Get Mystery Box with random crypto!

EBS TV NEWS

የቴሌግራም ቻናል አርማ ebs_tv_news — EBS TV NEWS E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ebs_tv_news — EBS TV NEWS
የሰርጥ አድራሻ: @ebs_tv_news
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.53K
የሰርጥ መግለጫ

BREAKING NEWS ABOUT WORLD!!!

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2022-04-12 12:37:51 EBS
7.1K views09:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-07 18:43:24
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር የፈተና ስርቆትን ለመከላከል ፈተና በኦንላይን የማስፈተን ፤ ይህ ባይሆን እንኳን ተማሪዎችን ወደ ማዕከል ዩኒቨርሲቲዎች በማስመጣት ፈተና ለመስጠት እያሰበ ነው።

የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ ለህ/ተ/ም/ቤት በሰጡት ማብራሪያ ባለፈው ዓመት ተጀምሮ የነበረውን የ12ኛ ክፍል ፈተናን በታብሌት ለመስጠት የተጀመረውን ስራ በከፍተኛ ደረጃ እየገፋንበት ነው ብለዋል።

ሂደቱ አሁን ላይ በአቅም ጉዳይ መቆሙን የገለፁት ሚኒስትሩ " ሁሉንም ሂደት ከጨረስን በኃላ ይሄ የሚጠይቀውን ወደ 1 ሚሊዮን ታብሌት ሃገር ውስጥ ለማስገባት ወደ 460 ሚሊዮን ዶላር ይጠይቃል፤ ይሄን ከቻይና መንግስት ጋር በሚደረግ ንግግር በእርዳታ ሊመጣ የሚችልበትን መንገድ በብዙ መንገድ ጠ/ሚኒስትሩም ገብተውበት እየገፋን ነው " ብለዋል።

" እሱ እንኳን ቢያቅተን በዚህ ዓመት የምንችለውን ሁሉ ሞክረን የምንወስደው እርምጃ ግን አንዱ በየትምህርት ቤቶቹ ፈተናን መፈት ትተን የሚያስወጣንን ወጪ አውጥተን ተማሪዎቹን ከየትምህርት ቤታቸው አምጥተን በየዩኒቨርሲቲ ማዕከላት ውስጥ ፈተናዎቹን እንዲወስዱ ማድረግ ነው ፤ ይሄን ነው አንዱ ልንሄድበት እያሰብን ያለነው " ብለዋል።

ሚኒስትሩ በአንድም ይሁን በሌላ መንገድ የፈተና ስርቆት መቆም አለበት ያሉ ሲሆን " ስርቆት መቆም ያለበት ሰነፍ ተማሪን እና ጎበዝ ተማሪን ለመለየት ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ የሞራል መሰረታችንን እየበላው በመሆኑ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።

አክለውም ፤ በቀጣይ አመት የሚጀመረው የመውጫ ፈተና የተገባበት አንድ ተማሪ ከታችን ያለውን አጭበርብሮ አልፎ ቢመጣ ኮሌጅም ከገባ በኃላ እንደገና ፈተና እንደሚጠብቀው አውቆ ቢያንስ ኮሌጅ ከገባ በኃላ በደንብ ተምሮ እንዲያውቅ ነው ብለዋል።

@EBS_TV_NEWS
9.3K views15:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-07 12:45:40 #MoE

መንግስት ከ2013 ዓ/ም ብሄራዊ ፈተና ስርጭት ጋር በተያያዘ ከባድ ፈተናዎች ገጥሞት እንደነበር እና የፀጥታ ኃይሎችም ተሰውተው እንደነበረ ገለፀ።

ይህን የተሰማው ትምህርት ሚኒስቴር የ9ወር የአፈፃፀም ሪፖርቱን ለህ/ተ/ም/ቤት ካቀረበ በኃላ ከምክር ቤቱ ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ በሰጠበት ወቅት ነው።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በሰጠው ማብራሪያ በፈተና ስርጭት ወቅት እጅግ ከባድ የሚባል ፈተና እንደነበር ገልጿል።

" ስርጭት ሲባል ፈተናውን ማድረስ እና የፈተናውን የመልስ ወረቀት መመለስ ጭምር ያካታታል ያሉት " የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ተፈራ ፈይሳ ፥ " በስርጭቱ ሂደት ከዚህ በፊታ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ወደ 3000 የሚጠጉ የፈተና ጣቢያዎች (ንዑስ ወረዳ ድረሥ) ላይ ፈተና የደረሰ ሲሆን ከባለፉት ዓመታት በ3 እጥፍ ያደገ ነው " ብለዋል።

" ፈተና መፈተን እራሱ ፈተና ነው የሚያስብል ነገር ያጋጠመን ስርጭት ላይ ነው " ያሉት ም/ ዋና ዳይሬክተሩ ፥ " በብዙ ቦታዎች ላይ የክልል መንግስታት ፣ የክልል የፀጥታ ኃይሎች ዋጋ እየከፈሉ እየተሰው ያደረሱበት ቦታ አለ። " ብለዋል።

የፌዴራል ፖሊስ አባላትም የተሰውቡት ሁኔታ መኖሩን ገልፀዋል።

" አንድ፣ ሁለት ፈተና ጣቢያዎች ላይ ማድረስም አቅቶን እስከመጨረሻ ድረስ ፈተናው ላይ እርምጃ የተወሰደበት ሁኔታ ነው የነበረው። " ሲሉም አስረድተዋል። እርምጃውን ግን በግልፅ አላብራሩም።

ከዚህ ባለፈ የፈተናው የመልስ ወረቀት በሚመለስበት ጊዜ ከባድ ፈተናዎችም እንደነበሩ ተጠቁሟል።

" ከዚህ በፊት የተማሪዎች መልስ የሚመጣው በአውቶብስ ነው ፤ ዘንድሮ ግን የተማሪዎችን የመልስ ወረቀት ለማውጣት የፌዴራል ፖሊሶች የተሰውቡት ሁኔታ ነበር የነበረው " ብለዋል።

የተማሪዎችን የፈተና መልስ ወረቀት ይዘው ለመውጣት በነበረ ሂደት 3 የፌዴራል ፖሊስ መሰዋታቸውን ተገልጿል።

በ3 ጣቢያዎች ላይ ደግሞ አንድ ሳምንት ሙሉ የፈተናውን ወረቀት ማውጣት ያልተቻለበት በኃላ በሀገር ሽማግሌ የወጣትበት ሁኔታ ነበር ተብሏል።

ምክትል ዋና ዳይሬክተር ተፈራ ፈይሳ ፥ " ስርጭቱ ከባድ ፈተና ነበር ፤ በፈተና ክዘና ላይ፣ ፈተና በሚሰጥበት ወቅት ያልተፈቀዱ ቁሳቁሶች ይዞ መገኘት ፣ ለሰው መፈተን ፣ ፈታኞችን Abuse የማድረግ በጣም ብዙ ቦታዎች ችግሮች ነበሩ። ይህ ችግር አንድ ክልል ብቻ ተብሎ የሚወሰድ ሳይሆን ሁሉም አካባቢ ነበር " ብለዋል።

@EBS_TV_NEWS
8.0K views09:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-01 21:03:19
የረመዳን ፆም ነገ ይጀምራል።

1443ኛው የረመዳን ፆም ነገ መጋቢት 24  ይጀምራል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ ቤት ጨረቃ ዛሬ ማምሻውን በመታየቷ ፆሙ ነገ ቅዳሜ እንደሚጀምር አረጋግጧል።

@EBS_TV_NEWS
8.9K views18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-29 08:52:51
" ወያኔም አልቻለም፤ ብልፅግናም አልቻለም " - አቶ ጃዋር መሀመድ

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሀመድ ከወራት በፊት ከእስር ከተፈቱ በኃላ በአደባባይ ንግግር ሲየደርጉ/ ሃሳባቸውን ሲገልፁ/ለሚዲያ ቃላቸውን ሲሰጡ አልተስተዋለም።

ባለፉት ቀናት በነበረው የፓርቲያቸው ጉባኤ ላይ ግን ንግግር አድርገዋል።

አቶ ጃዋር በንግግራቸው ሊበታትኗቸው የፈለጉ ኃይሎች ሁሉ ሊሳካላቸው እንዳልቻለ ገልፀዋል።

አቶ ጃዋር መሀመድ " ' ይሄን ካላደረጋችሁ እናፈርሳችኋለን " ይሄን ወያኔም አልቻለም፣ ብልፅግናም አልቻለም። ሊበታትኑን በፍፁም አይችሉም። ኦሮሞን በፍጹም ማስፈራራት አይቻልም በፍጹም " ብለዋል።

"እኔ በራሴ ከኦፌኮ ከወጣክ ይሄን እናደርግልሃለን ፣ ይሄንን ካላደረክ እንደዚህ አናደርግም ብለውኛል " ያሉት አቶ ጃዋር " ሞተን እንገኛለን እንጂ ካመንበት ነገር ወደኋላ አንመለስም " ሲሉ ተደምጠዋል።

አክለው፥ " ብልፅግና ከግማሽ በላይ ኦነግን ወስዶት እንኳን ኦነግን ማፍረስ አልቻለም። ኦነግ ፈርሷል? አልፈረሰም " ሲሉ ገልፀዋል።

አቶ ጃዋር፥ " ከቦረና፣ ከጉጂ የሚነሳውን ቅሬታ እንሰማለን፣ እንመካከራለን፣ እናስተካክላለን " ያሉ ሲሆን " እኔ ያልኩትን ካልወሰዳችሁ አርሲን ከዚህ አወጣለሁ፣ ሸዋን አወጣለሁ፣ ወለጋን ከዚህ አወጣለሁ ካልክ አንተ ነህ የምትወጣው እንጂ ጉጂም አርሲም አይወጡም " ሲሉ ተናግረዋል።

"እኔ OMN በነበርኩበት ሰዓት እንደዚህ አይነት ሙከራዎች ነበሩ " ያሉት አቶ ጃዋር " አንደዚህ ካላደረክ ከሀረርጌ የሚመጣውን ገንዘብ አንቆርጥብሃለን ከወለጋ የሚመጣውን ገንዘብ እንቆርጥብሃለን...ከቆረጣችሁ ትቆርጣላችሁ እንጂ የኦሮሞ አንድነት አይቆረጥም። ከተበታተንን እንበታተናለን እንጂ ወደኋላ አንመለስም" ብለዋል።

@EBS_TV_NEWS
10.3K views05:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ