Get Mystery Box with random crypto!

ዲያቆን ሄኖክ ሃይሌ Henok Haile

የቴሌግራም ቻናል አርማ diyakonhenokhaile — ዲያቆን ሄኖክ ሃይሌ Henok Haile
የቴሌግራም ቻናል አርማ diyakonhenokhaile — ዲያቆን ሄኖክ ሃይሌ Henok Haile
የሰርጥ አድራሻ: @diyakonhenokhaile
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.31K
የሰርጥ መግለጫ

Henok Haile
Author
https://l.instagram.com/?u=https://youtu.be/5R-pjvDeX4g&e=ATO0XVudOWg66a06guzC75IANTb2l2egLzkeGbr9wETcTg3FHuOHdrmPR4b2eOQb-H_knzwrLS0r1E7ACWyHbw&s=1

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-10-10 19:46:09 + የጴጥሮስ ጥላ +

አንድ አባት በተመስጦ ሆኖ እየጸለየ ነው:: ድንገት ሌላ አባት መጣና በቁጣ ጸሎቱን አስቆመው::
"አንተ ደፋር እንዴት ወደ ፀሐይ መውጫ (ምሥራቅ) ሳትዞር ትጸልያለህ?" አለው
ያ አባት መለሰ
"አንተ ፀሐይህን ፈልግ:: የኔ ፀሐይ ክርስቶስ መውጫ መግቢያ የለውም"::

በእውነትም ክርስቶስ በነቢዩ ሚልክያስ እንደተነገረለት ለሚፈሩት የሚወጣ እውነተኛ ፀሐይ ነው:: ወደ ፀሐይ ዞረን ስንጸልይም አባ ጊዮርጊስ እንዳለው ወደ ፀሐይ ሳይሆን ፀሐይን ወደሚያወጣው እንጸልያለን:: (አኮ ዘንጼሊ በቅድመ ፀሐይ አላ ለዘያሠርቆ ለፀሐይ")

ክርስቶስ ፀሐይ ነው:: አናት የሚበሳ ኃይል የሚያደክም ለሕመም የሚዳርግ ሳይሆን ኃይል ፈውስ የሚሠጥ ፀሐይ ነው::

@diyakonhenokhaile
ቅዱስ ጴጥሮስ በሐዋርያት ሥራ እንደተጻፈልን ሕሙማንን በጥላው ይፈውስ ነበር:: በዚህ ምክንያት በሽተኞችን በሚያልፍበት መንገድ አሰልፈው ጥላውን ብቻ እንዲያሳርፍ ያደርጉ ነበር::
የሰው ጥላ ጥሩ አይደለም ለበሽታ ይዳርጋል በሚል ማኅበረሰብ ውስጥ ሆነን ይህን ስንሰማ ምን እንል ይሆን? የጴጥሮስ ጥላ ግን ይፈውስ ነበር::

የጴጥሮስ ጥላ ምን የተለየ ነገር አለው? ምንም የለውም:: እንዲያውም በአሣ አጥማጅነቱ ጊዜ ከወንድሞቹ ጋር በቀን ዓሣ ሲያጠምዱ ጥላቸው በውኃው ላይ አርፎ አሣ እንዳያሸሽባቸው በሌሊት ማጥመድ ይመርጡ ነበር:: አሁን ግን ዓሣ የሚያሸሸው የጴጥሮስ ጥላ መድኃኒት ሆኖ ከዓሣ አልፎ ምእመናን ማጥመድ ጀመረ::

@diyakonhenokhaile
የጴጥሮስ ጥላ ከቀድሞው ጥላው በምንም አይለይም::
ያንን ሁሉ በሽተኛ መፈወስ የቻለው ጥላው ተቀይሮ ሳይሆን ያረፈበት ፀሐይ ተቀይሮ ነው:: ፈዋሹ ጥላ የተፈጠረው እውነተኛው ፀሐይ ክርስቶስ በጴጥሮስ ላይ ስላረፈ ነው:: እውነተኛው ፀሐይ በእኛ ላይ ሲያርፍ እኛ ተፈውሰን ሌላ እንፈውሳለን:: የእርሱ ብርሃንና ሙቀት ሲያርፍብህ የኃጢአት ቆፈን ቀስ በቀስ ይለቅህና ትፍታታለህ:: ከዚያም ሐሙስ ማታ ብርድ ፈርተህ እሳት ለመሞቅ ሦስቴ የካድከውን ፀሐይ ስትሞቀው ሦስት ሺህ ሰው ፊት ትመሰክርለታለህ:: እሱን ሞቀህ በጥላህ ደግሞ ለሌሎች ትተርፋለህ::
ክርስቶስ እንዴት ያለ ፀሐይ ነው? ፀሐይን ያጨለመ ፀሐይ! ፈረቃ የማያውቅ ፀሐይ! ፀሐይ ራስዋ የምትሞቀው ፀሐይ እርሱ ክርስቶስ ነው::

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
#Share
@diyakonhenokhaile
#Share
@diyakonhenokhaile
12.5K viewsᴍɪᴄᴋʏ, edited  16:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-10 19:45:44
#Share
@diyakonhenokhaile
9.3K viewsᴍɪᴄᴋʏ, edited  16:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-09 12:15:14 ጌታችን በስምዖን ቤት እያለ 300 ዲናር የሚያወጣ ሽቱ ይዛ ለመጣችውና ጠርሙሱን ሰብራ ላፈሰሰችው ባለ ሽቱዋ ማርያም ሲመሰክር

"መልካም ሥራ ሠርታልኛለችና ሴቲቱን ለምን ታደክሙአታላችሁ? ...እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል" ብሎ ነበር:: (ማቴ 26:10-11)

ለክርስቶስ በአንዲት ምሽት መልካም ሥራ የሠራችን ሴት ሊንቁ የሞከሩትን ሰዎች ክርስቶስ ከገሠፃቸው ሕይወትዋን ሙሉ በመልካም ሥራ የደከመችዋን ቅድስት አርሴማን [St. Hripsime] የማያከብር ምንኛ ተግሣፅ ይገባው ይሆን?

ባለ ሽቱዋ ማርያም በዝሙት ስትሠቃይ ኖራ በመጨረሻ ዕንባዋን ከሽቱ ቀላቅላ ከጌታ እግር ሥር የወደቀች ናት:: ቅድስት አርሴማ ግን በድንግልና ለመኖር ብላ በነገሥታትና ገዢዎች ብዙ መከራን የተቀበለች ውድ ሽቱን ንቃ በክርስቶስ በፍቅሩ መዓዛ ያጌጠች ነበረች::
ክርስቶስ ባለ ሽቱዋ ማርያም ያደረገችው ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን በዓለም ሁሉ ይነገራል አለ::
ባለ ሽቱዋ ማርያም ስለ ክርስቶስ ፍቅር የሰበረችው ጠርሙስ ነው ያፈሰሰችው ሽቱ ነው::
ቅድስት አርሴማ ግን የሰበረችው አንገትዋን ነው:: ያፈሰሰችው ደሟን ነው:: ስለዚህ በዓለም ሁሉ ስለ እርስዋ ይነገራል:: አርሴማ አርሴማ አርሴማ

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
#Share
@diyakon_henok_haile

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ! በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)
#Share
@diyakonhenokhaile
9.9K viewsᴍɪᴄᴋʏ, edited  09:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-09 12:14:38
8.3K viewsᴍɪᴄᴋʏ, 09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-06 08:48:26 ለማንም እንዳትናገር!
መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ የአንድን ዲዳና ደንቆሮ አንደበት ‘ተከፈት’ ብሎ በአምላካዊ ኃይሉ ከፈተ፡፡ ይህንን ካደረገ በኋላ ግን ‘ለማንም አትንገሩ ብሎ አዘዛቸው እነርሱ ግን ባዘዛቸውም መጠን ይልቅ እጅግ አወሩት’’ (ማር 7:36)
‘አትንገር ብዬ ብነግረው አትንገር ብሎ ነገረው’ ይሏል እንግዲህ ይኼንን ነው፡፡

የመልካም ሰውነት አንዱ መለኪያ ምሥጢር ጠባቂነት ነው፡፡ እውነተኛ ባልንጀርነትም ምሥጢርን መስማት ሳይሆን የሰሙትን ጠብቆ መያዝ ነው፡፡ ይህ የሚሆንላቸው ሰዎች በማኅበረሰቡ ዘንድ ይከበራሉ በፈጣሪም ዘንድ ዋጋቸው ከፍ ያለ ነው፡፡ በምድርም ቢሆን ለከፍተኛ ሓላፊነት የሚታጩትና ከፍ ያለ ክብር የሚሰጣቸው ሰዎች በማሰቃያ ሥፍራ ሳይቀር እየተንገላቱ ምሥጢር የሚጠብቁ ሰዎች ናቸው፡፡

አንዳንድ ሰው ግን የሰማውን ምሥጢር ለሌላ ሰው ለማዝረክረክ ማሰቃያ አያስፈልገውም፡፡ አትንገር የተባለውን እስኪናገር ድረስ ሆዱን ይቆርጠዋል፡፡ እግሩን እሾህ የወጋው ሰው እስኪነቀልለት ድረስ እንደሚንገበገብ ይህ ዓይነት ዓመል የተጠናወተውም ሰው ምሥጢሩን ለሌላ ሰው እስኪያሰማ ድረስ ይንቆራጠጣል፡፡ ‘ቀሊል ሰው’ ይለዋል ጠቢቡ ሲራክ
ምሥጢር ጠባቂነት ለወታደር የሞት ሽረት ጉዳይ ነው፡፡ በኮድ ማውራት ግድ የሆነውም ለዚህ ነው፡፡ ለሐኪም የሙያ ቃል ኪዳን ነው፡፡ ለጠበቃ የጥብuቅና ፈቃድን ላለማጣት የሚጠበቅ ሕግ ነው፡፡ ለካህናት የንስሓ ልጆችን የመጠበቅ ሰማያዊ ቃልኪዳን ነው፡፡ ዓለም የምትናወጸው በዚህ መርሕ ኖረው ምሥጢር በማይጠብቁ ሰዎች ነው ማለት ይቀልላል፡፡

#Share
@diyakon_henok_haile

2. ጌታችን ያደረገው ፈውስ ቢሆንም ማስታወቂያ ሥሩልኝ ግን አላለም:: እንዳይናገሩ አዝዛቸው:: ከዚህም የምንማረው ብዙ ነው:: የሰውን መልካም ነገርም ቢሆን ምሥጢር መጠበቅ የግድ ነው፡፡ ለዚያ ሰው ሥራ እንቅፋት ላለመሆን ሲባል ዝም ማለት እርዳታ ነው:: የሰውን ኃጢአትና ነውር መደበቅ ደግሞ "ከባቴ አበሳ" (በደልን ሸፋኝ) አስብሎ በፈጣሪ ክብር ያስገኛል::

ሙሴን ወደ ስደት የዳረገው ምሥጢር መቋጠር የማይችል እስራኤላዊ ነበር፡፡ ሙሴ ለእርሱ አግዞ ግብጻዊውን ገድሎ ቢቀብርና ነጻ ቢያወጣው ‘አመስጋኝ አማሳኝ’ /አመስጋኝ አጥፊ/ እንዲሉ ሔዶ ወሬውን ነዛው፡፡ ወሬው በአጭር ጊዜ ተዳርሶ እስከ ፈር ኦን እልፍኝ ደረሰ፡፡ በአንድ መቋጠር በማይችል ወንፊት ሰው ምክኛት ሙሴ ከቤተ መንግሥት ወጥቶ የዱር ስደተኛ ሆነ፡፡

ጌታችን በዚህች ምድር ሲመላለስ ተአምራቱን እንዳይናገሩ ያደርግ የነበረው ተአምራቱ ቢነገሩ የሚጎዱ ሆነው አልነበረም፡፡ በአንድ ወገን መከራ ከፊቱ አስቀምጦ ክብርን መፈላለግ እንደማይገባ ሲያስተምረን ሲሆን በሌላ በኩል ግን ከጊዜው በፊት መከራን ሊያደርሱበት እንዳይነሳሱና የመጣበትን ዓላማ ቅድሚያ መፈጸም እንደሚገባው ሲያስረዳ ነበር፡፡
ምሥጢር መጠበቅ በጎ ዕቅድንም ይጨምራል፡፡ ያለ ጊዜው የወጣ በጎ ዜናም ሆነ ዕቅድ በአፍ ይቀራል፡፡ ሳይሠራ ፈተና ይበዛበታል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ሳይሠሩ ቀድሞ ‘እሠራለሁ’’ ብሎ ነጋሪት መጎሰም ለጠላት ማንቂያ ደወል ነው፡፡ አበው ‘የሰይጣን ጆሮ አይስማ’ የሚሉት ለሰይጣን ብቻ አይደለም፡፡ አንዳንድ ነገር ሳይሠራ ተወርቶ ይዳረሳል፡፡ ክፋቱ በጣም ያወራከው ነገር የሰራኸው የሚመስልህ ነገር ነው፡፡ ብዙ ካወራህ በኋላ ያወራኸውን ከሰራኸው ለመለየት መቸገርህ አይቀርም፡፡ ዝም ብሎ መሥራትን የመሰለ ደግሞ ምንም ነገር የለም፡፡ ችግሩ ‘አሣ ሳትይዝ አሣ እጠብሳለሁ አትበል’ እንደሚባለው ከሥራ ማኒፌስቶው መቅደም የለበትም::

#Share
@diyakon_henok_haile

3. አንዳንዴ ደግሞ "በምሥጢር እየሥራ" መሆኑን የሚያወራም ሰው አለ:: ጳውሎስ ኞኞ በጻፈው አሁን የማላስታውሰው ጽሑፍ ላይ በድሮ ዘመን ደረታቸው ላይ "የምሥጢር ፖሊስ" የሚል ጽሑፍ የተለጠፈባቸው ሰላዮች ነበሩ ይባላል:: ምሥጢሩም እንዳይቀር ጉራውም እንዳይቀር ነው ነገሩ:: እንዲህ ያለ ነገር ስንት ሥራ አበላሽቶአል መሰላችሁ?!
ዝም ማለት የቻለ ተቋም ወይም ግለሰብ ባይሠራ እንኳን ዝምታው ግርማ ይሆነዋል፡፡ ‘ሬሳ የሚፈራው ለምንድር ነው? ቢሉ ዝም ስለሚል’’ ይባላል፡፡ ዝም የሚል ወገን ባይሠራ እንኳን ‘ዝም ያለው ምን እየሠራ ነው?’’ ያሰኛል፡፡ መረዳት ከቻልን ውስጥ ውስጡን የልባቸውን እየሠሩ ፣ በፈለጉት ቦታ የፈለጉትን እያስቀመጡ ፣ ንብረት እያፈሩ ፣ እየተደራጁ ጸጥ የሚሉ እንዳሉ ሁሉ ላይ ላዩን ደግሞ እያወሩ ምንም የማይሠሩ ዓለምን ሞልተዋታል፡፡
ሥጋትንህንም ሁሉ መደበቅ አንድ ብልህነት ነው፡፡ አንዱን ሰውዬ ዘራፊዎች አግኝተው ቅጥቅጥ አደረጉት ይባላል፡፡ ኪሱን ሲፈትሹ ግን ያገኙት አምስት ብር ብቻ ነው፡፡ ብስጭት ብለው ‘’አንተ ለ አምስት ብር ብለህ ልትሞት ነበር እንዴ?’’ ሲሉት ‘አይ እኔማ ካልሲዬ ውስጥ የደበቅኩትን አምስት መቶ ብር ትወስዱብኛላችሁ ብዬ ፈርቼ ነው’ ብሎ አረፈው፡፡
በዚህ ዘመን አንደበትን ያለመሰብሰብ ችግር እንደዚህ ሰውዬ እየጎዳንም ነው፡፡ እንዲህ ሊያደርጉ ነው ፣ እንዲህ ሊሠሩ ነው ወዘተ በሚል ጥቆማ ተበረታትተው ብዙ ክፉ የሠሩና የሚሠሩ ዘራፊዎች አሉ፡፡ አንዳንዴም እንደ ባለ አምስት መቶ ብሩ ሰውዬ ያላሰቡትን ያሳሰብናቸው ቀማኞች አሉ፡፡ የማይተዋወቁትን ሰዎች ሳናውቅ አብረን ሰድበን አንድ ያደረግናቸው ፣ የማይታወቁትን ሰዎች በነቀፋ ጀግና ያደረግናቸው ብዙ ናቸው፡፡
የዚህ ዘመን መሻገሪያ ወርቃማ ሕግ አንደበትን መቆጠብ ፤ የቻለ ድምጽ አጥፍቶ በጎ መሥራት ፣ ያልቻለም የሚሠሩ ሥራዎችን በአንዳንድ ነጋሪቶች አለማደናቀፍ ነው፡፡

‘ኢየሱስም ያዩትን እንዳይናገሩ አዘዛቸው’’

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
#Share
@diyakon_henok_haile
9.1K viewsᴍɪᴄᴋʏ, edited  05:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-06 08:46:48
7.2K viewsᴍɪᴄᴋʏ, 05:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-05 20:26:09 + ያደረግሽው ምንድን ነው? +

አዳም ዕፀ በለስን በበላና ክብሩን ባጣ ጊዜ እግዚአብሔር ሲጠይቀው እንዲህ አለ :- ከእኔ ጋር እንድትሆን የሠጠኸኝ ሴት ከዛፉ ሠጠችኝና በላሁ::

ከዚያ በኁዋላ ግን እግዚአብሔር ለሔዋን :- ለምን ዛፉን ብላ ብለሽ ሠጠሽው? አላላትም:: የተናገረ አንድ ዐረፍተ ነገር ነው - "ያደረግሽው ምንድነው" ብቻ አላት::

@diyakon_henok_haile
እርሱ በሰዎች አስተያየት አይፈርድም:: ሌላው ስለ አንተ የሚለውን ትቶ አንተን ለብቻህ ይጠይቅሃል:: የሰዎችን ግምገማ አይሰማም:: እንደ ሃናንያ "ኸረ ጌታ ሆይ ክርስቲያኖችን ሲያሳድድ ነበረኮ" ቢሉትም ቸል ብሎ ምርጥ ዕቃው ያደርግሃል:: በድንጋይ ልትወገር ይገባታል ሲሉት እየሰማ ክሱን ትቶ ከሳሾችዋን ሊከስስ መሬት ላይ ይጽፋል:: ዐሥርቱ ትእዛዛትን በጻፉ ጣቶቹ ዘማዊትዋን ሴት ነጻ ሊያወጣ አፈር ይጭራል::

#Share
@diyakon_henok_haile

ሰው ጨካኝ ፈራጅ እንደሆነ ያውቃልና በአዳም አስተያየት ሔዋን ላይ አይፈርድም:: ምንም ብታጠፋም "ያደረግሽው ምንድን ነው?" ብሎ ጠየቃት::

እግዚአብሔር ዛሬም ነፍሳችንን ይጠይቃታል::

ያደረግሽው ምንድን ነው? የአዳምን ክስ ሰምቻለሁ! ሰዎች ስለ አንቺ የሚሉትን አዳምጫለሁ:: አንቺ ግን ንገሪኝ:: ግራውን ሰምቼ አልፈርድም:: ምናልባት ቀኙን ብሰማ ይሻላል የሚል ርኅሩኅ አምላክ ነው::
እኛ የምንፈርድባቸው ሰዎች ሁሉ ቢጠየቁ የሚናገሩት የየራሳቸው የታሪክ ማዕዘን (side of the story) አላቸው::
ስለዚህ እግዚአብሔር አዳምን ሰምቶ አልፈረደም ሔዋንን ጠርቶ ጠየቃት
"ያደረግሽው ምንድን ነው?"

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
#Share
@diyakon_henok_haile
7.6K viewsᴍɪᴄᴋʏ, edited  17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-05 20:25:55
6.6K viewsᴍɪᴄᴋʏ, 17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ