Get Mystery Box with random crypto!

EBC(Ethiopian Brodcasting Corboration(EBC)

የቴሌግራም ቻናል አርማ ebc_news_zena — EBC(Ethiopian Brodcasting Corboration(EBC) E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ebc_news_zena — EBC(Ethiopian Brodcasting Corboration(EBC)
የሰርጥ አድራሻ: @ebc_news_zena
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.01K

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-02-15 18:31:28 #ሰበር ዜና
በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ በቀደሞ ስምቸው እነ አባ ሳሪዎስ በዛሪው አለት በጽርሐ መንቀር ፓትርያርክ የይቅርታ ደብዳቤ ምስገባታቸው ተወህዶ ሚዲያ ማእከል ዘግበዋል

#ሰላም ለሀገራችን
308 viewsedited  15:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-28 21:38:06 ሳይንቲስት የመሆን ህልም ያላት ተማሪ ገሊላ ውጤቴ ባልረካም ወደ ዩንቨርሲቲ የሚያስገባኝ ስለሆነ አይከፋኝም




ተማሪ ገሊላ አሰፋ ትባላለች፤ ከህጻንነቷ ጀምሮ ሳይንቲስት የመሆን ህልምን ይዛ ትምህርቷን ስትከታተል የነበረችው ገሊላ በአጣዬ ከተማ ተወልዳ ማደጓን ነግራናለች።
“የደረጃ ተማሪ መሆኔ ምኞቴ እንደሚሳካ የእርግጠኝነት ስሜት እንዲሰማኝ ያደርገኛል” የምትለው ተማሪ ገሊላ “በአካባቢያችን በተደጋጋሚ የተከሰቱት ጦርነቶች አስጨናቂ እና ተስፋ አስቆራጭ ነበሩ” ብላለች።
“በተለይ ደግሞ 11ኛ ክፍል ተማሪ እያለች በ2013 ዓ.ም ላይ የተከሰቱት ሁለት ግጭቶች መኖሪያ ቤታችንን ጨምሮ ትምህርት ቤታችን እና ሌሎች ንብረቶቻችን ሲቃጠሉ መግለጽ የሚከብዱ ከባድ የተስፋ መቁረጥ ስሜቶች ተሰምተውኛል ብላናለች፡፡
በነዚህ ግጭቶች ምክንያት ህይወታችንን ለማትረፍ በተደጋጋሚ ለስደት ተዳርገናል የምትለው ተማሪ ገሊላ ሳይንቲስት የመሆን ምኞቴ ቀርቶ ፍላጎቴ በህይወት መኖር ብቻ እንደነበርም ተናግራለች፡።
ከአንድ ዓመት በፊት ህወሓት ወደ ሰሜን ሸዋ ጥቃት በመክፈቱ ምክንያትም እሷ እና ቤተሰቦቿ ለሶስተኛ ጊዜ ወደ ደብረብርሃን መሰደዳቸውን ነግራናለች።
አካባቢው መልሶ ሲረጋጋ ግን ትምህርቷን ለመቀጠል ስትል በአንድ ዘመዷ እና በሸዋሮቢት ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እርዳታ ምክንያት ከ11ኛ ክፍል ሁለተኛ መንፈቀ- ትምህርት ጀምሮ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን እንደወሰደችም ነግራናለች።
ቤተሰቦቼ እና መምህራኖቼ ያደረጉልኝ ድጋፍ በጦርነቱ ምክንያት ያየኋቸውን መጥፎ ሁኔታዎች ሁሉ እንድረሳ አድርጎኛል የምትለው ተማሪ ገሊላ ቤተሰቦቿን እና መምህራንን አመስግናለች።
የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተናን በሰላም በደብረብርሃን ዩንቨርሲቲ ተፈትና 569 ማምጣቷን ጠቅሳለች። “መፈናቀሉ እና ጦርነቶቹ ሁሉ ባይኖሩ ከዚህ የተሻለ ውጤት ላመጣ እችል ነበር፣ ይሁንና ይህ ውጤት ወደ ዩንቨርሲቲ የሚያስገባኝ በመሆኑ አይከፋኝም” ብላለች። ይህ ውጤት ከሰሜን ሸዋ እና አካባቢው ከሴቶች ከፍተኛው ውጤት እንደሆነ ሰምተናል።
ጦርነት የሰውን ልጅ ሲገድል እና ድሃ ሲያደርግ አይቻለሁ ያለችን ተማሪ ገሊላ ለመላው ኢትዮጵያዊያን ሰላምን ተመኝታለች።
በቀጣይ በዩንቨርሲቲ በሚኖራት ጊዜ ሶፍትዌር ኢንጅነሪንግ ማጥናት የመጀመሪያ ፍላጎቷ መሆኑን የነገረችን ተማሪ ገሊላ 12 ዓመት ሙሉ የለፉ የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪዎች ውጤት በዚህ መልኩ መደምደሙ እንደሚያሳዝናትም ጠቁማለች።
Via አል ዓይን
476 viewsedited  18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-28 21:37:57
452 views18:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-26 18:40:00 የ12 ክፍል ውጤት ይፋ ሆነ
አዲስ አበባ ጥር 18 /2015 የ12 ክፍል ውጤት ይፋ መሆኑ የትምህርት ምዘና ፈተናዎች አገልገሎት አስታወቀ
ውጤቱን ዛሬ ከሌሊቱ 5:30 ጀምሮ በዌብሳይት
https://eaes.edu.et/
ወይም 6284 register number በመላክ እና በቴሌግራም
@EAESbot
ላይ ማወቅ ትችላላችሁ
738 viewsedited  15:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 20:31:57 ሊዮኔል ሜሲ በኢትዮጵያ ዐይነ-ስውራንን ለመደገፍ ከኦርካም ቴክኖሎጂ ጋር በትብብር ለመሥራት ተስማማ
****

አርጀንቲናዊው የእግር ኳስ ኮከብ ተጫዋች ሊዮኔል ሜሲ በኢትዮጵያ የሚገኙ ዐይነ-ስውራን ዜጎችን ለመደገፍ ከኦርካም ቴክኖሎጂ ጋር በትብብር ለመሥራት ተስማምቷል።

ተጫዋቹ በኢትዮጵያ የሚገኙ ዐይነ ስውራን ዜጎችን ለመደገፍ በመስማማቱም ክብር እንደሚሰማው በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ አስታውቋል።

የኦርካም ቴክኖሎጂ በሺህዎች የሚቆጠሩ ዐይነ ስውራንን ሕይወት እያሻሻለ ያለው ሊዮኔል ሜሲ፣ ቴክኖሎጂው ዐይነ ስውራን ሕልሞቻቸውን እንዲያሳኩ ይረዳቸዋል ብሏል።

የቀዳማዊ እመቤት ጽ/ቤት በቅርቡ የዘመኑ የቴክኖሎጂ ውጤት የሆነ “OrCam MyEye” የተሰኘ ዐይነ ስውራንን የሚያግዝ መነፅር ለሁለት ሺህ ዐይነ ስውራን አስረክቧል።

መሣሪያው አማርኛም ሆነ እንግሊዝኛ የሚያነብብ ሲሆን የገንዘብ ኖቶችን ለይቶ ለተጠቃሚው ያስረዳል፤ የቀለም ዓይነትን ይለያል እንዲሁም ከፊት ለፊት ምን እንዳለ እና ማን እንደመጣ መዝግቦ በመያዝ መረጃ ይሰጣል።
1.3K views17:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-11 11:15:24
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

በፊልም ሥራዎቹ ብዙዎች ዘንድ ተወዳጅነትን እና ዝናን ያተረፈው አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

ወጣቱ የፊልም ባለሙያ ባደረበት ሕመም ለሳምንታት በሕክምና ሲረዳ ቢቆይም ሕይወቱ ሊያልፍ ችሏል።

አርባ ያህል ፊልሞች ላይ የተወነው አርቲስት ታሪኩ በሕመም ምክንያት ሕይወቱ ማለፉን ኢፕድ ከአርቲስቱ የቅርብ ሰዎች ማረጋገጡን ዘግቧል።
89 views08:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-30 14:10:59 ክርስትያኖ ሮናልዶ የሳውዲውን ክለብ ለመቀላቀል ከስምምነት ላይ ደረሰ

ኅዳር 21/2015 (ዋልታ) ክርስትያኖ ሮናልዶ የሳውዲውን ክለብ አልናስርን ለመቀላቀል ከስምምነት ላይ መድረሱ ተዘገበ፡፡

የስፔኑ ማርካ እንዳስነበበው የአምስት ጊዜ የባሎንዶር ኮከቡ ክርስትያኖ ሮናልዶ ለሳውዲው ክለብ የሁለት ዓመት ከስድስት ወር ኮንትራት ለመፈረም ተስማምቷል፡፡

እንደመረጃው ከሆነ 137 ሚሊየን ዩሮ በዓመት የሚከፈለው ሲሆን በእግር ኳስ ተጨዋቾች ታሪክ ውዱ ክፍያ እንደሚሆንም ተነግሯል፡፡

የ37 ዓመቱ ተጨዋች የዓለም ዋንጫ ውድድሩ ሲጠናጠቀቅ ውሉን እንደሚፈፅም እና በይፋ የክለቡ ተጨዋች እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡

እስከ 40 ዓመቱ መጫወት እንደሚፈልግ የሚናገረው ሮናልዶ ከፒርስ ሞርጋን ጋር ካደረገው አወዛጋቢ ቃለመጠይቅ በኋላ ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር በስምምነት መለያየቱ ይታወሳል፡፡
410 views11:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-06 21:36:16 ተወዳጁ ድምጻዊ የክብር ዶክተር አሊ ቢራ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
*****

ድምጻዊ አሊ ቢራ በአዳማ አጠቃላይ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ የቆየ ሲሆን ዛሬ ምሽት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ከኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

በኢትዮጵያ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ አሁን ለደረሰበት ደረጃ ባለውለታ ከሆኑት አንጋፋ ከያኒያን መካከል ዓሊ ቢራ በቀዳሚነት ከሚቀመጡት ይመደባል። በበርካታ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጭምር በተጫወታቸው ሙዚቃዎቹ የሚታወቀው አርቲስት ዓሊ ቢራ በተለይ በአፋን ኦሮሞ በተጫወታቸው በርካታ ሙዚቃዎቹ ዘመን ተሻጋሪ ተፅዕኖ ፈጣሪ መሆን በመቻሉ የቋንቋው ምልክት እስከመሆን ደርሷል ይሉታል በርካቶች።

በግንቦት 1940 ዓ.ም በድሬዳዋ የተወለደው አርቲስት ዓሊ ቢራ፣ በህጻንነቱ የተለያዩ የአገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ ሙዚቃዎችን እያደመጠ ማደጉን እና ለትምህርት ቤት ጓደኞቹ እና ለቤተሰቦቹ በማንጎራጎር የሙዚቃ ህይወቱን መጀመሩን በተለያያ ጊዜ ከሰጣቸው ቃለ ምልልሶች መረዳት ይቻላል።

የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በድሬዳዋ ከተማ ፣ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በአዲስ አበባ ካቴድራል ትምህርት ቤት ተከታትሏል። አሜሪካ ሀገር በሚገኘው የሳንታ ሞኒካ ኮሌጅም የሙዚቃ ትምህርቱን ተምሯል።

አርቲስት ዓሊ ቢራ በ1954 ዓ.ም የኦሮሞን ሙዚቃ ለማስተዋወቅ ዓላማ ያደረገ የባህላዊ ሙዚቃ ቡድን “አፍረን ቀሎ”ን በመቀላቀል ነበር የሙዚቃ ስራውን የጀመረው። በቡድኑ ውስጥ ሌላ ዓሊ የተባለ ልጅ በመኖሩ ሁለቱን ለመለየት መጀመሪያ ከሚያዜመው "ቢራ ዳ ባሬ" ዘፈን ተወስዶ "ዓሊ ቢራ" የሚለው ሰም ተሰጠው። ዓሊ ስለ አፍረንቀሎ የሙዚቃ ባንድ ወቅት ሲናገር “ እኔ ከመስራቾቹ አንዱ ነኝ እንጂ መስራች አይደለሁም፤በእድሜ ከነሱ አነስ እላለሁ።

አፍረንቀሎን ከመሰረቱት ውስጥ ዓሊ ሸቦ የሚባል እሱም ከሃረማያ ዩኒቨርሰቲ የክብር ዶክትሬት ተሰጥቶታል። እኔ ከነሱ ጋር ተቀላቅዬ አፍረንቀሎን መሰረትኩ” ብሏል።

አርቲስት ዓሊ ቢራ በክብር ዘበኛ ኦርኬስትራ ተቀጥሮ ለሦስት ዓመታት ሰርቷል፤ እንዲሁም ‘አይቤክስ’ ባንድን በመቀላቀል ለስምንት ዓመታት የሙዚቃ ስራዎቹን በዲ አፍሪካ ሲያቀርብ ቆይቷል። ስለ ፍቅር፣ አካባቢ እና ፖለቲካ በጥቅሉ ከ267 በላይ ሙዚቃዎችን ተጫውቷል። ዓሊ ጊታር፣ ፒያኖ፣ ኡድ እና ሌሎች የሙዚቃ መሳሪያዎችን ይጫወታል። ከአርባ በላይ ሀገራት (በሁሉም አህጉራት) እጅግ በርካታ በሆኑ መድረኮች የሙዚቃ ስራዎችን ተጫውቷል።

ዓሊ ቢራ “Birra Children’s Education Fund” የተባለ ምግባረ ሰናይ ድርጅት ከባለቤቱ ጋር አቋቁመው ለሕፃናት ትምህርት ድጋፍ በመስጠት ላይ ይገኛሉ።

አርቲስት ዓሊ ከኦሮምኛ በተጨማሪ፣ በሶማሊኛ፣ በአፋርኛ፡ በሐረሪ፣ በአማርኛ እና በአረብኛ ቋንቋዎች በርካታ ዘፈኖችን መጫወት ችሏል።አንድ ሰሞን ስለ ራሱ የተናገረው አርቲስት ዓሊ ቢራ "ራሴን የምፈርጀው የሀቅ ታጋይ ነኝ ብዬ ነው" ብሏል።

የ75 ዓመቱ አርቲስት ዓሊ ቢራ ለኢትዮጵያ ህዝቦች አብሮነትና ማህበራዊ ትስስር ከፍ ያለ አስተዋጽኦ አበርክቷል።በሙዚቃዎቹ ዘመን ተሻጋሪ መልዕክቶችን በማስተላለፍ መልካም ትውልድ እንዲቀረጽ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል።የተለያዩ ፈተናዎችን ተሻግሮ በከፍተኛ ጽናትና ብቃት ለረጅም ዓመታት በኪነ ጥበቡ ውስጥ ያሳለፈ መሆኑ ደግሞ አሁን ላለው ትውልድ ታላቅ ተምሳሌት ያደርገዋል።

አርቲስቱ በተስረቅራቂ ድምፁ ዘመን ተሸጋሪ ጥዑም ሙዚቃን ከመጫወት በተጨማሪ የግጥምና ዜማ ደራሲም ነው። አርቲስት ዓሊ ቢራ ባለፉት 50 ዓመታት በኦሮሞ የሙዚቃ ስራዎች ውስጥ እንቁ ሆኖ ቆይቷል።

ለቋንቋው የሙዚቃ እድገትም ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።

በኪነጥበቡ ዘርፍ ላበረከተው አስተዋፅኦ የክብር ዶክተሬት ማዕረግ የተሰጠው አርቲስት ዓሊ ቢራ፣ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገር ተቋማት የተለያዩ እውቅናዎችን እና ሽልማቶችን አግኝቷል።

• በአጠቃላይ ከሃምሳ በላይ ታላላቅ ሽልማቶች ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ ተቋማት ወስዷል።
• ከድሬዳዋ እና ከጅማ ዩኒቨርስቲዎች የክብር ዶክትሬት ተበርክቶለታል።
• በድሬደዋ ከተማ ፓርክ እንዲሁም በአዳማ መንገድ በስሙ ተስይሟል።
• የኦሮሚያ ክልል በሙዚቃው ዘርፍ ላበረከተው አስተዋጽኦ ልዩ የኒሻን ሽልማት አበርክቶለታል።
• የመጀመሪያው የኢሬቻ የሰላም ሽልማት ተሸላሚም ነው።
• የመጀመሪያው የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ የኪነጥበብ ሽልማት የህይወት ዘመን ተሸላሚም ሆኗል።
• የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ከፍተኛ ሽልማት
• በካናዳ ቶሮንቶ የአፍሪካን የምንግዜም አንጋፋ ሙዚቀኛ ሽልማት እና
• የኦዳ አዋርድ የሕይወት ዘመን ተሸላሚ ነው።
231 views18:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-02 19:54:15 ሰበር

የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት ዘላቂ ግጭት የማቆም ስምምነት ተፈራረሙ

ጥቅምት 23/2015 (ዋልታ) የኢፌዲሪ መንግስት እና ሕወሓት በደቡብ አፍሪካ በሚካሄደው ድርድር ከስምምነት ላይ ደረሱ፡፡

በደቡብ አፍሪካ ለ10 ቀናት በደቡብ አፍሪካዋ ፕሪቶሪያ ከተማ የሰላም ንግግር ሲያካሄዱ የሰነበቱት የፌደራል መንግሥቱ እና ህወሓት በዘላቂነት ግጭት ለማቆም ከስምምነት ደርሰዋል።

ይህ የተገለጸው ሁለቱ ኃይሎች በደቡብ አፍሪካ ሲያደርጉ የነበረው የሰላም ንግግር ውጤት በተገለጸበት ወቅት ነው።
ጦርነቱን በሰላም ለመቋጨት የሚደረገውን ድርድር ተከትሎ ሕወሓት ትጥቅ ለመፍታት ተስማምቷል፡፡

በድርድሩ ትህነግ ጦር ለመፍታት፣ አባላቱ ወደ ካምፕ እንዲገቡ፣ በሂደትም የፌደራል መንግስት በሚያውቀው የፀጥታ መዋቅር ስር እንዲገቡ እንዲደረግ ተስማምቷል፡፡

ከዚህ ቀደም በትግራይ ክልል በህገ-ወጥ መንገድ የተካሄደው ምርጫ ተቀባይነት እንደሌለው፣ አሁን ላይ በህገ ወጥ መንገድ ክልሉን እየመራሁ ነው የሚለው ህወሓት አስተዳደሩ እንዲፈርስ እና በምትኩም ሌላ ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም ከስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡

በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ከተመሰረተ በኋላ መንግስት የሚያውቀው ህጋዊ ምርጫ ይካሄዳል፡፡

ትህነግ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም የሚጎዳ የትኛውንም ተግባር ላይ ላለመሳተፍ የተስማማ ሲሆን ይህም የፌደራል መንግስት ስልጣን የሆነው የውጭ ግንኙነትን አለማድረግን ይጨምራል፡፡

መንግስት በትግራይ ክልል የሚገኙ የፌደራል ተቋማትን በሙሉ አየር መንገዶችን ጨምሮ በመቆጣጠር ማስተዳደር እንዲችል ከስምምነት ተደርሷል፡፡
220 views16:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ