁ፤ ሁለት ነገሮች አድርጉ፤

1. ኃጢአተኛ መሆናችሁን አውቃችሁ ተጸጸቱና እግዚአብሔርን ይቅርታ ጠይቁት። እኔ ኃጢአተኛ ነኝ ይቅር በለኝ። በሉት። የዚህ ይቅርታ መገኛ ደግሞ ከላይ ያልኩት ክርስቶስ አምላክ ሳለ ሰው ሆኖ ኃጢአታችንን በመስቀል ላይ መውሰዱ ነው። ይቅር በለኝ ስንል ይህ የኃጢአታችን ደመወዝ በዚያ መስቀል ላይ መከፈሉን መገንዘባችን ነው።

2. ይቅርታ ከጠየቅን በኋላ ጌታ እርሱ ጌታችን እንዲሆን ወደ ልባችን እንዲገባ መጋበዝ ነው። ጌታ ሆይ ና ወደ ሕይወቴ፥ ወደ ልቤ፥ ወደ ኑሮዬ ግባ፤ መሪዬ ጌታዬ ሁን እንበለው።

ይህን ካደረግን እንደ ተስፋ ቃሉ ታማኝ ነውና ወደ ሕይወታችን ይገባል። አዲስ ፍጥረትም ሆነናል። ከዚህ አዲስነት በኋላ በቅርባችን የምትገኝ ወንጌልን የምትሰብክ፥ ቃሉን የምትኖር ቤተ ክርስቲያን ፈልገን አብረን ማምለክ፥ ይህን ያገኘነውን አዲስ ሕይወት ለሌሎች ማካፈል እና በቆላ. 2፥6 እንደተጻፈው በእርሱ መመላለስ እንጀምር።

እኔ ጌታን ተቀብያለሁ። አንተስ፥ ጌታን ተቀብለሃል? አንቺስ፥ ጌታን ተቀብለሻል?

ዘላለም መንግሥቱ
1.0K viewsSam Sisay, 08:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 11:37:15 ጌታን ተቀብለሃል? ጌታን ተቀብለሻል? (ለሌሎች አካፍሉት)

ሰዎች ጌታን ተቀበይ ወይም ተቀበል ብለው ሲጋብዙን ወይም፥ ጌታን የግል አዳኝህ አድርገህ ተቀብለሃል? ተቀብለሻል? ሲሉ፥ ወይም እኔ ጌታን የተቀበልኩት በዚህ በዚህ ቀን ነው ሲሉ ሰምተን እናውቃለን? ለምሳሌ፥ እኔ ጌታን የተቀበልኩት በኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1975 ከፋሲካ ቀጥሎ በነበረው ማክሰኞ ግንቦት 2 ቀን ነው። [ወይም May 10, 1983 ነው።]

ግን ምንድርን ነው ይህ ጌታን መቀበል? ጌታን መቀበል የተወሳሰበ የስነ መለኮት ቃል አይደለም። ፍቺና ፈቺ የሚፈልግ ጥልቅ አስተምህሮም አይደለም። ይህንን ትልቅ እና ድንቅ እውነት እግዚአብሔር የተወሳሰበ አድርጎ አላቀረበም። በጣም ግልጽ፥ በጣም ቀላል ነው። ሁላችንም ሰጥተንም ተቀብለንም እናውቃለን። ይህ መስጠትና መቀበል ከሰው ፍጥረት ጀምሮ የኖረ ልምድ ነው። በመስጠትና በመቀበል ውስጥ ሰጪ አለ፤ ተቀባይ አለ፤ ስጦታ ደግሞ አለ።

ይህንን ጌታን መቀበል የሚለውን እውነት የሚያስረዱን ሁለት ጥቅሶች እንመልከት።
የመጀመሪያው፥ የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፥ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም። ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው። የሚለው ነው፤ ዮሐ. 1፥11-12።

ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ የመጣ አምላክ ነው። ሙሉ አምላክ ሆኖ ከአምላክነቱ ምንም ሳይቀነስ ፍጹም ሰው ሆኖ የመጣ ነው። በሥጋ መምጣት የኖረበት ምክንያት ሊቤዠን ወይም ቤዛ ለመሆን ነው። ቤዛ ማለት ምትክ ማለት ነው። በምትካችን ሊሞት፥ ኃጢአታችንን ሊወስድ ማለት ነው። ሳይሞት ኃጢአታችንን ሊወስድ ወይም ሊደመስስ አይችልም ነበር ወይ? ኃጢአት እንዲህ በቀላሉ ድምስስ የሚል ነገር አይደለም። ኃጢአት ደመወዝ አለው፤ ደመወዙም ሞት ነው፤ ሮሜ 6፥23። ኃጢአት የእግዚአብሔር ተቃራኒ ባህርይ ነውና ኃጢአት ሁሉ ሕይወትን ይጠይቃል።

ሰው ሁሉ ደግሞ በአዳም በኩል እና በራሱም ሥራ ኃጢአተኛ ነው። ማንም ኃጢአት የለብኝም ወይም ኃጢአተኛ አይደለሁም ማለት አይችልም። ሮሜ 3፥23። ሁሉ ከኃጢአት በታች፥ ከፍርድ በታች ናቸው። የኃጢአት ደመወዙ ሞት ከሆነ ደግሞ ሁሉ ሟቾች ናቸው። አንድም በሕይወት የሚተርፍና የሚኖር የለም። ማንም ደግሞ የማንንም ሞት መውሰድ አይችልም። አዳኝ ወይም ቤዛ ለሰው ልጅ ኃጢአት መሞት ከኖረበት ያ ቤዛ ማሟላት ያለበት አራት ነገሮች አሉ። (ከአንድ ጓደኛዬ የትርጉም መጽሐፍ የወሰድኩት ነው።) እነዚያም

1ኛ፥ ሰው መሆን አለበት። ጌታ አምላክ እያለ ሰው የሆነው በዚህ ዋና ምክንያት ነው። ለመሞት ሥጋ መልበስ አለበት። ደሙን ለማፍሰስ ደም እንዲኖረው ያስፈልጋል፤ ደም እንዲኖረው ሰው መሆን አለበት።

2ኛ፥ ምንም ኃጢአት የሌለበት መሆን ይገባዋል። ያለዚያ ራሱም ኃጢአተኛ ነዋ! የራሱ ኃጢአት ምን አድርጎ ለሌላው ይሞታል? ለራሱ ኃጢአት ብቻ ነው የሚሞተው። ሌላውን ማዳን አይችልም።

3ኛ፥ አምላክ መሆን አለበት፤ ይኸውም በምትክነት የሚሰዋው ቁጥር ስፍር ለሌለው ኃጢአትና እጅግ ብዙ ኃጢአተኞች በመሆኑ ነው። ሰው ብቻ ከሆነ ከሰው ይህን ማድረግ የሚችል ንጹሕ ሰው የለም። ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና። ይህ ቤዛ ከተራ ሰው በላይ የሆነ ሰው መሆን አለበት።

4ኛ፥ እራሱን ለሌሎች ኃጢአት ሲል አሳልፎ ለመስጠት ፈቃደኛ መሆን አለበት።

ጌታችን እነዚህን መስፈርት የሚያሟላ ቤዛ ነው። ይህንን ሆኖ ነው ወደ ወገኖቹ የመጣው። የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፥ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም። ሰው ሆኖ መምጣት ከኖረበት ወደ አንድ ወገን መምጣት አለበት። ያ ወገን ማንም ሊሆን ይችላል። ያንን ወገን ከአብርሃም ወገን እንዲሆን እግዚአብሔር መረጠ። ተስፋ ሰጠ። በትንቢት ተናገረ፤ ሕጻን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናል እያሉ ነቢያት ተናገሩ። ተሰጥቶናል ሲሉ ስጦታ መሆኑን መናገራቸው ነው።

ስጦታ ከሆነ ይህ ስጦታ የሚቀበሉት ስጦታ ነው። ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው። የሚለው ነው። ስጦታ ዋጋ የተከፈለበት፥ ግን ተቀባዩ ያልከፈለበት፤ እንዲቀበሉት የተገባ ግን ግዴታ የሌለበት የፈቃድ ነገር ነው።

ይህ ነው መቀበል። መቀበል መውሰድና የራስ ማድረግ ነው። ስጦታው ዕቃ ከሆነ ወስዶ መጠቀሚያ ማድረግ ነው። ስጦታው ጌጥ ከሆነ ተቀብሎ ማጌጥ ነው። ስጦታው ጌታ ከሆነ ተቀብሎ ጌታ ማድረግ ነው። ክርስቶስን ጌታ አድርጎ መቀበል ማለት በራስ ላይ ጌታ እንዲሆን መፍቀድ ነው።

ይህ 'የግል አዳኝ' የተባለው ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የለም። ግን መጽሐፍ ቅዱሳዊ አሳብ ነው። የግል ማለት የራስ ማለት ነው። የግል አዳኝ አድርጎ መቀበል ሲባል ተቀባዩ ራሱ በውሳኔው የሚቀበለው መሆኑን መናገሩ ነው። ወላጆቼ ስለ እኔ ጌታን አይቀበሉልኝም። ኦርቶዶክሳውያን ሃይማኖተኞች ስለነበሩ በ40 ቀኔ አስጠምቀውኛል፤ የክርስትና ስም ተሰጥቶኛል፤ ያንን ማድረጋቸው ለኔ ክርስቲያን መሆን አስበው ነው። መልካም ምኞት ነው፤ ያስመሰግናቸዋል። ግን ያ እነርሱ ለኔ ያደረጉት ነገር እኔን አያድነኝም። ፈቃዴ የለበትማ! ይልቅስ ከዚያ በኋላ ቃሉን በማስተማር፥ ክርስቶስን በማሳየት ተግተው ኖሮ ቢሆን መልካም ነበር። ያንንም እንኳ አድርገው እኔ በራሴ ውሳኔ፥ በራሴ ፈቃድ ጌታን ጌታዬ አድርጌ ካልተቀበልኩ አይሆንም።

ምክንያቱም ይህ የጌታና የተከታይ ግንኙነት ነው። በግድ ከሆነ ፈቃድ የለበትም። ተገድጄ ነው የምከተለው። ፈቃድ ደግሞ እግዚአብሔር ማንንም ሳይለይ ለሰው ልጆች ሁሉ የሰጠው ድንቅ ስጦታ ነው። ለዚህ ነው የግል አዳኝ የተባለው። ውሳኔው ማንም ለማንም የማያደርገው የግልና የፈቃድ ውሳኔ ስለሆነ ነው።

አንዴ ከካናዳ ትምህርቴን ጨርሼ እንደተመለስኩ በዲላ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን አንድ እሁድ አገለግል ሳለሁ ከካናዳ የገዛኋትን ቆንጆ ሰዓት አሳየሁና፥ ይህችን ሰዓት የሚወስድ ካለ መጥቶ መውሰድ ይችላል፤ የሚወስድ አለ? ብዬ ጠየቅሁ። ሰው አፍሮ ዝም። ፈልገዋል፤ ግን ምንተፍረት ያዛቸው። ኋላ ትንሽ ልጅ ወደ ፊት መጣና እጁን ዘረጋ፤ በገዛ እጄ አውጥቼ ሰጠሁት። ስጦታ ነው፤ የሚቀበል ካለ ብዬ ጋበዝኩ፤ አንድ መጣ፤ ተቀበለ። እንግዲህ መቀበል ይህ ነው። ተቀብሎ የራስ ማድረግ። የምንቀበለው ጌታ ከሆነ ተቀብሎ የራስ ጌታ ማድረግ ነው። ጌታን ተቀብለሃል? ጌታን ተቀብለሻል? አሁን ጥያቄው ግልጽ ነው።

ሁለተኛው፥ እንግዲህ ጌታን ክርስቶስ ኢየሱስን እንደ ተቀበላችሁት በእርሱ ተመላለሱ። የሚል ቃል ነው፤ ቆላ. 2፥6። ጌታን ስንቀበል የተቀበልነው እንደ ጌጥ ወይም እንደ መብል ሳይሆን እንደ ጌታ ነው። ስለዚህ በኛ ላይ በፈቃዳችን የሆነ ጌትነቱን ነው የተቀበልነው። ባንቀበለውም እርሱ ጌታ ነው። አንድ ቀን ጉልበት ሁሉ ለእርሱ ይንበረከካል፤ መላስ ሁሉ ለአብ ክብር ኢየሱስ ጌታ እንደሆነ ይመሰክራል። ይህ እውነት ነው። ግን ጌትነቱን መቀበል በኛ ላይ ጌታ፥ አለቃ፥ አዛዥ፥ ባለ ሙሉ ሥልጣን፥ ንጉሥ፥ አምላክ እንዲሆን ፈቅደን መቀበላችን ነው።
786 viewsSam Sisay, 08:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 02:43:18
@Elolam_the_Everlasting_God
728 viewsSam Sisay, edited  23:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 02:13:02 @Elolam_the_Everlasting_God
737 viewsSam Sisay, edited  23:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 02:13:01
773 viewsSam Sisay, 23:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-14 08:25:43 ተባረኩበት ይህን መዝሙር እኔ ወድጄዋለሁኝ
@Elolam_the_Everlasting_God
953 viewsSam Sisay, edited  05:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-14 05:07:45 Why God doesn't let us forget our sins

1.We can't testify unless we remember it
2.To not repeat it
3.To Rejoice in the victory over it.

Voddie Baucham
960 viewsSam Sisay, 02:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ