Get Mystery Box with random crypto!

EBC(Ethiopian Brodcasting Corboration(EBC)

የቴሌግራም ቻናል አርማ ebc_news_zena — EBC(Ethiopian Brodcasting Corboration(EBC) E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ebc_news_zena — EBC(Ethiopian Brodcasting Corboration(EBC)
የሰርጥ አድራሻ: @ebc_news_zena
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.01K

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-09-18 09:41:29
#EthiopiaCheck Fact Check

በ4ኛ ክፍል የሂሳብ መፅሃፍ ላይ አለ ተብሎ የተሰራጨው መረጃ በትክክልም ቀደም ብሎ በትምህርት ቢሮ በኩል ለትምህርት ቤቶች የተሰራጨው ሶፍት ኮፒ ላይ ይገኛል።

ባለፉት ጥቂት ቀናት በ4ኛ ክፍል የሂሳብ መፅሃፍ ላይ "የግዕዝ ቁጥሮች ምልክቶች በቀጥታ ከግሪክ ፊደል ቁጥሮች የተወሰዱ ናቸው" የሚል መረጃ እንዳለ የሚገልፁ መረጃዎች በስፋት ማህበራዊ ሚድያ ላይ ሲሰራጩ ነበር። ይህን መረጃም በርካታ ተከታይ ያላቸውን ገፆች ጨምሮ በርካታ ግለሰቦች ሲያጋሩት ነበር።

ይህን ተከትሎ ዛሬ ማምሻውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ "በአንዳንድ አካላት በ4ኛ ክፍል የሂሳብ መፅሐፍ ላይ አለ ተብሎ እየተሰራጨ ያለው ፅሁፍ በመሐሃፉ ላይ የማይገኝና የተሳሳተ ነዉ" የሚል መረጃ በፌስቡክ ገፁ አጋርቷል።

ትምህርት ቢሮው አክሎም "ዛሬ ይፋ በተደረገውና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት የ4ኛ ክፍል የሂሳብ መጻሕፍት ገፅ 18 ላይ የግእዝ ቁጥርን አስመልክቶ ወጥቷል ተብሎ የተገለፀው ሃሳብ በመፅሐፍ ውስጥ የማይገኝ ሆነ ተብሎ የሃሰት መረጃ በማሰራጨት ውዥንብር ሊፈጥሩ በሚፈልጉ አካላት የተፈበረከ ነዉ" ያለ ሲሆን ይህም በመንግስት ሚድያዎች እና በበርካታ ሚድያዎች ተዘግቧል።

በዚህ ዙርያ ኢትዮጵያ ቼክ ማጣራት አርጓል።

ኢትዮጵያ ቼክ በመጀመርያ ያናገራቸው በኮልፌ ቀራንዮ በሚገኝ አንድ ትምህርት ቤት የሚያስተምሩ መምህር "የግዕዝ ቁጥሮች ምልክቶች በቀጥታ ከግሪክ ፊደል ቁጥሮች የተወሰዱ ናቸው የሚለው መረጃ የአመቱ መጀመርያ ላይ ከትምህርት ቢሮ በደረሰን የሶፍት ኮፒ PDF ላይ ይገኛል። የመፅሀፍ ህትመት በወቅቱ ስላልተጠናቀቀ እሱን ተጠቀሙ ተብሎ ነበር የተሰጠን" ብለዋል። መምህሩ ለማስረጃ እንዲሆን ይህንን ፋይል ለኢትዮጵያ ቼክ አሳይተዋል፣ እኛም መረጃው እንዳለ አረጋግጠናል።

ኢትዮጵያ ቼክ በመቀጠል ያናገራቸው ወላጅም ይህ ከላይ ስለ ግዕዝ የተጠቀሰው መረጃ በ PDF እንደደረሳቸው አረጋግጠዋል። "ስለዚህ ዛሬ ምሽት ለትምህርት ቢሮው እንደተባለው የሀሰት ነው ሳይሆን ስህተቱን አስተካክለናል መሆን ነበረበት" ብለው አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። እርሳቸውም ይህንን ልጃቸው ሲማርበት የነበረውን እና ከትምህርት ቤቱ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ያገኙትን የ PDF ፋይል ለኢትዮጵያ ቼክ አሳይተዋል።

ስለዚህ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ማምሻውን "የግዕዝ ቁጥሮች ምልክቶች በቀጥታ ከግሪክ ፊደል ቁጥሮች የተወሰዱ ናቸው በሚል የተሰራጨው መረጃ የሀሰት ነው" ብሎ ያወጣው መግለጫ በራሱ የተሳሳተ ነው፣ ምክንያቱም አዲስ የታተመው እና ዛሬ ርክክብ የተደረገበት መፅሀፍ ላይ ማስተካከያ ቢደረግም ቀድሞ ለትምህርት ቤቶች የተሰራጨው ሶፍት ኮፒ ላይ መረጃው ሰፍሮ ይገኛል።

በዚህ ዙርያ ማብራርያ ለመጠየቅ ኢትዮጵያ ቼክ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮን የኮሚኒኬሽን ክፍል ለማናገር ቢሞክርም አልተሳካም።

via:- Ethiopia Check
384 views06:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-14 07:11:57 የኪራይ ቤቶችን ዋጋ ለመወሰን የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ በዚህ አመት ይፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል!

ለኪራይ የሚዘጋጁ ቤቶችን ዋጋ ደረጃ ለመወሰን የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ በዚህ አመት ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ ተናገሩ።በተለይ በከተሞች ያለው የመኖሪያ ቤት ከራይ መወደድና የአከራይና ተከራይ ጭቅጭቅ መላ ሊበጅለት እንደሚገባ በርካቶች ያምናሉ።

ለችግሩ እልባት ለመስጠት ተዘጋጅቶ ሚኒስትሮች ምክር ቤት የደረሰው ረቂቅ አዋጅ፥ የኪራይ ውል ጊዜን ከመወሰን ባለፈ ለኪራይ የሚዘጋጁ ቤቶች ሊያሟሏቸው የሚገቧቸውን መሰረተ ልማቶች በግልጽ ያስቀምጣል ብለዋል።በረቂቅ አዋጁ እንደተቀመጠውም አከራዮች የኪራይ ዋጋ መጨመር ሲፈልጉ በምን ያህል ጊዜና ምን ያህል የሚለውም ተለይቷል።ተከራዮችም በኪራይ የወሰዷቸውን ቤቶች በአግባቡ መያዝ እንደሚገባቸውና ሌሎች ግዴታዎቻቸውንም አስፍሯል ነው የተባለው።

ረቂቅ አዋጁ በደላሎች የሚዘወረውን የኪራይ ቤቶች ዋጋና አቅርቦት በማስተካከል አከራይንና ተከራይን ከማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎች ይታደጋልም ተብሎ ታምኖበታል።የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒም ረቂቅ አዋጁ በዚህ አመት ፀድቆ ወደ ስራ ይገባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነው የተናገሩት።

Via FBC
591 views04:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 23:13:56 ነገ ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት በመዲናዋ ይሰጣል

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ነገ ጳጉሜን 4 ነጻ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት በመዲናዋ እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ አስታወቁ።

ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ፥ “የአገልጋይነት ቀን” ን ምክንያት በማድረግ ነው የነጻ ትራንስፖርት አገልግሎት እንደሚሰጥ የገለጹት፡፡

በዚህም አዳዲስ የሚሰማሩ አውቶቡሶችን ጨምሮ ፣ ሸገር የብዙኃን ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅትና አንበሳ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ድረስ በነፃ አገልግሎት እንደሚሰጡ ገልጸዋል፡፡

አክለውም ፥ ጷጉሜን 4 “የአገልጋይነት ቀን” ብለን የሰየምነው ሁሉም ዜጋ የአገልጋይነት ባሕልን በማዳበር ሁለንተናዊ ለውጥ ማምጣት እንድንችል ነው ብለዋል፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ መጪው ዘመን የደስታ፣ የፍስሃ እና የስኬት እንዲሆን ተመኝተዋል፡፡
811 views20:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 21:06:13 የኢንግሊዟ ንግስት ኤልሳቤጥ ሁለተኛ አረፉ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢንግሊዟ ንግስት ኤልሳቤጥ ሁለተኛ አረፉ።

ለ70 ዓመት በንግስትነት ያገለገሉት ንግስት ኤልሳቤጥ በ96 ዓመታቸው ዛሬ አርፍዋል።

በኪንግሃም ቤተመንግስት እረፍታቸውን ማምሻውን ይፋ አድርጓል።

የንግስቲቱ የጤና ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑን ዛሬ መገለፁን ተከትሎ ቤተሰቦቻቸው ተሰባስበው ባሉበት ሁኔታ ነው ያረፉት።
715 views18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 15:47:35
ታላቁ የኅዳሴ ግድብ ፕሮጀክትን ለማጠናቀቅ ተጨማሪ 60 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ ተገለጸ

ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ፕሮጀክትን ለማጠናቀቅ ተጨማሪ 60 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ የፕሮጀክቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ክፍሌ ሆሮ ገለጹ። የታላቁ ኅዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ሲሆን በጉባኤው ላይ ተገኝተው የፕሮጀክቱን አፈፃፀም ያቀረቡት የፕሮጀክቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ክፍሌ ሆሮ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀም 88 በመቶ መድረሱን ጠቅሰው ፕሮጀክቱን ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ተጨማሪ 60 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።

የኅዳሴ ግድብ በሁለት ዩኒት ኃይል ማመንጨት መቻሉ እና የግድቡ 3ኛ ዙር የውሃ ሙሌት የ2014 ወሳኝ ክንውኖች መሆናቸውን አስታውሰዋል።እየታየ ላለው ህዝባዊ ተሳትፎ ምክር ቤቱ ጉልህ ድርሻ እንዳለው ገልፀው ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡

ፕሮጀክቱን በ70 ቢሊዮን ብር ለማጠናቀቅ ታቅዶ የተጀመረ ቢሆንም በተለያዩ ምክንያቶች እስከ ሐምሌ 2014 ብቻ የወጣው ገንዘብ 172 ቢሊዮን ብር መድረሱን ማሳወቃቸውን ኢቲቪ ዘግቧል። የታላቁ ኅዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽ/ቤት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍቅርተ ታምር በ2014 ብቻ በተለያዩ ገቢ ማሰባሰቢያዎች 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ከኅብረተሰቡ መሰብሰቡን ጠቅሰዋል።
675 views12:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 19:09:16
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለብጹዕ አቡነ ኤርምያስ እና ለኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ የክብር ዶክትሬት ሊሰጥ ነው
**

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለብጹዕ አቡነ ኤርምያስ እና ለኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ የዓመቱን የክብር ዶክትሬት ሊሰጥ መሆኑን አስታወቀ።

ዩኒቨርሲቲው ለብጹዕ አቡነ ኤርምያስ የክብር ዶክተሬቱን የሚሰጣቸው በሃይማኖት አባትነታቸው የተማሩትን እና ያስተማሩትን በተግባር በመኖራቸው እና ሰውን በሰውነቱ ብቻ በማክበራቸው እንደሆነ ገልጿል።

ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ ደግሞ ኢትዮጵያን ብሎም አፍሪካን በስፖርቱ ዓለም በማስጠራት ጀምራ ለኅብረሰተብ ፍቅር እና አንድነት መጎልበት እየተጋች በመሆኑ የክብር ዶክትሬትቱን ሊሰጣት እንደሆነ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ አስታውቋል።
396 views16:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 16:16:17 ኔቶ ወደ ክሪሚያ ከተጠጋ 3ኛው የዓለም ጦርነት ይጀመራል ስትል ሩሲያ ገለጸች ኔቶ የሰዊድን እና ፊንላንድን የአባልነት ጥያቄ ከተቀበለ ሩሲያ ወደሁለቱ ሀገራት ሚሳኤል ታቆማለች ተብሏል

የቀድሞው የሩሲያ ፕሬዝዳንት ድሚትሪ ኔድሜዴቭ እንዳሉት ኔቶ ወደ ክሪሚያ የሚያደርጋቸው እያንዳንዷ እንቅስቃሴ ሶስተኛውን የዓለም ጦርነት እንደሚያስነሳ ገልጸዋል።

ክሪሚያ የሩሲያ አንድ አካል ናት የሚሉት ኔድሜዴቭ የኔቶ ጦር ወደዚህ አካባቢ ከደረሰ ሶስተኛው የዓለም ጦርነት ተጀመረ ማለት ነው ሲሉም አክለዋል፡፡

አሁን ላይ የሩሲያ ጸጥታ ምክር ቤት ሊቀመንበር የሆኑት ድሚትሪ ኔድሜዴቭ ኔቶ በማድሪድ ስብሰባው የፊንላንድ እና ስዊድንን ጥያቄ ከተቀበለ ሩሲያ በሁለቱ ሀገራት ድንበሮች ላይ ጥብቅ የጸጥታ ስራዎችን ከመስራት ባለፈ ኢስካንዴር ሀይፐር ሶኒክ ሚሳኤሎችን ወደ ሁለቱ ሀገራት ታጠምዳለች ብለዋል፡፡

ሩሲያ በዩክሬን ላይ እየተቀዳጀችው ያለው ወታደራዊ ድል ያሰጋው የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) የጦሩን ቁጥር ለማሳደግ እየሰራ መሆኑ የድርጅቱ ዋና ጸሃፊ ጄንስ ስቶልተንበርግ መናገራቸው ይታወሳል፡፡

ዋና ጸሃፊው በቀጣይ ቀናት በማድሪድ ከሚካሄደው ስብሰባ በፊት ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት “የኔቶን ኃይል እናጠናክረዋለን እንዲሁም የከፍተኛ ዝግጁነት ሀይላችንን ቁጥር ከ 300 ሺህ በላይ እናሳድጋለን" ብለዋል፡፡

ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃልኪዳን ጦር ወይም ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ከሩሲያ ጋር ጦርነት ከጀመረች 124ኛ ቀኑ ላይ የደረሰ ሲሆን በነዚህ ቀናት ውስጥ አያሌ ጉዳቶች ተከስተዋል፡፡

እስካሁን ጦርነቱን ተከትሎ ከ15 ሚሊዮን በላይ ዩክሬናዊያን ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን የዓለም መግብ እና ነዳጅ ዋጋ ከፍተኛ ጭማሪ ሲያሳይ ምዕራባዊያን ሀገራት ደግሞ የዋጋ ጭማሪውን ለመቆጣጠር የተለያዩ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ናቸው፡፡
387 views13:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 16:16:02
349 views13:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-18 13:19:05 አማራ ባንክ ተመርቆ ሥራውን በይፋ ጀመረ


አማራ ባንክ አክሲዮን ማህበር በዛሬው እለት ተመርቆ ሥራውን በይፋ ጀምሯል።

ባንኩ ዛሬ በተለያዩ የክልል ከተሞች እና በአዲስ አበባ ስራውን ሲያስጀምር የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር ዶ/ር ይልቃል ከፋለን ጨምሮ የተለያዩ የፌዴራል እና የክልል የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

አማራ ባንክ ዘመኑ የደረሰበትን የኮር ባንኪንግ ሲስተም በመጠቀም ከ185 ሺህ በላይ ባለአክሲዮኖችን በመያዝ የተመሰረተ ባንክ ነው።

አማራ ባንክ 4.9 ቢሊዮን የተከፈለ እና 6.5 ቢሊዮን ብር የተፈረመ ካፒታል ይዞ ወደ ስራ እንደገባም ለማወቅ ተችሏል።

በዛሬው እለት ከ70 በላይ የባንኩ ቅርንጫፎች ተከፍተው አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል።

ባንኩ የዛሬውን ምርቃቱን በማስመልከት ነፃ የአንበሳ አውቶብስ ትራንስፖርት አገልገሎት አዲስ አበባ እና በዙሪያዋ ባሉት ከተሞች ሁሉ አቅርቧል።

በተጨማሪም በአገሪቱ ዋና ዋና ከተሞች በሚገኙ ሆስፒታሎች በዛሬው እለት ለሚወልዱ እናቶች ለእያንዳንዳቸው በስጦታ በስማቸው የ2 ሺህ ብር አካውንት በባንኩ እንደሚከፈትላቸውም ተገልጿል።
577 views10:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 07:39:36
በሱዳን ዳርፉር ግዛት በተነሳ የጎሳ ግጭት 100 ሰዎች ተገደሉ

➯የተመድ ስደተኞች ኤጀንሲ እና አንድ የጎሳ መሪ እንዳስታወቁት በአንድ ሳምንት ውስጥ በጎሳ ግጭት መነሻነት 100 ሰዎች ተገድለዋል፡፡ ግጭቱ የተነሳው በአረብ እና በአፍሪካ ጎሳዎች መካከል መሆኑን ዋሸንግተን ፖስት ዘግቧል፡፡ 

➯የተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን አስተባባሪ ቶቢ ሃርዋርድ ግጭቱ የተነሳው ኩለቡስ በምትባል የምስራቅ ዳርፉር ግዛት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ እንደ ኮሚሽኑ አስተባባሪ መረጃ ከሆነ የአረብ እና የአፍሪካ ጎሳዎች ግጭቱን የጀመሩት በመሬት ይገባኛል ጥያቄ ነው፡፡

➯አብካር አል ታወም የተባሉ የጎሳ መሪ ሚሊሻዎቹ 20 መንደሮች ያቃጠሉ ሲሆን በዚህም የ 62 ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል ተብሏል፡፡ በዚህ ግጭት የሞቱ ሌሎች ብዙ ሰዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡ 
Alain
607 views04:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ